• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ

August 13, 2025 12:16 pm by Editor 1 Comment

* ይግባኝ ለማለት ወደ ፖለቲካው መመለስ የግድ ሆኖበታል

በአሜሪካ የጥገኝነት ማመልከቻ ያስገባው አቶ በቀለ ገርባ የስደት ፈቃድ ማመልከቻው ውድቅ ተደረገ። በድጋሚ እንዲታይለት ይግባኝ መጠየቁም ታውቋል። ዳግም ወደ ፖለቲካ ተሳትፎ የተመለሰውም በዚህ ሳቢያ እንደሆነ ተመልክቷል።

ከእስር ከተፈታ በኋላ ምስጋና ለማቅረብ ወደ አሜሪካ ከጃዋር ጋር ያመራው አቶ በቀለ በምስጋና ጉዞው ወቅት ከአቶ ጃዋር ሲራጅ መሐመድ ጋር ባለመግባባት መለያየቱና ይህ አለመግባባት አዲስ አበባ እያሉ የተጀመረ እንደነበር ጉዳዩን የሚያውቁ ማስታወቃቸው አይዘነጋም።

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበረው አቶ በቀለ ገርባ ከፓርቲው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) በመልቀቅ በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቁን ይፋ ያደረው ራሱ በቢቢሲ በኩል ነበር።

ወደ አሜሪካ ከመጣ አንድ ዓመት ከሦስት ወር እንደሞላው ገልጾ ለቢቢሲ ምክንያቱን ያስረዳው አቶ በቀለ ገርባ፣ “መጀመሪያ ስንመጣ የነበረኝ ዕቅድ በውጭ ከሚኖረው ሕዝባችን ጋር ተገናኝተን፣ አንደኛ ከእስር እንድንለቀቅ ላደረጉት ትግል ለማመስገን ሁለተኛ ደግሞ ወደፊት ምን ማድረግ አለብን የሚለው ላይ ለመወያየት ነበር” ካለ በኋላ፣ አሜሪካ በቆየባቸው 15 ወራት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በመቀየሩ “ወደዚያ አገር መመለሱ አስፈላጊ መስሎ አልታየኝም” ሲል አስታውቆ ነበር።

የስደት ማመልከቻውን ያየው ፍርድ ቤቱ ችግር መኖሩን ገልጾ ወደ አገር ቢመለስ ለሕይወቱ አስጊ ጉዳይ እንደሌለ በመጥቀስ ማመልከቻቸውን ውድቅ ማድረጉን የፍርድ ሂደቱን የሚያውቁ ገልጸዋል።

አቶ በቀለ በዕድሜ የገፋ ሰው መሆኑና በዚህ ዕድሜው የተረጋጋ ሕይወት ሊኖር የሚገባው ወቅት መሆኑን ያስታወቁት እነዚህ ወገኖች አቶ በቀለ በጠበቃው አማካይነት ይግባኝ መጠየቁን ገልጸዋል። ውሳኔው ሊቀየር እንደሚችልም ገምተዋል።

በቅርቡ በጀርመን ድምጽ “ምነው ጠፉ?“ በሚል ለቀረበለት ጥያቄ “አዎ ትክክል ነዉ። ብዙም አልታይም። ተሳትፎዬ ላይ አንዳንድ ገደቦች አድርጌያለሁ። ገደብ ያደረኩባቸዉ ምክንያቶችም፤ አንደኛ፤ ቀድሞ የፓርቲ ኃላፊነቴ የሚጥልብኝ ግዴታ ነበረ። ስለዚህ በኃላፊነቴ ወጥቼ መናገር ይገባኝ ነበር። አሁን ግን ያ ኃላፊነት የለብኝም። ሁለተኛ፤ እኔ ማድረግ የምችለዉን ነገር ሌሎች አገር ዉስጥም ከአገር ዉጭም ያሉ ሰዎች አሉ። ስለዚህ አንዱ የሚናገረዉን መልሶ መናገር አስፈላጊነቱ ብዙም ስለማይታየኝ፤ ሌላዉ ሰዉ ከሠራዉ የሚል አስተያየት ስላለኝ ነዉ” የሚል መልስ አቶ በቀለ ሰጥቶ ነበር።

ከሁሉም በላይ እንደ ዋና ምክንያት ያቀረበውና “ሦስተኛ” ያለው ምክንያት ” … ዋንኛዉ ደግሞ በኢትዮጵያ የፖለቲካዉ አካሄድ፤ ቀድሞ ከማዉቀዉ እና ከማስበዉ አካሄድ ዉጭ እየተጓዘ በመሆኑ ነዉ። የፖለቲካ ባሕሉ እጅግ ተቀይሯል። ድሮ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት አነሰም በዛ፤ በክርክር በሃሳብ የበላይነት በዉይይት፤ ባይስማሙም ተቀራርቦ በመነጋገር ጥረት ይደረግ ነበረ። አሁን ግን ያ ሁኔታ አይታይም። ሚዲያን ያለአግባብ ኢ፡ሞራላዊ በሆነ መንገድ፤ በገፍ በመጠቀም አድማጭን በማደናገር እና የመጡብህ ፖለቲካ ፍርሃትን በማሰራጨት ፖለቲካዉ በጣም ቆሽሿል” የሚል ነበር።

አቶ በቀለ ይህን ባለ ሳምንታት ውስጥ በሲያትል ተደረገ በተባለ የኦሮሞ ልሒቃን ስብሰባና ኅብረት፣ እንዲሁም “ከዐቢይ ውድቀት በኋላ’ በሚል ጃዋር ባዘጋጀው የዙም ውይይት ላይ ተናጋሪ ሆኖ ታይቷል።

ይህንኑ ተከትሎ የተሰጠው አስተያየት አቶ በቀለ ከተለየው ፖለቲካና ”ቆሽሿል” ካለው የሚዲያ አጠቃቀምና የፖለቲካ ዐውድ ዳግም የተመለሰው ምን አልባትም ይግባኝ ላለበት የስደት ማመልከቻው ግብዓትና ተጨማሪ ማስረጃ እንዲሆነው በማሰብ ሊሆን እንደሚችል የሚያመላክቱ ሆነዋል።

ይህንኑ አስመልክቶ ያነጋገርናቸው ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣን ”አቶ በቀለ ወደ አገራቸው ተመልሰው መሥራትና በሙያቸው አገራቸውን ማገልገል ይቻላሉ። ምንም ስጋት ሊገባቸው አይገባም። እንደውም ትብብር ይደረግላቸዋል” የሚል አስተያየት ሰጥተዋል። (𝖊𝖙𝖍𝖎𝖔𝖗𝖊𝖛𝖎𝖊𝖜.𝖔𝖗𝖌)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: bekele gerba, Immigration case denied, jawar, Jawar Mohammad, ofc

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    August 14, 2025 05:10 pm at 5:10 pm

    የራስን ቤትና ሃገር እሳት እየለኮሱና እያስለኮሱ እግሬ አውጭኝ የሚለው የሃበሻ የብሄር ሰካራም ሁሉ አሁን ላይ መግቢያ እያጣ ነው። ትላንት በውሸት ጋብቻው፤ በስርቆት ወረቀትና በሌላም አሻጥር የውጭ ሃገር የመኖሪያ ፈቃድ አግኝተው መንግስት በሰጣቸው የድጎማ ገንዘብና ቤት ውስጥ እየተንፈላሰሱ ሃገር ቤት ሃሎ እያሉ ያላቸውን ቢዝነስ ሲያሳልጡ የነበሩ ሁሉ አሁን ላይ እየተጋለጡና ራሳቸውን እያጋለጡ ወደመጡበት በመመለስ ላይ ይገኛሉ። ከዚህም በከፋ ሁኔታ እናትና አባቶቻቸውን ከመሸ አሻግረው ባልኖሩበትና ባልሰሩበት ሃገር ጡረታ ተቀባይ ያደረጉ ሁሉ አሁን ላይ አይን ፍጥጥ ሆኗል። እማማና አባባ ከሞቱ ዘመን አልፏል እነርሱ ግን እስከ ዛሬ ድረስ በሙት ስም ገንዘብ እየተቀበሉ መኖራቸው ተረጋግጦ በባዕድ ሃገር ዘብጥያ የወረድ አሉ። ብቻ ስለ አፍሪቃዊያን የማታለል ስልት ማን ተጠቅሶ ማን ይቀራል። ከናይጀሪያው እስከ ሱማሊያ ከአዲስ አበባ እስከ አስመራ የማይፈጸም ግፍና በደል የለም። በሃበሻዋ ምድር ነገር ሁሉ ከመጣረሱ የተነሳ ህጻናትን አፍነው ገንዘብ አምጡ የሚሉ እብዶች ተፈልፍለዋል። ሃገር ሲያረጅ አሜኬላ ያበቅላል ይባል የለ።
    ታዲያ አቶ በቀለ ገርባ በኦሮሞ የጠባብ ብሄርተኞች ፓለቲካ ሰበብ እንደ ለማኝ አቆማዳ በሄደ በመጣው የሃበሻ መንግስት ሲታሰር ሲፈታ የኖረ ቆይቶ ደግሞ ሁሉም ነገር ተማቶበት የቋንቋው መምህር ለኦሮሞዎች በቋንቋችሁ ለማያናግራችሁ እቃ አትሽጡ እስከማለት የደረሰ አሁን ላይ የመሸበት ፓለቲከኛ ነው። በቀለ ገርባ ሃገር ቤት ቢመለስ ማንም አይነካውም። ራሳቸው አበጥረውና ፈጭተው ያቀረቡት ፓለቲካ ነው አሁን ሃገሪቱን እያመሳት ያለውና! ሃገር በብሄር የአፓርታይድ ክልል ተሸንሽና ሰላም ሊኖር አይችልም። ከለለ ማለት ለእኔ አለ/አጥር አበጀ ማለት ነው። ለዚህ ነው ዛሬ ላይ ግዛታችን ተይዞ እያለ ወያኔ የሚያላዝነው። ፓለቲከኞች ጀለፎዎች ናቸው። ካለፈው እንከፍ የፓለቲካ አካሄድና እይታ ጭራሽ አይማሩም። Game over ያለን የኤርትራው የእድሜ ልክ መሪ አሁን ላይ ከወያኔ ትራፊ ቡድን ጋር ቂጥ መግጠሙ ምን ያህል የሃገራችን ፓለቲከኞች በተሰላ መንገድ እንደማይራመድ ያሳያል። የትላንቱ ከአስመራ አዲስ አበባ የሁለቱ መሪዎች ሽርሽር ምን ፍሬ አፈራ? ዜሮ! ወያኔስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሻቢያ በትግራይ መሬት ግፍ ሰርቶ መሬታችን ይዞ እያለ ሲያለቅስ የነበረውን ዋይታ የት አስገባው? ስለዚህ የወያኔ ከሻቢያ ጋር መጣመድ ሌሎችም በሃገር ውስጥ ህዝብን የሚያስጨንቁ ታጣቂዎች ሁሉ ከወያኔና ከሻቢያ ጋር ማበር ለኢትዪጵያ ህዝብ የሚያመጣው አንድም መልካም ነገር አይኖርም። እርስ በእርሱ የማይተማመን ባልንጀራ በየወንዙ ይማማል እንዲሉ እንኳን መንግስት ሊሆኑ የቀን ተቀን እቅዳቸውን እንኳን በውል አያውቁም። ታዲያ ከብልጽግና ማግስት ሻቢያና ወያኔ የሃገር አለቃ እንዲሆኑ ነው የሚሰሩት ወይስ ከዚህ የተሻለ ጥምረትና ሃሳብ አላቸው? የሰማነው ምንም ነገር የለም። ዝም ብሎ በደመ ነፍስ መውተርተር ነው። ይህ ሁሉ ከአቶ በቀለ የጥገኝነት አለመሳካት ጋር ምን አገናኘው ይል ይሆናል አንባቢ። በደንብ ነው የሚገናኘው። ያኔ ሰው በላው ኢምፔሪያሊዝም እያሉ አልባኒያንና ራሺያን ሲልላቸውም ቻይናን ሲያሞካሹ የነበሩ የጊዜው ፓለቲከኞችና ታጣቂዎች አሁን ላይ ያሉት በምዕራቡ ዓለም እንጂ በአመለኳቸው ሃገሮች በአንድም አይደለም። ታዲያ አሁንም ትርምስ ቢፈጠርና የዛሬው ታጣቂ በሌላ ታጣቂ ስልጣኑን ቢቀማ ሽሽቱ ወደ ዋሽንግተን፤ ለንደንና ፍራንክፈርት እንጂ ሌላ ሃገር አይሆንም። ግን ትላንት ዛሬን አይሆንምና ምንም ቢሆን ምንም ነጩ ዓለም ጥቁሩን ዓለም ማስተናገድ ሰልችቶታልና ያ እድል አይገኝም ቢገኝም ሰርቶ መኖር ራሱ የመከራ መከራ ነው የሚሆነው። ስለሆነም ለአቶ በቀለ ያለኝ ወንድማዊ ምክር ወደ ሃገር ቤት ይመለስና የሚሆነውን ሆኖ ቀሪ ዘመኑን ከቤተሰቡና ከወገኖቹ ጋር ቢያሳልፍ መልካም ነው እላለሁ። ቢታሰርም አሳሪውን መንግስት የበለጠ ያሳጣል እንጂ በአቶ በቀለ ገርባ የሚፈርድ አንድም ኢትዮጵያዊ አይኖርም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule