* ዳያስፖራው ራሱን ከትግሉ እያገለለ ነው ከሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በተደረገ ተከታታይ ስምሪት የፋኖ ኃይል እጅግ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለጸ። በተለይ በራያ ቆቦ ወረዳ የተደረገው ሥምሪት ባካባቢው በሚገኘው የፋኖ ኃይል የደረሰው ጉዳት መጠነ ሰፊ እንደሆነ ተመልክቷል። በፋኖ ተስፋ የቆረጠው ዳያስፖራ ከሚኖርበት ሀገር የገጠመው ችግር ተጨምሮ ለፋኖ የሚሰጠውን ድጋፍ እየቀነሰ ነው። እስከ ዛሬ ድረስ በራያ ቆቦ ወረዳ በአማያ፣ በባይባዋ፣ በፀበለት እና አካባቢው በተደረገው ተከታታይ ስምሪት የመከላከያ ሠራዊት በፋኖ ላይ ባደረሰው ከፍተኛ ምት ንብረቱን፣ ትጥቁን እና ተተኳሹን በመተው ከአካባቢው ሲለቅቅ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 802ኛ ኮር አካል የሆነው 48ኛ ክፍለ ጦር በተጠቀሱት ቦታዎች እና ልዩ ሥፍራው "አካምባ" በሚባል ቦታ ፈጥኖ በመድረስ የፋኖው ኃይል ጥሎት … [Read more...] about የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ
North Wollo Fano
“ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን”
”ነገሮች ተበላሽተዋል” በሚል የፋኖ አሰባሳቢ ኮሚቴ ናቸው የሚባሉት ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ ከመስከረም ጋር በስልክ ያደረጉትን ንግግር ይፋ በሆነ ማግስት በሰሜን ወሎ ዞን አካባቢ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበልና ይፋዊ ይቅርታ በማቅረብ ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለሳቸውን የአማራ ክልል አስታወቀ። ክልሉን ጠቅሶ የአማራ ማስ ሚዲያ ይፋ እንዳደረገው በሰሜን ወሎ ዞን አካባቢ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበልና ይፋዊ ይቅርታ በማቅረብ ወደ መደበኛ ህይወታቸው ተመልሰዋል ብሏል። “ተታለን ነው” በሚል ሽማግሌ የላኩትን የሰሜን ወሎ ፋኖዎች ጥያቄ ለመቀበል የአገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ከዚህ በኋላ ምንም አይነት መንገድ እንዳይዘጋ፣ምንም አይነት የታጠቀ አካል ከተማ ውስጥ እንዳናገኝ … [Read more...] about “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን”


