* “ዓለም እያዘነብን እየሳቀብን ነው አንድ እንሁን” - ዘመነ ካሤ አርበኛ ዘመነ ካሴ “ዓለም እያዘነብንም እየሳቀብንም ነው” በማለት “መተው ነገሬን ከተተው" እንደሚባለው በመተው "አንድ እንሁን" የሚል ጥሪ አሰማ። ፋኖ ኢትዮጵያን ሠርቶ ምስራቅ አፍሪካን ያረጋጋል ብሏል፤ አንድነት ለመፍጠር “አንድ ማንኪያ ቅንነት” ነው የሚያስፈልገው አለ። በጎጃም እና በደቡብ ጎንደር የተሰማራው የአገር መከላከያ በበኩሉ ስም፣ ቦታና ኃላፊነት ጠቅሶ በፋኖ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን አስታውቋል። የዘመነ መልዕክት የተሰራጨው የመከላከያ መረጃዎች እኩል ቀን ነሐሴ 16 በሪፖርት መልክ ይፋ ከሆነ በኋላ ነው። "የዕለቱ መልዕክት" በሚል የአማራ ፋኖ በጎጃም መሪ ዘመነ ካሴ "በቃ መተው እንልመድ" ሲል የተለያዩትን የፋኖ አመራሮችና አደረጃጀቶች ዘርዝሮ " ... አንድ መሆን አለበት" … [Read more...] about መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ
endf
በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ
የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የምልምል ሰልጣኞች የስልጠና መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል። ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ በሥልጠና መክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ሥልጠናው መጀመሩን በይፋ ያበሰሩት በሰላም ማሰከበር ማዕከል የኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አዛዥ ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ መከላከያ ወድ ህይወቱን ሳይሰስት የሚሰጠውን ሃገራዊ ተልዕኮ በስኬት የሚፈፅም የሀገር ኩራት መሆኑን አንስተዋል። ውትድርና ሀገር ወዳድ የሆነ ኢትዮጵያዊ ለሃገር ዘብ እቆማለሁ ብሎ በፍላጎት በተነሳሽነት በቁርጠኝነት እና በታማኝነት አገልግሎት የሚሰጥበት የሚያኮራ ሙያ መሆኑንም አዛዡ ገልፀዋል፡፡ ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ከመላው የሃገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ተመልምለው መመልመያ መሥፈርቱን አሟልተው የመጡ አዲስ ወጣቶችን እያሠለጠነ የሚያበቃ ነውና … [Read more...] about በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ
በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ
እስካሁን በደቡብ ጎንደር እና በጎጃም 127 እጃቸውን ሰጥተዋል የመከላከያ ሠራዊት ባደረገው ተከታታይ ስምሪት ጠላትን በማሳደድ፣ በመክበብ እና በመደምሰስ ከፍተኛ ድሎችን አስመዝግቧል። በዚህ ኦፕሬሽን ክፉኛ አከርካሪው የተሰበረው ብረት ነካሽ ግማሹ ህይወቱን ለማዳን በየበረሀው ሲወሸቅ ቀሪው ደግሞ ለሠራዊታችን እጁን እየሰጠ ይገኛል። በጎጃም በሚገኙ አራት ዞኖች እና በደቡብ ጎንደር የተሰማራው ምስራቅ ዕዝ እና ተደራቢ ክፍሎች ከአማራ ክልል የፀጥታ ሀይል ጋር ባደረጋቸው ዘመቻዎች መላወሻ ያጣው የፅንፈኛው ቡድን ከግንቦት አንድ ወዲህ ብቻ 127 ታጣቂዎቹ ለወገን እጃቸውን ሰጥተዋል። እነዚህ ታጣቂዎች ሞርተር፣ ድሽቃ፣ ፒ ኬ ኤም/መትረየስን ጨምሮ የተለያዩ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን እና ትጥቆቻቸውን ጭምር በመያዝ ነው እጅ የሠጡት። በተለይም በጸዳሉ ደሴ የተመሩት … [Read more...] about በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ
ዘመኑን የጠበቀ የወታደራዊ ሬዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ተከፈተ
በመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የኤሌክትሮኒክስ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ የራዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣ የጦር ሀይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ እና የተቋሙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በተገኙበት ነው ተመርቆ የተከፈተው። የመከላከያ ሰራዊታችን አገራችን በየጊዜው የገጠሟትን ፈተናዎች በሌሎች አገራት ቴክኖሎጂዎች ላይ በመመርኮዝ ግዳጅ እየተወጣ እንደዘለቀ አውስተው የተመረቀው የወታደራዊ ራዲዮ ፋብሪካ የሰራዊቱን የተልዕኮ አፈፃፀምና የግዳጅ ስምሪት የሚያቀላጥፍ እንደሆነ ተናግረዋል። "ወታደራዊ ራዲዮው በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ የመጨረሻው የዲጅታል ስታንዳርድ ራዲዮ ነው።" ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ይህንኑ እውን በማድረግ ረገድ የቻይናው ሀይቴራ ካምፓኒ እና የመከላከያ … [Read more...] about ዘመኑን የጠበቀ የወታደራዊ ሬዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ተከፈተ
የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
በ116ኛው የሠራዊት ቀን ሲከበር ንግግር ያደረጉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ “ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበትን ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እንዲከበር ተደርጓል” በማለት ቀኑ ለምን እንደተመረጠ ይፋ አደረጉ። ከዚህ ሌላ ፊልድ ማርሻሉ በንግግራቸው፤ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ከጀግኖች የተረከብናትን ኢትዮጵያ እንደተከበረች እና ማንነቷ እንደተጠበቀ ለማስቀጠል ወታደራዊ ዝግጁነታችንን አሳድገንና ቁመናችንን አዘምነን ማንኛውንም ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለመፈጸም ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አሣውቀዋል። የሠራዊቱ አባላት የተሠጣቸውን ታላቅ አደራ በድል ለመወጣት የመፈጸም ብቃታቸውን በማሣደግ በዓላማ ጽናታቸው እንዲቀጥሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አሳስበዋል፡፡ ሠራዊቱ ሀገሩን እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን … [Read more...] about የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
ጥቅምት 15 ለምን?
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአዲስ መልክ ጥቅምት 15 ቀን ላይ መከበሩ ለምን እንደሆነ ከዚህ በታች ለመረዳት እንዲቻል በቀላሉ የተሠራውን መግለጫ ይመልከቱ። ስለ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የማዕረግ ምልክቶች ምን ያህል ያውቃሉ? ከ"ፊልድ ማርሻል ጄነራል" ጀምሮ እስከ "ምክትል አስር ዓለቃ" ድረስ በአጠቃላይ 18 ማዕረጎች ይገኛሉ። የማዕረጎቹን ዝርዝር ከነምልክቱ እነሆ፦ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ጥቅምት 15 ለምን?
“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት " በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው ለዘንድሮ ለ116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን። እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ የረዥም ዓመታት ሀገርን ከጠላት የመከላከል የተጋድሎ ታሪክ ካላቸው ሀገራት መካከል በጀግኖች ልጆቿ የአይበገሬነት ፊት የምትሠለፍ ታሪካዊት ሀገር ናት። ከቀደመው ዘመን ጀምረን አሁን ላይ ያለውን እውነታ እንኳ ብንቃኝ ኢትዮጵያ በርካታ የውጪ ወራሪ ሀገራት ያሠፈሠፉባት ጥቂት የማይባሉ የውስጥ እርስ በርስ ግጭቶች የተከሰቱባት በባንዳዎች የተፈተነችበትና በየትኛውም ዘመን ያልተንበረከከች የወራሪዎችን ፈተና አልፋ ዛሬ ላይ የደረሠች ሥለመሆኗ የታሪክ ድርሳናት መዝግቧል። በሀገራችን የጀግንነት የታሪክ መዝገብ ያልሠፈሩ ግን ደግሞ አለም ያወቃቸው ቱባ ባህሎችና ድንቅ ታሪኮች ያላት ኢትዮጵያ በታሪክ … [Read more...] about “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”
“ውትድርና ሕይወቴ ነው”
ኢትዮጵያዊያን በሀገራችው ሰማይ ስር የመጣን ጠላት በማሽመድመድ ካስመዘገቡት ደማቅ ታሪክ ፊት ለፊት ትልቁን ድርሻ ከሚወስዱት አንዱ ናቸው። ለሀገራቸው በዋሉት ውለታ ከሚተረክላቸው ቀዳሚ ባለ ታሪኮች ቀድመው ይጠቀሳሉ። ሙሉ ህይወታቸውን ለሀገራቸው የሰጡ ናቸው። ጀግና ተዋጊ፣ የበቁ የጦር መሪ፣ የተሳካላቸው የጦር አዛዥ ሆነው አገልግለዋል። በበርካታ የጦር ሜዳ ውጊያዎች ተሳትፈው የሀገርን ሉዓላዊነት፣ የህዝብን ነፃነት ያስከበረ ደማቅ ድል አስመዝግበዋል። ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያም። ጄኔራል መኮንኑ በ1934 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ከቸሀ ወረዳ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሲሰ መንደር ተወለዱ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም እዚያው እምድብር ከተማ ተምረው በ1948 ዓመተ ምህረትም አጠናቀዋል። ከ1949-1952 ዓ.ም ድረስ አምቦ የእርሻ ልማት … [Read more...] about “ውትድርና ሕይወቴ ነው”
መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
አየር ኃይል የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አስተማማኝና ዘመናዊ አየር ኃይል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በተለይም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ አየር ኃይሉ በሁሉም ረገድ በመዘመንና ስኬታማ በመሆን ሀገር የምትኮራበት ታላቅ ተቋም መሆኑንም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አሁን ላይ በውጊያ መሠረተ-ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና አጠቃቀም በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቡን በተቋሙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተማማኝ የሀገር መከታ በመሆን ለየትኛውም ግዳጅ አፈጻጸም ብቁና ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ዘመናዊ ተቋም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በአየር ኃይል … [Read more...] about መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች
የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል ያሠለጠናቸውን የመሠረታዊ ኮማንዶ አባላት አሥመርቋል።በዚሁ የምርቃት መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር) ከተናገሩት የተወሠደ፦ 👉 የኢትዮጵያ ሠራዊት መሆን ያኮራል ፤👉 ሠራዊቱ ሁለት ዓላማዎች አሉት 1ኛ ጥፋት ውድመት እና ሌላ ክስተት እንዳይፈጠር ውጊያን ማሥቀረት 2ኛ ውጊያን መጨረስ ፤👉 ውጊያን ሠው ጀምሮ ሠው አይጨርሰውም የምንዋጋው በቴክኖሎጂ የምንጨርሰው በሠራዊቱ ነው ፤👉 ውጊያን ጨርሳችሁ ድል የምታደርጉት እና የኩሩ ህዝቦች መዝሙር የምትዘምሩት እናንተው ናችሁ ፤👉 ለሀገራችሁ ሶስት ነገሮችን ስጡ 1ኛ እንድታሥቡ አዕምሯችሁን 2ኛ ለሀገር ፍቅር ልባችሁን 3ኛ እንድትሠሩ እጃችሁን ፤👉 ኢትዮጵያ የሀገር ፍቅር እና የመለዮ … [Read more...] about ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች










