”ነገሮች ተበላሽተዋል” በሚል የፋኖ አሰባሳቢ ኮሚቴ ናቸው የሚባሉት ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ ከመስከረም ጋር በስልክ ያደረጉትን ንግግር ይፋ በሆነ ማግስት በሰሜን ወሎ ዞን አካባቢ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበልና ይፋዊ ይቅርታ በማቅረብ ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለሳቸውን የአማራ ክልል አስታወቀ። ክልሉን ጠቅሶ የአማራ ማስ ሚዲያ ይፋ እንዳደረገው በሰሜን ወሎ ዞን አካባቢ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበልና ይፋዊ ይቅርታ በማቅረብ ወደ መደበኛ ህይወታቸው ተመልሰዋል ብሏል። “ተታለን ነው” በሚል ሽማግሌ የላኩትን የሰሜን ወሎ ፋኖዎች ጥያቄ ለመቀበል የአገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ከዚህ በኋላ ምንም አይነት መንገድ እንዳይዘጋ፣ምንም አይነት የታጠቀ አካል ከተማ ውስጥ እንዳናገኝ … [Read more...] about “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን”
endf
የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል
የኮማንዶ ብርጌዱ የተሣካ የተልዕኮ አፈፃፀሙ ታይቶና ተገምግሞ በ1992 ዓ.ም በክፍለጦር ደረጃ ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ከክፍለጦር በላይ ሆኖ መደራጀቱም እንዲሁ፡፡ በሀገራችን ላይ የሚፈፀም ማንኛውንም ትንኮሳ መመከት እና መደምሰስ የሚችል አደረጃጀት ለመፍጠር በማሰብ የልዩ ኃይልና የአየር ወለድ አሃዱዎችን በማሥፋት የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሚለውን ስያሜ እና አደረጃጀት አሁን ላይም ይዞ ይገኛል፡፡ የሚሠጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በእምነት የሚፈፅምና በከፍተኛ ፅናት ዘብ የሚቆም እንዲሁም በተሰማራበት የውጊያ ውሎ የውጊያው ማርሽ ቀያሪ እና አይበገሬ ሠራዊት በመገንባት ባሳለፍናቸው ዘመቻዎች አኩሪ የጀግንነት ገድል እንደ ዕዝ በመፈፀም የላቀ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል፡፡ በኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ሥር ካሉት ወታደራዊ የአቅም ግንባታ … [Read more...] about የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል
“ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት እየገነባን ነው የመከላከያ ሠራዊት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ "የጥንካሪያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው" በሚል መልዕክት የፓናል ውይይት ተካሄደ። በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር አብርሐም በላይ (ዶክተር)፣ አሁን በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ግንባታ ከፍተኛ አቅም ተፈጥሯል፤ ከሩቁ የሚፈራ መከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላቶች ሳንቆም ሊጥሉን ሞክረዋል፤ አሁን ቆመን ማንም ሊነቀንቀን የማይችልበት ደረጃ ደርሰናል ያሉት ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ጊዜ ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ሠራዊት መገንባት መቻሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የግዛት አንድነቷ በማንም እንደማይሸረፍ በመስዋዕትነት የሚያረጋግጥ ጀግና ወታደር ያላት ሀገር እንደሆነች የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይህን በተግባር እያረጋገጠ … [Read more...] about “ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
“በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት” የሰላም ንግግሩ ይቀጥላል – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቁልፍ የሚባሉ የትግራይ ከተሞችን መቆጣጠሩን ቀጥሏል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። ይህንን ሲያደርግም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውጊያ ሳይደረግ የህወሓትን ወታደራዊ ዐቅም ለማሽመድመድ የሚያስችል ስልት ተጠቅሟል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከሰብአዊ የርዳታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሰብአዊ ርዳታ እንዲደርስ እየሠራ ይገኛል። የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በእነዚህ አካባቢዎች አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እንዲያፋጥኑ እያደረገ ነው። ከየአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር በመነጋገር ሕዝባዊ አስተዳደር የሚቋቋምበትንና ማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚጀምሩበትን መንገድ እያመቻቸ ይገኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፍሪካ ኅብረት በኩል በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር የሚሳተፍ ይሆናል። አጋጣሚውንም … [Read more...] about “በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት” የሰላም ንግግሩ ይቀጥላል – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያን “በእኛ ትውልድ ማንም ተነስቶ እንዲፈነጭባት አልፈልግም” ምክትል ፲ አለቃ በዝናሽ ወዳጆ
ኢትዮጵያ ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር የተሠጠኝን ግዳጅ በጀግንነት እወጣለሁ ትላለች ምክትል ፲ አለቃ በዝናሽ ወዳጆ። በሰቆጣ ግንባር የአሸባሪውን የህወሓት ታጣቂ ዶግ አመድ ካደረጉት ጀግኖች መካከል አንዷ ናት ምክትል አስር አለቃ በዝናሽ ወዳጆ። ምክትል አስር አለቃ በዝናሽ ወዳጆ እንደተናገረችው ኢትዮጵያን ተላላኪ የሽብር ቡድን ሰላሟን እንዳያደፈረስ ላፍታም ቢሆን ሳልዘናጋ የተሠጠኝን ግዳጅ በጀግንነት እወጣለሁ። አባቶች በመስዋትነታቸው ያስረከቡንን ሀገር በእኛ ትውልድ ማንም ተነስቶ እንዲፈነጭባት አልፈልግም። በተሰለፍኩበት ግንባር የሀገሬን ጠላት እስከ መስዋዕትነት ከፍዬ ግዳጄን በቁርጠኝነት እወጣለሁ ብላለች። (መከላከያ ሠራዊት) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ኢትዮጵያን “በእኛ ትውልድ ማንም ተነስቶ እንዲፈነጭባት አልፈልግም” ምክትል ፲ አለቃ በዝናሽ ወዳጆ
ደስታ ጌታሁን – የደጀንነት ጀብዱ
ወይዘሮ ደስታ ጌታሁን ነው የምትባለው፡፡ ይህች እህታችን በሰቆጣ ከተማ በትንሽዬ የዳስ ውስጥ ቡና እና ሻይ በመስራት ሁለት ልጆችዋን ታስተዳድራለች፡፡ ወይዘሮ ደስታ ለእናት ሃገሩ ኢትዮጵያ ለሚፋለመው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን የምታደርገው ነገር ግራ ቢገባትም ከልጆችዋ እና ከራስዋ የእለት ጉርስ ቀንሳ በግዳጅ ቀጠናው ለሚፋለሙ የሰራዊት አባላት ቡና እና ሻይ ይዛ ተገኝታለች፡፡ ወይዘሮ ደስታ ጌታሁን ሰራዊቱ በግዳጅ ላይ ፋታ ሲያገኝ ቡና እና ሻይ በማቅረብ ደጀንነቷን በጀግንነት አስመስክራለች፡፡ (ዘግባና ፎቶግራፍ፤ ልመነህ ሻወል የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ደስታ ጌታሁን – የደጀንነት ጀብዱ
ባህር ኃይል ለማዘመን ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
"የኢትዮጵያን ባህር ኃይል ለማዘመን ከሀገር ውጭ እና በሀገር ውስጥ የሚሠጡ ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ" ሲሉ ተናገሩ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ። የኢትዮጵያ ባህር ኃይል በአዲስ መልክ ከተመሠረተ ጀምሮ የተለያዩ አቅም ፈጣሪ ስልጠናዎችን ከሀገር ውጭ እና በሀገር ውስጥ አባላቱን በማሠልጠን ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ዋና አዛዥ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ በብላቴ የኮማንዶ እና የአየር ወለድ ኃይል ማሠልጠኛ ማዕከል ተገኝተው የማሪን ኮማንዶ የሚሠለጥኑ የባህር ኃይል አባላትን ጎብኝተዋል። ዋና አዛዡ የስልጠና ሂደቱን ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኋላ እንደተናገሩት የማሪን ኮማንዶ ሠልጣኞች በማሠልጠኛ ማዕከሉ የሚሠጡ ስልጠናዎችን በድሲፒሊን፣ በሞራል እና በብቃት መወጣት አለባቸው። እየተሠጠ ያለው ስልጠና ከሌሎች የሠራት ክፍሎች ጋር በመሆኑ የተሞክሮ እና … [Read more...] about ባህር ኃይል ለማዘመን ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው
የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ በኅልውና ዘመቻ እና በዘመቻ ለሕብረብሔራዊ አንድነት የግዳጅ ወቅት ከፍተኛ ጀግንነት ለፈጸሙ የመምሪያው አባላት የዕውቅናና የምስጋና መርኃግብር አካሂዷል። በመርኃግብሩ ላይ በመገኘት ሽልማቱን የሰጡት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሙሉዓለም አድማሱ እንደተናገሩት አሸባሪው የትህነግ ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ከፈፀመበት ጊዜ ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ሀገርን ከውድቀት ለመታደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። መምሪያው በቀጣይ የሚሰጠውን ሀገራዊ ግዳጅ በጀግንነት ለመወጣት ይበልጥ ዝግጁ መኾን እንደሚገባውም ምክትል አዛዡ አሳስበዋል። የዕዙ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ወርቅነህ ነዳሳ በበኩላቸው ክፍሉ በግዳጅ አፈጻጸም ወቅት … [Read more...] about የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው
በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
በሽብርተኛው የሸኔ ታጣቂ ሃይል ጉዳት የደረሰበት የመልካ ጉባ ድልድይ መገንባት ዘርፈ ብዙ ወታደራዊ ጠቀሜታዎች እንዳሉት በቦታው የሚገኙ የፀጥታ ተቋማት አመራሮች ተናገረዋል። የድልድዩ መሰራት ሰራዊቱ በዳዋ ወንዝ ሙላት ምክንያት ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ ግዳጅ ለመፈፀም የነበረበትን ተግዳሮት የፈታ የግንባታ ሂደት መሆኑም ተጠቅሷል። በደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ብርጌድ አዛዥ የሆኑት ኮሎኔል ብርሃነ ልጃለም እንዳሉት ከዚህ ቀደም የሸኔን ታጣቂ ሃይል ለመደምሰስ በተደረገው ዘመቻ የዳዋ ወንዝ ከፍተኛ ለተልዕኮ ችግር እንደነበር አውስተው የድልድዩ ግንባታ ፈጣን፣ ተወርዋሪና በሁሉም ቀጠናዎች ተንቀሳቅሶ ለድል የሚበቃ ሰራዊት የመገንባት አንድ አካል ተደርጎ ይወሰዳል ብለዋል። በዕዙ የሬጅመንት አዛዥ የሆኑት ሻለቃ ገበረ ጋሞ በበኩላቸው ግንባታው የሰራዊታችን ድካም በመቀነስ … [Read more...] about በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
“አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ”
መከላከያ ሰራዊታችን በውጊያ ወቅት ሀገርና ህዝብ የሰጠውን ተልዕኮ በጀግንነትና በድል ለመወጣት ሀሩር እና ብርዱ ሳይበግረው በየተራራው በየጥሻው ድንጋይ ተንተርሶ ሙቀቱን በላቡ ዝናቡን በሰውነቱ ሙቀት እየተቋቋመ ግዳጁን በድል ይወጣል። አንፃራዊ ሰላም ባለበት ደግሞ በደረሰበት ቦታ ሁሉ ህዝባዊ ሰራዊትነቱን በተግባር ያሳያል። ካለው የዕለት ጉርሱ ቀንሶ ለተቸገሩ ወገኖች ያካፍላል። በጉልበቱም በገንዘቡም ይረዳል። በምዕራብ ዕዝ በሚገኝ ክ/ጦር ሁለተኛ አባይ ሬጅመንት የሆነው እንዲህ ነው። ህፃን አማኑኤል ሽፈራው ይባላል። የ11አመት ታዳጊ ሲሆን ተወልዶ ያደገው በሰሜን ጎንደር አድዓርቃይ ወረዳ አምበራ አካባቢ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በሚባል ሰፈር ነው ። ህፃን አማኑኤል እንደሚለው እናቴ ትግራይ ለስራ እንደሄደች አልተመለሰችም። አባቴን አላውቀውም። ከአጎቴ ጋር ነበር … [Read more...] about “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ”