• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ

October 26, 2023 01:30 pm by Editor 1 Comment

በ116ኛው የሠራዊት ቀን ሲከበር ንግግር ያደረጉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ “ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበትን ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እንዲከበር ተደርጓል” በማለት ቀኑ ለምን እንደተመረጠ ይፋ አደረጉ።

ከዚህ ሌላ ፊልድ ማርሻሉ በንግግራቸው፤

ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ከጀግኖች የተረከብናትን ኢትዮጵያ እንደተከበረች እና ማንነቷ እንደተጠበቀ ለማስቀጠል ወታደራዊ ዝግጁነታችንን አሳድገንና ቁመናችንን አዘምነን ማንኛውንም ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለመፈጸም ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አሣውቀዋል።

የሠራዊቱ አባላት የተሠጣቸውን ታላቅ አደራ በድል ለመወጣት የመፈጸም ብቃታቸውን በማሣደግ በዓላማ ጽናታቸው እንዲቀጥሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አሳስበዋል፡፡

ሠራዊቱ ሀገሩን እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን በመጠበቅ ረገድ ሄላፊነቱን በብቃት እየተወጣ መሆኑን የገለፁት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ የታጠቁ ኃይሎችን እና ኢ- መደበኛ አደረጃጀቶችን ወደ ሕጋዊ መስመር ለማስገባት እየተሠራ ያለው በሱዳን የተከሰተው ችግር በኢትዮጵያም እንዳይደገም በማሰብ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡

የምድር ሃይል፣ የአየር ሃይል ፣ የባሕር ሃይል እና የሳይበር ኃይሎቻችንንም ዘመኑን እና ኢትዮጵያን በሚመጥኑ መልኩ እየገነባን የተሻለ አስተማማኝ ደረጃ ላይ ማድረስ ችለናልም ብለዋል።

የካቲት 7 ቀን 1987 ዓ.ም የሠራዊት ቀን ሆኖ እንዲከበር መወሰኑ ወገንተኝነት የፈጠረው አንዱ ታሪካዊ ስህተት መሆኑንም አንስተዋል።  

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የተሳሳተውን ውሳኔ በማሥተካከል የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሠራዊት እንደ ተቋም የተመሠረተበት ቀን ጥቅምት 15 እንዲሆን መወሠኑን ተናግረዋል። በመሆኑም “ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበትን ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እንዲከበር ተደርጓል” ብለዋል ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ።

ጥቅምት 15 ቀን 1900 ዓ.ም ዳግማዊ አጼ ምኒልክ ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲነግዴን (አባ መላን) የመጀመሪያው የጦር ሚኒስትር አድርገው የሾሙበት እና ሠራዊቱ ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆን መሠረት የጣሉበት መሆኑን የጠቆሙት ፊልድ ማርሻሉ፣ ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲነግዴ ሠራዊቱ ዘመን ተሻጋሪ ሆኖ እንዲቀረፅ በሳል አመራርነት ሰጥተዋል ብለዋል።

116ኛው የሠራዊት ቀን ለሀገራቸው በየዘመናቱ መስዋዕት የከፈሉ ጀግኖችን የምንዘክርበት ቃላችንን የምናድስበት እና ይበልጥ ለማንኛውም ተልዕኮ የምንነሳሳበት ዕለት ነው። (የመከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: 116 anniversary of endf, emiye menelik, emperor menelik, endf, father of modern ethiopian defense force, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 30, 2023 10:32 am at 10:32 am

    መቸውንም ቢሆን ያለፈ ነገርን እየናድ ሃገር መገንባት አይቻልም። ማርሻሉ አጼውን ማውሳታቸው መልካም ነገር ነው። የሃገራችን የያኔም ሆነ የአሁን ችግር የዘረኝነት በሽታ ነው። ሰው ዛሬን እንጂ ነገን አለማየት። እርግጥ ነው ወያኔና ሻቢያ የከተማ አለቆች ከሆኑ ጀምሮ ነገሮች ሁሉ ከፍተዋል። ዛሬም በትግራይ ውስጥ ወያኔ የሚሰራው ክፋት ማቆሚያ የለውም። የሚገርመው ግን አሜሪካም ከወራታት በህዋላ ዛሬም ወያኔን አይዞህ ለማለት ወደ መቀሌ መመላለሳቸው ነው። የወያኔን የፕሮፓጋንዳ ሚዲያ ላዳመጠ ሰውን ሃዘን አስቀምጦ ሌላ ጦርነት ቀስቃሽ ፕሮፓጋንዳ እንደሚነዙ በግልጽ ያሳያል። እብደታችን መቼ ይሆን የሚቆመው? በየስብሰባውና በየጎዳነው የትግራይ (ወያኔ) ባንዲራን እያውለበለቡ ሃገር ነን ማለታቸውን ዛሬም አልተውም። የሃገሬ ሰው እንደሚለው ” ሲኖሩ ልጥቅ ሲለዪ ምንጥቅ ነው” ዝም ብሎ ሲደላ ኢትዮጵያዊ ነን ሲከፋ ትግራይን ሃገር እናረጋለን እያሉ ሰውን ማወናበድ አስፈላጊ አይደለም።
    በወያኔ ጊዜ የነበረው የኢትዮጵያ ሰራዊትና አሁን ላይ ከተዋቀረው የሰራዊት አሰራርና ጥንካሬ የተለየ አይደለም የሚሉን ተጨፈኑና ላሞኛችሁ የሚሉ የፓለቲካ ስልቦች ናቸው። ለውጥ አለ። ለውጡ ግን ገና ብዙ ሥራ ይቀረዋል። ምድሪቱ በዘርና በቋንቋ የተሰመረውን የአፓርታይድ የክልል ፓለቲካ ህገ መንግስቱን በማሻሻል እስካልተቀረፈ ድረስ መገዳደላችን ይቀጥላል። አሁን በፋኖና በመከላከያ መካከል የሚደረገው ፍልሚያ ጭራሽ መሆን የማይገባው የእብደት ሥራ ነው። መቆም አለበት። የብልጽግናው መንግስትም የጊዜው የኑሮና የፓለቲካ ጫና ያስነጠሰውን ሁሉ መንግስቴን ልትንድ ነው በማለት ማስርና ማሰቃየቱን ማቆም አለበት። ለመገዳደልና ጥይት ለማጮህ የምንቸኩለውን ያህል ለሥራ ለሰላም ብንተጋ ዛሬ ሃገሪቱ የት በደረሰች። ግን በዚህች ምድር ላይ ለሚኖረን አጭር ጊዜ ስንቶችን አስለቅሰን፤ ቀምተንና አሳዝነን ሁሉም ወደማይቀርበት ዓለም እንሻገራለን። በእኔ እምነት ብሄርተኞች የቁም ጅሎች ናቸው። በሌላው ደምና እንባ የሚነግድ። እስቲ የፍልስጤሙ ሃማስ አሁዶችን በማጥቃቱ ያተረፈው ምንድን ነው? ሰቆቃና ዋይታ! በዚህ ግጭት የተነሳ ገና ብዙ ጉድ ይፈጠራል። የሱዳንን የእርስ በእርስ ጦርነት ከቅርብና ከሩቅ ሆነው ነዳጅ የሚያርከፈክፉበት አረቦችና ነጮች ስለ ሱዳን ህዝብ አይገዳቸውም። አንዲት ምላስ የምታክል ምድር ግን ስትወረር ዓለም ሁሉ አብሮ ያለቅሳል? ግን ለጥቁር ህዝብ አረቡና ነጩ አይገደው? ገጣሚው እንዳለው
    ብርሃንን ፍለጋ እልፎች ሲሯሯጡ
    ሰላም ሰላም ብለው ጦርን እየጫሩ
    ዞረው ተመልሰው አዛኝ አንጓች ሆነው
    አፍርሰው ገንብተው ደግመው እየናድ
    የኋሊት አስኬድን ቀን እየቆጠሩ
    እኛም የጅል ጅሎች አብረን እየዶለትን
    ቤታችን ፈረሰ ሰላም ሰላም እያልን።
    የአሁኑ የኢትዮጵያ መከላከያ ካለፉት ወታደራዊ ውድቀቶችና መመናመን ትምህርት ሊቀስም ይገባል። በተለይም ወያኔ በዘሩና በቋንቋው ላ ዕላይና ታህታይ መዋቅሩን ሁሉ በወታደራዊ መስኩና በኢኮኖሚውም መያዙ ከመፈንገል እንዳላስጣለው ሁሉ የብልጽግናው መንግስትም ከዚያ ውድቀት ተምሮ ኢትዪጵያ |2| የሚሸት ለሃገሩና ለወገኑ የሚዋደቅ ሰራዊት መገንባት አለበት። በሃይማኖትና በቋንቋ እንዲሁም በክልልና በብሄር የተደራጀ ሃይል መፈራረሱ አይቀሬ ነውና ከታሪክ እየተማሩ በመራመድ ነገሮችን ማሳመር ከአሁኑ የኢትዮጵያ ሰራዊት የሚጠበቅ ነው።፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule