የገጠመን ጠላት ጦርነትን እንደኦክስጅን የሚቆጥር ያለጦርነት መሽቶ የማይነጋለት ደመ-ቀዝቃዛ ኃይል ነው። በፍፁም የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ያለው ወያኔ ኢትዮጵያን ለማፍረስ፣ ቀጠናውን ለማተራመስ እረፍት የለውም፡፡ ምክንያቱም በአንድ በኩል የት*ግሬን ወጣት ሊመግበው የሚችለው በዘራፊነት አሰማርቶ ብቻ ነውና፡፡ የወያኔ ሠራዊት ዘራፊና ወሮ-በላ (pillager) ሠራዊት ነው፡፡ ወሮ-በላ ሠራዊት ደግሞ ዓይኑን ጨፍኖ ለመዝረፍ የሚመጣ ኃይል ነው፡፡ መዝረፍ፣ ማውደም፣... ግብሩ ነው። ቆቦ፣ ወልድያ፣ ሐይቅ፣ ደሴ፣ ኮምበልቻ፣ ከሚሴ፣ ሸዋሮቢት፣ ንፋስ መውጫ፣... ዐቢይ ማሳያ ሆነው ይቀርባሉ። ከሐምሌ-ታህሳስ በዘለቀ የወሎ፣ ከፊል ሸዋና ጎንደር የጦር ወረራው ከዶሮ እንቁላል እስከ ፋብሪካ ማሽነሪ፤ ከአልባሳት እስከ ቀንድ ከብት፤ ከማህበራዊ የልማት ተቋማት እስከ እርሻ … [Read more...] about የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች
endf
መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
ከመካከለኛው ምስራቅ አካባቢ የሚሰሙ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ ከትህነግ ጋር ወደ ዳግም ጦርነት ልትገባ እንደምትችል ጠቁመዋል። ትህግም ለውጊያ እየተዘጋጀሁ ነኝ ሲል ተሰምቷል። ኤርትራ ደግሞ በሩሲያ ሠራሽ ድሮኖች ራሷን አጠናክራለች። ከተለያዩ የዜና ምንጮች ለመገንዘብ እንደሚቻለው የኢትዮጵያ መካላከያ ሠራዊት አዲስ የማጥቃት ዘመቻ ሊጀምር ይችላል እየተባለ ነው። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ኢትዮጵያ አዳዲስ ድሮኖችን ጨምሮ ተጨማሪ ተዋጊ ጀቶችን ወደ አገር ቤት በዚህ ማስገባቷ ተሰምቷል። ቱርክ ሰራሹ ባይራክ 32 ድሮን እና ተጨማሪ ጀቶች ወደ አዲስ አበባ ሳይገቡ አልቀረም። ከዚህ በፊት በተለያየ ዙር ሲሰለጥኑ የኖሩና በመጀመሪያው የክተት አዋጅ፣ የተመዘገቡ ወታደሮች እስካሁን ማስልጠኛ ካምፕ ውስጥ ቆይተው ሰሞኑን ወደ ወደ ተለያየ ክልል በተለይም ወደ አማራ ክልል ገብተዋል። … [Read more...] about መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
“ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው
ሠራዊታችን እንደ አገር ሊቃጣብን የሚችልን ማንኛውም ትንኮሳና ጥቃት በብቃት መመከት በሚያስችል የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ተናገሩ። የትህነግ ቡድን ከጀሌዎቹ ጋር በማበር የከፈተውን አገር የማፍረስ እቅድ መከላከያ ሰራዊቱ በውስብስብ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ማክሸፍ መቻሉን ያስታወሱት ጀኔራል ጌታቸው ከዘመቻ በኋላ የተገኘውን አንፃራዊ ሰላም በመጠቀም ተቋሙ በሞራል፣ በሰው ሃይል፣ በብቃትና በማቴሪያል የተሟላና ግዙፍ ኃይል እንዲሆን ማድረግ ተችሏል ብለዋል። ሠራዊታችን እያንዳንዷን ሰዓት በስልጠና ላይ በማዋል መቺና ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ እንዲደርስ ማድረግ ተችሏል ያሉት ጄነራል መኮንኑ አገራችንን ለመድፈር በሚያስቡ አካላት ላይ መንግስት በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሰረት የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ … [Read more...] about “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው
“የመከላከያ ጥምር ኃይልና ህዝቡ አሸባሪውን ቡድን እንደ እግር እሳት እየፈጁት ነው”
የመከላከያ ጥምር ሀይልና ህዝቡ አሸባሪው ቡድን ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች እንደ እግር እሳት እየፈጀው እንደሚገኝ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። የፌዴራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ የሽብር ቡድኑ ለከፈተው አገርን የማፍረስ ጦርነት ለመመከት ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርካታ ቁጥር ያለው ህዝብ በከፍተኛ ቁጭትና ወኔ ወደ ግምባር እየዘመቱ ይገኛሉ ብለዋል። የመከላከያ ጥምር ሀይልና ህዝቡ አሸባሪው ቡድን ሰርጎ በገባባቸው አካባቢዎች እንደ እግር እሳት እየፈጀው እንደሚገኝም ገልጸዋል። አሸባሪው ቡድን ሰርጎ ቢገባም አይወጣም ያሉ የደሴ ወጣቶች "እንደገና" ብለው በመደራጀት አሸባሪውን እየቀጡትና አካባቢያቸውንም በንቃት እየጠበቁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። (ኢፕድ) ከዚሁ ጋር … [Read more...] about “የመከላከያ ጥምር ኃይልና ህዝቡ አሸባሪውን ቡድን እንደ እግር እሳት እየፈጁት ነው”
ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!
ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የህወሃት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷልበወሎ ዩኒቨርሲቲ ፎቶ ለመነሳት ገብቶ የነበረ የጥፋት ቡድኑ ፎቶ ናፋቂም ባለበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ እስከወዲያኛው ተሸኝቷልየደሴ ከተማና አካባቢዋን ተቆጣጥረናል በማለት ጮኸው የሚያስጮሁ የወራሪው ወሬ አራጋቢዎችም በስፍራው እየተፋለሙ የሚገኙትን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወኔና ጀግንነት አልተረዱም ልዩ መረጃ፤ ከጥቂት ደቂዎች በፊት ጎልጉል እንዳረጋገጠው ደሴን ያረጋጋው መከላከያ ሠራዊት፣ ልዩ ኃይል፣ ሕዝባዊ ሚሊሻና ፋኖ በርካታ አካባቢዎችን እየተቆጣጠረና በወገን እጅ ሥር እያደረጋቸው ይገኛል። በዚህም ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመሰሰና እየሸሸ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ላለቁት ልጆቹ ትህነግን ለመጠየቅ እንዲዘጋጅ … [Read more...] about ደሴ በወገን እጅ – መከላከያ እየገፋ ነው!
ጀብዱ ፈጻሚዎቹ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የጦር ሜዳ ፈርጦች
ጀግኖቹ በስሌት እና በቀመር የሚተኩሱት ተተኳሽ ዶግ አመድ የሚያደርገው የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት ክምር መረማመጃ ያሳጣል፡፡ በተረበሸው የጠላት ምሽግ ዙሪያ እንደ ዘንዶ የተጠመጠሙት የእናት ኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ድልን ለማጣጣም መጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል፡፡ ሴት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላትም ከወንድሞቻቸው ጋር ጠላት የገባበት ጉድጓድ ገብተው ወደ ቋመጠው ሞት በመሸኘት ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራ እና ተከብራ እንደምትኖር እያሳዩት ነው፡፡ ፈርጣማ ወታደራዊ ተክለ ቁመና እና የገዘፈ ኢትዮጵያዊ ልብ የታደሉት እነዚህ እንስቶች የሚሰጣቸውን ግዳጅ በብቃት ይፈጽማሉ፤ ቆፍጣና አዋጊዎችም ናቸው፡፡ አልመው አይስቱም፤ ሽብርተኛው ትህነግ የትኛውንም ያህል ብዛት እና ብቃት አለው ብሎ የሚያሰማራውን ወራሪ ቡድን በኮንክሪት ጭምር ተጨንቆ የገነባው ምሽግ ድረስ … [Read more...] about ጀብዱ ፈጻሚዎቹ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የጦር ሜዳ ፈርጦች
የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው
የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸው የአየር ድብደባዎች ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎች ላይ ብቻ እንደሆነና ኢላማቸውን የመቱ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ ገጽ ባወጣው መግለጫ፤ የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸውን የአየር ድብደባዎች በተመለከተ የተዛባ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በተቃራኒው ጥቃቶቹ ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎችን ብቻ ነው ብሏል። የመከላከያ ሠራዊት የሚያከውናቸው እነዚህ ሥራዎች የሽብር ድርጅቱ ከባድ የጦር መሣሪያዎችን እና ሌሎች ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን ለመሸሸግ የሚጠቀምባቸውን እና ወደ ወታደራዊ መገልገያነት የቀየራቸውን የተወሰኑ ቦታዎች ከጥቅም ውጭ ለማድረግ ያለመ ነው ሲልም አስታውቋል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው
እያፈገፈገ ያለውን ሽፍታ የሚመራው ፃድቃን ጦርነቱ “በቀናት፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ይጠናቀቃል” አለ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / ትህነግ አማጺ ሃይል መሪ የሆነው ጻድቃን ገብረትንሳይ ጦርነቱ እንደማይራዘም አመለከተ። አዲስ ተጀመረ የተባለውን ጦርነት “የቀናት ጉዳይ ነው፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል” ሲል የተናገረው ለኒውዮርክ ታይምስ ነው። የትግራይ ሕዝብ የዕድሜ ልክ ጠላት ሲሉ የጠራቸው ኢሳያስ መወገድ እንዳለባቸው ለዓለም ማህበረሰብ አስታውቋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እስካሁን ማጥቃት አለመጀመሩን፣ ነገር ግን ዝግጅቱን አጠናቆ መመሪያ እየጠበቀ መሆኑንና ማጥቃት ከጀመረ “ድረሱልኝ” የሚል ጊዜ የሚሰጥ እንዳልሆነ ከዚህ በፊት ሲነገር ነበር። ትህነግ ያወጣውን የድረሱልኝ ጥሪ ተከትሎ መከላከያ ይህንን ቢልም የተለያዩ ሃላፊዎችና ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዎች ደጋግመው ጥቃት መጀመሩን እያስታወቁ ነው። የአየር ሃይል አዛዥም በባንዲራ ቀን አየር ኃይል “ጠላትን … [Read more...] about እያፈገፈገ ያለውን ሽፍታ የሚመራው ፃድቃን ጦርነቱ “በቀናት፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ይጠናቀቃል” አለ
ከልጅ እጅ ጠብቀው፥ ከሚያገኙት ቀንሰው ለወገን ጦር ድጋፍ የቸሩ እናት
ወ/ሮ ውዴ በለጠ ይባላሉ። ነዋሪነታቸው ጎንደር ከተማ ቀበሌ 17 ነው። ሀገሬ በችግር ውስጥ ሆና እኔ በድሎት አልኖርም በማለት ልጆቻቸው ለቀለብ ብለው ከሚሰጧቸው ጥቂት ገንዘብ እየቆጠቡ ለሰራዊት አባላት በግላቸው ስንቅ አዘጋጅተው አቅርበዋል። ወ/ሮ ውዴ የልጆቻቸውን እጅ ጠብቀው የሚኖሩ እናት ቢሆኑም ለህልውና ዘመቻ የሀገርን ክብርና የወገንን ህልውና ለማስጠበቅ ግንባር ለተሰለፉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የአማራ ልዩ ሀይል፣ ሚሊሻና ፋኖ ይሁንልኝ ሲሉ 3 ኩንታል በሶ አዘጋጅተው ድጋፍ አበርክተዋል። ግለሰቧ “ከዚህ በፊትም ልጆቼ በቻሉት አቅም ግንባር ለዘመቱ ወገኖቻቸው ድጋፍ አድርገዋል” ይላሉ። “አሁን ደግሞ የኔ ተራ ነው፤ ከወር ቀለቤ እየቀነስኩ በሰበሰብኳትና ልጆቼ በሰጡኝ ጥቂት ገንዘብ ይህንን አድርጌያለሁ” አሉ። እኔ በሰላም ወጥቼ እንዲገባ እነሱ ህይወታቸውን … [Read more...] about ከልጅ እጅ ጠብቀው፥ ከሚያገኙት ቀንሰው ለወገን ጦር ድጋፍ የቸሩ እናት
ባለፉት 100 ዓመታት ያልተገነባ ሠራዊት ለመገንባት እየሠራን ነው – ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የ2014 ዓ.ም አዲስ ዓመትን ከሠራዊቱ ጋር ለማክበር ማይጠብሪ ግንባር ተገኝተዋል። በማይጠብሪ ግንባር ከሠራዊቱ ጋር በዓልን ለማክበር የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ፣ ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሌትናል ጄኔራል አበባው ታደሰ፣ የመከላከያ ኅብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሜጄር ጄኔራል ዘውዱ በላይ፣ የምእራብ እዝ እና የማይጠብሪ ግንባር አዛዥ ሜጄር ጄኔራል መሠለ መሠረት ጨምሮ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተገኝተዋል። የሠራዊት አባላት ተልዕኳቸን በላቀ ብቃት በመወጣት በአዲሱ ዓመት በሀገራችን አስተማማኝ ሠላም እናሰፍናለን ብለዋል። ሕዝባችን ያሳየንን ከፍተኛ ድጋፍ የሞራል ስንቅ አድርገን በአዲሱ ዓመት ለሕዝባችን ታላላቅ የድል ብሥራቶችን ለማሰማት እንዘጋጅ … [Read more...] about ባለፉት 100 ዓመታት ያልተገነባ ሠራዊት ለመገንባት እየሠራን ነው – ጠ/ሚ/ር ዐቢይ