• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች

May 19, 2022 09:37 am by Editor Leave a Comment

የገጠመን ጠላት ጦርነትን እንደኦክስጅን የሚቆጥር ያለጦርነት መሽቶ የማይነጋለት ደመ-ቀዝቃዛ ኃይል ነው። በፍፁም የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ያለው ወያኔ ኢትዮጵያን ለማፍረስ፣ ቀጠናውን ለማተራመስ እረፍት የለውም፡፡ ምክንያቱም በአንድ በኩል የት*ግሬን ወጣት ሊመግበው የሚችለው በዘራፊነት አሰማርቶ ብቻ ነውና፡፡

የወያኔ ሠራዊት ዘራፊና ወሮ-በላ (pillager) ሠራዊት ነው፡፡ ወሮ-በላ ሠራዊት ደግሞ ዓይኑን ጨፍኖ ለመዝረፍ የሚመጣ ኃይል ነው፡፡ መዝረፍ፣ ማውደም፣… ግብሩ ነው። ቆቦ፣ ወልድያ፣ ሐይቅ፣ ደሴ፣ ኮምበልቻ፣ ከሚሴ፣ ሸዋሮቢት፣ ንፋስ መውጫ፣… ዐቢይ ማሳያ ሆነው ይቀርባሉ።

ከሐምሌ-ታህሳስ በዘለቀ የወሎ፣ ከፊል ሸዋና ጎንደር የጦር ወረራው ከዶሮ እንቁላል እስከ ፋብሪካ ማሽነሪ፤ ከአልባሳት እስከ ቀንድ ከብት፤ ከማህበራዊ የልማት ተቋማት እስከ እርሻ ሰብል፤…ድረስ ያለውን ንብረት የቻለውን ዘርፎ ያልሆነለትን አውድሞ መሸሸቱ ይታወሳል። በብዙዎቹ ቦታዎች ከባድ ምት ደርሶበት ከመሸሹ በፊት ‘scorched earth policy’ ተግብሯል።

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰራዊት ባልገነባችባቸው በጥንት ዘመን እንኳ አሁን ካለው የወያኔ ወርሮ-በላ ሠራዊት በላይ ክፉ ጠላት ያጋጠማት አይመስልም። ከቋንቋ ተናጋሪነት ውጭ ከድርቡሽ የሚለይበት ነገር የለውም።

ሌላኛው እውነታ፣ ወያኔ የሚከተለው የጦርነት ስትራቴጂ መትረፍን እንደ ዓይነተኛ ዓላማ የያዘ መሆኑ ላይ ነው፡፡ የፖለቲካም ሆነ የውጊያ ሁለ-ነገሩ ‘Survival as a Strategy’ ነው። ለወያኔ በሕይወት ለመኖር መዋጋት መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ወያኔነት በራሱ አስተሳሰብ ስለመሆኑ ነው። የአስተሳሰቡ ተሸካሚ የሆነ (ማህበራዊ መሰረቱ) ወሮ-በላነት የማንነቱ መገለጫ ሆኗል።

እነዚህን መሠረታዊ እውነታዎች ታሳቢ አድርገን ስንመለከተው፣ “ወያኔ ሰላም ይፈልጋል” ማለት ከፍ ሲል ተራ ቅዠት፤ ዝቅ ሲል ቅጥፈት ነው፡፡

ባለፈው ክረምት በነበረው ውጊያ 350,000 በላይ የትግሬ ወጣት ወደቤቱ አልተመለሰም። እዚያው ትግራይ ውስጥ በስኳር፣ ደም ግፊትና በምግብ እጥረት የረገፈውን ስንደምረው በዚህ ጦርነት 400,000 ገብሮበታል። ይህም ሆኖ ሰላም አይናፍቀውም፣ ዛሬም አውዳሚ ጦርነትን ያልማል።

በአጭሩ ወያኔ፦

  • የሰው ሕይወት በጅቶ የሚዋጋ የዘመናችን በላዔሰብ መሆኑን፤
  • ጦርነት ካቆመ ሕይወት እንደማይኖረው፤
  • ሁልጊዜም በጦርነት ውስጥ መኖር ለዚህ ድርጅት ህልውና ወሳኝ ኦክስጂን መሆኑን፤ … መረዳት
    ይገባል፡፡

ስለሆነም ከፊትለፊታችን የዋንጫ ጦርነት ነው የሚጠብቀን። ይልቁንስ ወንድም ጓንጉል የአርማጭሆው እንዳለው የአሁኑ ጦርነት ወያኔንና አስተሳሰቡን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከኢትዮጵያ ምድር ነቅሎ ለመጣል መሆን አለበት!!

አንድ መታወቅ ያለበት መሰረታዊ እውነታ የዋንጫው ጦርነት የአካባቢውን ሀገራት የግዛት ሁኔታና የሕዝቦችን ሥነ-ልቦናዊ ስሪት የሚቀይር ስለመሆኑ ነው።

እጅግ በተለየ ቀጣና ውስጥ ነው የምንኖረው፣ የቅኝ-ግዛት ድንበሮችን የማይቀበል፣ በሁሉም ተጎራባች አገራት መካከል የድንበር ውዝግብ ያለበት፣ በአለቃ አልባው የዘመናችን የዓለም ሥርዓት ውስጥ የጥላቻ ተፎካካሪዎች (Bitter Rivals) እጃቸውን ያስረዘሙበት አካባቢ ነው።

በዘመናዊው የአፍሪካ ታሪክ ረዥሙ ጦርነት የተካሄደው እዚሁ ቀጣና ብቻ ሳይሆን እኛ ሀገር ላይ ነው። ከቀጠናው ባህሪ አኳያ ነገሮችን ብንመለከት እንኳ የወያኔ መነቀል የሰላም ትሩፋቱ በተዋረድ ታንዛኒያና ኮንጎ ይደርሳል። ይቅርና ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት።

በዚህ ጦርነት እንደአፋር ያሉ ድንበር ተሻጋሪ ማንነት ያላቸው ማኀበረሰቦች ሚና በቀላሉ አይታይም። ጉዳዩ የማዕከላዊ መንግሥት መጠናከርና መዳከም ጉዳይ አይደለም ከዛም የሚሻገር ነው። ስለሆነም ወያኔን መቅበር የምርጫ ጉዳይ አይደለም። ምርጫ የለንም!

እናማ በዚህ ጦርነት ጠላት ኦንደፍልፈል እየገፋ ባለበት ሁኔታ “የሰላም ሰባኪ ነኝ” የሚለውን ጭምብላም በማይካድራ፣ በጭና፣ በቆቦ፣ በአጋምሳ፣ በንፋስ መውጫ፣… ሰማዕታት ስም ምህረት ንፈገው። የእነ እሸቴ ሞገስ አደራ አለብኝ በለው።

በመጨረሻም በዚህ ጦርነት የተለመደው አይነት የማጥቃት ስልቶች ይመጣሉ።

የማያቋርጥ የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት፣ የሳይበር ጦርነቱን በሐሳብ የበላይነት የሚመሩ ግለሰቦችን አካውንት ማዘጋት፣ በማህበራዊ ሚዲያ የተመረጡ ግለሰቦችን ስም ማጥፋት፣ የደቦ ፍርድ ቅስቀሳ፣ … ወዘተ የሚጠበቁ ቀውሶች ናቸው። ያለምህረት መታገል የኛ ኃላፊነት ነው።

በተረፈ አካይስትና መሸጦውን ንቀህ ተወው አልልህም፤ ጀርባህን ለምታምነው ብቻ ሰጥተህ ግን ተዋጋ!! (ሙሉዓለም ገብረመድኅን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions, Politics Tagged With: endf, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule