• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች

May 19, 2022 09:37 am by Editor Leave a Comment

የገጠመን ጠላት ጦርነትን እንደኦክስጅን የሚቆጥር ያለጦርነት መሽቶ የማይነጋለት ደመ-ቀዝቃዛ ኃይል ነው። በፍፁም የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ያለው ወያኔ ኢትዮጵያን ለማፍረስ፣ ቀጠናውን ለማተራመስ እረፍት የለውም፡፡ ምክንያቱም በአንድ በኩል የት*ግሬን ወጣት ሊመግበው የሚችለው በዘራፊነት አሰማርቶ ብቻ ነውና፡፡

የወያኔ ሠራዊት ዘራፊና ወሮ-በላ (pillager) ሠራዊት ነው፡፡ ወሮ-በላ ሠራዊት ደግሞ ዓይኑን ጨፍኖ ለመዝረፍ የሚመጣ ኃይል ነው፡፡ መዝረፍ፣ ማውደም፣… ግብሩ ነው። ቆቦ፣ ወልድያ፣ ሐይቅ፣ ደሴ፣ ኮምበልቻ፣ ከሚሴ፣ ሸዋሮቢት፣ ንፋስ መውጫ፣… ዐቢይ ማሳያ ሆነው ይቀርባሉ።

ከሐምሌ-ታህሳስ በዘለቀ የወሎ፣ ከፊል ሸዋና ጎንደር የጦር ወረራው ከዶሮ እንቁላል እስከ ፋብሪካ ማሽነሪ፤ ከአልባሳት እስከ ቀንድ ከብት፤ ከማህበራዊ የልማት ተቋማት እስከ እርሻ ሰብል፤…ድረስ ያለውን ንብረት የቻለውን ዘርፎ ያልሆነለትን አውድሞ መሸሸቱ ይታወሳል። በብዙዎቹ ቦታዎች ከባድ ምት ደርሶበት ከመሸሹ በፊት ‘scorched earth policy’ ተግብሯል።

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰራዊት ባልገነባችባቸው በጥንት ዘመን እንኳ አሁን ካለው የወያኔ ወርሮ-በላ ሠራዊት በላይ ክፉ ጠላት ያጋጠማት አይመስልም። ከቋንቋ ተናጋሪነት ውጭ ከድርቡሽ የሚለይበት ነገር የለውም።

ሌላኛው እውነታ፣ ወያኔ የሚከተለው የጦርነት ስትራቴጂ መትረፍን እንደ ዓይነተኛ ዓላማ የያዘ መሆኑ ላይ ነው፡፡ የፖለቲካም ሆነ የውጊያ ሁለ-ነገሩ ‘Survival as a Strategy’ ነው። ለወያኔ በሕይወት ለመኖር መዋጋት መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ወያኔነት በራሱ አስተሳሰብ ስለመሆኑ ነው። የአስተሳሰቡ ተሸካሚ የሆነ (ማህበራዊ መሰረቱ) ወሮ-በላነት የማንነቱ መገለጫ ሆኗል።

እነዚህን መሠረታዊ እውነታዎች ታሳቢ አድርገን ስንመለከተው፣ “ወያኔ ሰላም ይፈልጋል” ማለት ከፍ ሲል ተራ ቅዠት፤ ዝቅ ሲል ቅጥፈት ነው፡፡

ባለፈው ክረምት በነበረው ውጊያ 350,000 በላይ የትግሬ ወጣት ወደቤቱ አልተመለሰም። እዚያው ትግራይ ውስጥ በስኳር፣ ደም ግፊትና በምግብ እጥረት የረገፈውን ስንደምረው በዚህ ጦርነት 400,000 ገብሮበታል። ይህም ሆኖ ሰላም አይናፍቀውም፣ ዛሬም አውዳሚ ጦርነትን ያልማል።

በአጭሩ ወያኔ፦

  • የሰው ሕይወት በጅቶ የሚዋጋ የዘመናችን በላዔሰብ መሆኑን፤
  • ጦርነት ካቆመ ሕይወት እንደማይኖረው፤
  • ሁልጊዜም በጦርነት ውስጥ መኖር ለዚህ ድርጅት ህልውና ወሳኝ ኦክስጂን መሆኑን፤ … መረዳት
    ይገባል፡፡

ስለሆነም ከፊትለፊታችን የዋንጫ ጦርነት ነው የሚጠብቀን። ይልቁንስ ወንድም ጓንጉል የአርማጭሆው እንዳለው የአሁኑ ጦርነት ወያኔንና አስተሳሰቡን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከኢትዮጵያ ምድር ነቅሎ ለመጣል መሆን አለበት!!

አንድ መታወቅ ያለበት መሰረታዊ እውነታ የዋንጫው ጦርነት የአካባቢውን ሀገራት የግዛት ሁኔታና የሕዝቦችን ሥነ-ልቦናዊ ስሪት የሚቀይር ስለመሆኑ ነው።

እጅግ በተለየ ቀጣና ውስጥ ነው የምንኖረው፣ የቅኝ-ግዛት ድንበሮችን የማይቀበል፣ በሁሉም ተጎራባች አገራት መካከል የድንበር ውዝግብ ያለበት፣ በአለቃ አልባው የዘመናችን የዓለም ሥርዓት ውስጥ የጥላቻ ተፎካካሪዎች (Bitter Rivals) እጃቸውን ያስረዘሙበት አካባቢ ነው።

በዘመናዊው የአፍሪካ ታሪክ ረዥሙ ጦርነት የተካሄደው እዚሁ ቀጣና ብቻ ሳይሆን እኛ ሀገር ላይ ነው። ከቀጠናው ባህሪ አኳያ ነገሮችን ብንመለከት እንኳ የወያኔ መነቀል የሰላም ትሩፋቱ በተዋረድ ታንዛኒያና ኮንጎ ይደርሳል። ይቅርና ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት።

በዚህ ጦርነት እንደአፋር ያሉ ድንበር ተሻጋሪ ማንነት ያላቸው ማኀበረሰቦች ሚና በቀላሉ አይታይም። ጉዳዩ የማዕከላዊ መንግሥት መጠናከርና መዳከም ጉዳይ አይደለም ከዛም የሚሻገር ነው። ስለሆነም ወያኔን መቅበር የምርጫ ጉዳይ አይደለም። ምርጫ የለንም!

እናማ በዚህ ጦርነት ጠላት ኦንደፍልፈል እየገፋ ባለበት ሁኔታ “የሰላም ሰባኪ ነኝ” የሚለውን ጭምብላም በማይካድራ፣ በጭና፣ በቆቦ፣ በአጋምሳ፣ በንፋስ መውጫ፣… ሰማዕታት ስም ምህረት ንፈገው። የእነ እሸቴ ሞገስ አደራ አለብኝ በለው።

በመጨረሻም በዚህ ጦርነት የተለመደው አይነት የማጥቃት ስልቶች ይመጣሉ።

የማያቋርጥ የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት፣ የሳይበር ጦርነቱን በሐሳብ የበላይነት የሚመሩ ግለሰቦችን አካውንት ማዘጋት፣ በማህበራዊ ሚዲያ የተመረጡ ግለሰቦችን ስም ማጥፋት፣ የደቦ ፍርድ ቅስቀሳ፣ … ወዘተ የሚጠበቁ ቀውሶች ናቸው። ያለምህረት መታገል የኛ ኃላፊነት ነው።

በተረፈ አካይስትና መሸጦውን ንቀህ ተወው አልልህም፤ ጀርባህን ለምታምነው ብቻ ሰጥተህ ግን ተዋጋ!! (ሙሉዓለም ገብረመድኅን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions, Politics Tagged With: endf, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule