የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ለ69ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን “የጥቁር አንበሳ” ዕጩ መኮንኖችን አስመረቀ። ተመራቂዎቹ “የጥቁር አንበሳ” መባላቸው በምዕራባዊያንና በውስጡ ነበሩ በተባሉ “ካሃዲዎች” የተበተነውን ታላቁን የኢትዮጵያ መከላከያ ያስታወሰ መሆኑ ልዩ ስሜት የሚሰጥ እንደሆነ ምርቃቱን ተከትሎ አስተያየት ተሰጥቷል። “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም በሚል ቁጭት ነው ኢትዮጵያን የሚመጥን የመከላከያ ኃይል ለመገንባት እየሠራን ያለነው” በማለት የጦር ኃይሎች ም/ጠ/ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ በተናገሩ ማግስት፣ አዳዲስ መኮኖች መመረቃቸው፣ ጀነራሉ በንግግራቸው የሚገነባው ኢትዮጵያን የሚመስልና የሚመጥን ሰራዊት ዘመናዊና ቴክኖሎጂን የተላበሰ፣ በምሁራን የተገነባ እንደሚሆን ካመላከቱት ጋር ተያያዥ ሆኗል። ተመራቂዎቹ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው፣ በራሳቸው ተነሳሽነት ከሲቪል … [Read more...] about የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ