• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ

May 29, 2022 04:01 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ለ69ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን “የጥቁር አንበሳ” ዕጩ መኮንኖችን አስመረቀ። ተመራቂዎቹ “የጥቁር አንበሳ” መባላቸው በምዕራባዊያንና በውስጡ ነበሩ በተባሉ “ካሃዲዎች” የተበተነውን ታላቁን የኢትዮጵያ መከላከያ ያስታወሰ መሆኑ ልዩ ስሜት የሚሰጥ እንደሆነ ምርቃቱን ተከትሎ አስተያየት ተሰጥቷል።

“ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም በሚል ቁጭት ነው ኢትዮጵያን የሚመጥን የመከላከያ ኃይል ለመገንባት እየሠራን ያለነው” በማለት የጦር ኃይሎች ም/ጠ/ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ በተናገሩ ማግስት፣ አዳዲስ መኮኖች መመረቃቸው፣ ጀነራሉ በንግግራቸው የሚገነባው ኢትዮጵያን የሚመስልና የሚመጥን ሰራዊት ዘመናዊና ቴክኖሎጂን የተላበሰ፣ በምሁራን የተገነባ እንደሚሆን ካመላከቱት ጋር ተያያዥ ሆኗል። ተመራቂዎቹ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው፣ በራሳቸው ተነሳሽነት ከሲቪል የስራ መስካቸው ወደ ውትድርና ያመሩ ተተኪ መኮንኖች መሆናቸው ታውቋል።

የሀገር መከላከያ ሰራዊት መኮንኖች ኢትዮጵያዊ ጀግንነት፣ ከሀገር ፍቅርና ከሕገመንግሥቱ የሚቀዳ ዓላማና ሁለገብ ዕውቀት ሊኖራቸው እንደሚገባ የጠቀሱት ደግሞ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ ናቸው። ይህንንም ያሉት በምረቃው ሥነሥርዓት ላይ ነው።

በተከታታይ በወታደራዊ ሳይንስና ትምህርት የሰለጠኑ፣ በሜካናይዝድና ኢንተለጀንስ የተሠሩ አዳዲስና ወጣት ሙያተኞችን እያካተተ ያለው የመከላከያ ሠራዊት ውጊያን በትንሽ ኪሣራ፣ በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ እንዲችል ተደርጎ እየተሠራ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲገልጽ እንደነበር ይታወሳል።

በ1983 የኢትዮጵያ መከላከያ “የደርግ ሠራዊት” ተብሎ እንደተበተነው ሁሉ በቅርቡ ትህነግ አማራና አፋር ክልልን ወሮ በነበረበት ወቅት “እጃችሁን ለትግራይ ኃይልን ስጡ” በሚል ጥሪ ሲቀርብለት የነበረና ወረራውን በአጭር ጊዜ ራሱን አደራጅቶ የቀለበሰና ልምድ ያካበተ እንደሆነ ከፍተኛ መኮንኖች ሲያስታውቁ ቆይተዋል። በወቅቱ የትህነግ አመራሮች ይህ በአዲስ እየተደራጀ ያለውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት “የዐቢይ ሠራዊት” በማለት ዳግም እንደሚያፈርሱት ሲዝቱ እንደነበር ይታወሳል።

የምረቃውን ሥነ ሥርዓት አስመልክቶ በታተሙ ምስሎች ለመረዳት እንደተቻለው የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አዛዥ የነበሩትና የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ጀግና አንደኛ ደረጃ ኒሻን የተሸለሙት ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያምና ሌሎች ዕውቅ የቀድሞ ባለኮከብ መኮንኖች በሥነሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።

ዛሬ የመንግሥት መገናኛዎች እንዳሉት የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ 69ኛ ዙር የጥቁር አንበሳ ኮርስ የሲቪል ወታደራዊ መኮንኖችን በምክትል መቶ አለቃ ማዕረግ ዛሬ አስመርቋል። በመርሀ ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ፣ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ተገኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልእክት የሀገር መከላከያ ሠራዊት መኮንኖች ኢትዮጵያዊ ጀግንነት፣ ከሀገር ፍቅርና ከሕገመንግሥቱ የሚቀዳ ዓላማና ሁለገብ ዕውቀት ሊኖራችሁ ይገባል ብለዋል።

የነገ የሀገር ኩራት ጄኔራሎችና ሀገር መሪዎች መሆናችሁን በቅጡ በመረዳት ለዓላማችሁ የምትታትሩ፣የምትተጉና ከቀድሞ የጦር መሪዎች ተምራችሁ የምትሠሩና የምታሠሩ መሆን ይጠበቅባችኋል ሲሉ አሳስበዋል።

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ብርሀኑ ጁላ፤ የዛሬ ተመራቂዎች የተሰጣቸውን ሥልጠና በብቃት በመወጣት የመከላከያ ሠራዊት አባል መሆን የቻሉ መኮንኖች መሆናቸውን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ችግር ውስጥ በገባችበት ወቅት ሀገራቸውን አስቀድመው በአስቸጋሪና ውስብስብ ስልጠና ተፈትነው ያለፉና ለምረቃ የበቁ መኮንኖች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

የ69ኛ ተመራቂ መኮንኖች አብዛኞቹ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩበት ሥራቸውን አቁመው በራሳቸው ተነሳሽነት እናት ሀገር ጥሪን ተቀብለው ሠራዊቱን የተቀላቀሉ ናቸው። (ኢትዮ 12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: black lion army, endf, ethiopian military academy, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule