• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች”

May 26, 2022 08:19 am by Editor 1 Comment

በሙያቸው ብቃት እና በስነ ምግባራቸው በሠራዊታችንም ሆነ በሰቪል ማህበረሰቡ ዘንድ ተመስግነው የማያልፍ ታሪክን ሰርተው ህዝብና ሀገርን አኩርተዋል።

በዋሉበት አውድ ሁሉ በፅናትና በጀግንነት ከጦር ሠራዊቱ ጋር ፊት ለፊት በመሰለፍ ሠራዊቱን አክመዋል ባስ ሲል ደግሞ ጠመንጃቸውን አንስተው ጠላትን እያፍረከረኩ ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ድርብ ኃላፊነት በጀግንነት ተወጥተዋል።

ሰራዊቱ ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር በሚል ቁልፍ እሴት በተግባር ተቃኝቶ በህዝብና በሀገር የመጣን ጠላት ሲፋለም መተከያ የሌላትን ህይወት ለመታደግ እና ከደረሠበት ጉዳት ድኖ ወደ ግንባር እንዲመለስ በማድረግ ጀብዱ ፈፅመዋል ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ዶክተሮች።

ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው እና ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ ይባላሉ።

ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ናቸው። ከህግ ማስከበር እስከ ዘመቻ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት ድረስ ሠራዊቱን እና በአካባቢው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንዴት አገልግሎት ሲሰጡ እንደነበረ ይናገራሉ።

አሸባሪው የህውሃት ቡድን በሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ ጥቃት ባደረሰ ማግስት የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አባላት ከወትሮ በተለየ መልኩ ዘመቻውን ለመደገፍ የሚያስችል አደረጃጀት አድርገን ወደ ግንባር አቅንተናል።

ሠራዊታችን እለት ከእለት ድልን እያስመዘገበ እና የጠላትን ሃይል አከርካሪውን እየሰባበረ ወደ ፊት በሚገሰግስበት ጊዜም ተንቀሳቃሽ ሆስፒታሉ በፍጥነት ከሰራዊቱ ጋር በመንቀሳቀስ የሚጠበቅበትን የጦር ሜዳ አገልግሎት ሠጥቷል።

ተዋጊው ሃይላችን ከተማዎችን እየተቆጣጠረ ወደ ፊት ሲገሰግስ በከተማዎቹ ይኖሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ በማድረግ ህይወታቸውን መታደግ ችለናል። በዚህም ከራስ በፊት ለህዝብ እና ለሀገር የሚለውን ዕሴታችን በተግባር ማሳየት ችለናል።

በማይጠብሪ ግንባር እና በወሎ ግንባር ስንገባም እንደተለመደው ለሠራዊቱ የህክምና አገልግሎት በመስጠት የማድረግ አቅሙን፣ ሞራሉ እና ወታደራዊ ስነ ልቦናው እንዲጠበቅ በማድረግ ሠራዊቱ ወደ ግንባር ተመልሶ ጠላትን እንዲደመስስ ማድረግ ችለናል።

የተለያዩ ከመንግስትና ከሲቪል የህክምና ተቋማት የመጡ ባለሙያዎችም ከእኛ ጋር በግንባር በመሰለፍ ሠራዊቱን በሙያቸው አገልግለዋል። ከልጆቹ እና ከእለት ጉርሱ ቀንሶ ለእኛ ያካፈለን ደጀን ለሆነን ህዝባችን እና በሙያቸው ላገለገሉን የጤና ሙያተኞች ምስጋና አቅርቧል።

ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ በምዕራብ ዕዝ በተዘጋጀው የሜዳይ ሽልማት ላይ የሁለተኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ በመሆኑ ደስታኛ ነው። ሽልማቱ ቀጣይ ለሚጠብቀው ግዳጅ ሞራል እና ተነሳሽነትን እንደፈጠረለትም ገልጿል።

ሌላኛው የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አባል ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው፥ ውትድርና ብዙ የሙያ መስኮች የሚገኙበት እና በሀገራችን ህዝቦች ዘንድ ደግሞ ተወዳጅ የሆነ የሙያ ዘርፍ መሆኑን በመግለፅ ተቋሙ ባስተማረው እና ባበቃው የዶክተርነት ሙያ አሸባሪው የህውሃት ቡድን በሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ ጥቃት ባደረሰበት ጊዜ ከባልደረቦቼ ጋር በመሆን ሠራዊታችንን በሙያችን በማገልገል የድል ባለቤት እንዲሆን የበኩላችንን ድርሻ መወጣት ችለናል።

ጀግናው ሠራዊታችን የሚያደርገውን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ በመከታተል እና ምሽግ ድረስ በመጓዝ ጤንነቱ የተጠበቀ እና የማድረግ አቅሙ የላቀ እንዲሆን የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አሁንም ያልተቆራረጠ ክትትል እያደረገ ይገኛል።

ዕዛችን በተንቀሳቀሰበት የግዳጅ ቀጣናዎች ሁሉ ሠራዊቱ ጉዳት ደርሶበታ ሲመጣ ተኝቶ እንዲታከም በማድረግ እና በፍጥነት አገግሞ ወደ ግዳጁ እንዲመለስ ያደረጉ የግል እና የመንግስት ሆስፒታሎችን ከልብ ማመስገን እወዳለሁ ሲሉ ተናግረዋል።

ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው በነበራቸው የላቀ ግዳጅ አፈፃፀም ከሻለቃ ማዕረግ ወደ ሌ/ኮ ማዕረግ ከፍ እንዲሉ ተደርጓል።

ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ዶክተሮች ቀናቶችን በተጋድሎና በጀብዶቻቸው እያደመቁ በፈታኝ እና ውስብስብ ግዳጆች ሳይበገሩ በሌላ ተልዕኮ ሌላ ገድል ለመፈፀም እራሳቸውን አዘጋጅተዋል። (ዘገባና ፎቶ ፍፁም ከተማ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    May 26, 2022 12:35 pm at 12:35 pm

    ሁሉም በተሰጠው ሙያና ሃላፊነት በፅናት ከሰራ ብሔራዊ ግዴታውን ስለተወጣ ከጀግኖችና በመልካም ታሪክ ይመዘገባል።
    ከሌቦች ኮሌጅ ተመርቀው እንደ አይጥ እየተዟዟሩ የሕዝብ ሓብት ሲዘርፉ የነበሩ ግን ሌቦች በሚል ታሪክ ስማቸው ይመዘገባል። ኢትዮጵያ የተለያዩ ልጆች ወልዳለች በጀግንነት የሚሞቱላት፣ በንቃት የሚጠብቋትና የሚንከባከብዋት፣በደር ቁጭ ብለው የሚመለከትዋትና ኣሰልፈው ለጠላት የሚሰጥዋት ናቸው።
    አገር ወይሞ ሞት የተባለበት ዘመን ነበር። ዛሬ ግን ብር ወይም ሞት ሆኖኣል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule