• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች”

May 26, 2022 08:19 am by Editor 1 Comment

በሙያቸው ብቃት እና በስነ ምግባራቸው በሠራዊታችንም ሆነ በሰቪል ማህበረሰቡ ዘንድ ተመስግነው የማያልፍ ታሪክን ሰርተው ህዝብና ሀገርን አኩርተዋል።

በዋሉበት አውድ ሁሉ በፅናትና በጀግንነት ከጦር ሠራዊቱ ጋር ፊት ለፊት በመሰለፍ ሠራዊቱን አክመዋል ባስ ሲል ደግሞ ጠመንጃቸውን አንስተው ጠላትን እያፍረከረኩ ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ድርብ ኃላፊነት በጀግንነት ተወጥተዋል።

ሰራዊቱ ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር በሚል ቁልፍ እሴት በተግባር ተቃኝቶ በህዝብና በሀገር የመጣን ጠላት ሲፋለም መተከያ የሌላትን ህይወት ለመታደግ እና ከደረሠበት ጉዳት ድኖ ወደ ግንባር እንዲመለስ በማድረግ ጀብዱ ፈፅመዋል ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ዶክተሮች።

ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው እና ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ ይባላሉ።

ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ናቸው። ከህግ ማስከበር እስከ ዘመቻ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት ድረስ ሠራዊቱን እና በአካባቢው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንዴት አገልግሎት ሲሰጡ እንደነበረ ይናገራሉ።

አሸባሪው የህውሃት ቡድን በሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ ጥቃት ባደረሰ ማግስት የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አባላት ከወትሮ በተለየ መልኩ ዘመቻውን ለመደገፍ የሚያስችል አደረጃጀት አድርገን ወደ ግንባር አቅንተናል።

ሠራዊታችን እለት ከእለት ድልን እያስመዘገበ እና የጠላትን ሃይል አከርካሪውን እየሰባበረ ወደ ፊት በሚገሰግስበት ጊዜም ተንቀሳቃሽ ሆስፒታሉ በፍጥነት ከሰራዊቱ ጋር በመንቀሳቀስ የሚጠበቅበትን የጦር ሜዳ አገልግሎት ሠጥቷል።

ተዋጊው ሃይላችን ከተማዎችን እየተቆጣጠረ ወደ ፊት ሲገሰግስ በከተማዎቹ ይኖሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ በማድረግ ህይወታቸውን መታደግ ችለናል። በዚህም ከራስ በፊት ለህዝብ እና ለሀገር የሚለውን ዕሴታችን በተግባር ማሳየት ችለናል።

በማይጠብሪ ግንባር እና በወሎ ግንባር ስንገባም እንደተለመደው ለሠራዊቱ የህክምና አገልግሎት በመስጠት የማድረግ አቅሙን፣ ሞራሉ እና ወታደራዊ ስነ ልቦናው እንዲጠበቅ በማድረግ ሠራዊቱ ወደ ግንባር ተመልሶ ጠላትን እንዲደመስስ ማድረግ ችለናል።

የተለያዩ ከመንግስትና ከሲቪል የህክምና ተቋማት የመጡ ባለሙያዎችም ከእኛ ጋር በግንባር በመሰለፍ ሠራዊቱን በሙያቸው አገልግለዋል። ከልጆቹ እና ከእለት ጉርሱ ቀንሶ ለእኛ ያካፈለን ደጀን ለሆነን ህዝባችን እና በሙያቸው ላገለገሉን የጤና ሙያተኞች ምስጋና አቅርቧል።

ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ በምዕራብ ዕዝ በተዘጋጀው የሜዳይ ሽልማት ላይ የሁለተኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ በመሆኑ ደስታኛ ነው። ሽልማቱ ቀጣይ ለሚጠብቀው ግዳጅ ሞራል እና ተነሳሽነትን እንደፈጠረለትም ገልጿል።

ሌላኛው የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አባል ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው፥ ውትድርና ብዙ የሙያ መስኮች የሚገኙበት እና በሀገራችን ህዝቦች ዘንድ ደግሞ ተወዳጅ የሆነ የሙያ ዘርፍ መሆኑን በመግለፅ ተቋሙ ባስተማረው እና ባበቃው የዶክተርነት ሙያ አሸባሪው የህውሃት ቡድን በሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ ጥቃት ባደረሰበት ጊዜ ከባልደረቦቼ ጋር በመሆን ሠራዊታችንን በሙያችን በማገልገል የድል ባለቤት እንዲሆን የበኩላችንን ድርሻ መወጣት ችለናል።

ጀግናው ሠራዊታችን የሚያደርገውን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ በመከታተል እና ምሽግ ድረስ በመጓዝ ጤንነቱ የተጠበቀ እና የማድረግ አቅሙ የላቀ እንዲሆን የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አሁንም ያልተቆራረጠ ክትትል እያደረገ ይገኛል።

ዕዛችን በተንቀሳቀሰበት የግዳጅ ቀጣናዎች ሁሉ ሠራዊቱ ጉዳት ደርሶበታ ሲመጣ ተኝቶ እንዲታከም በማድረግ እና በፍጥነት አገግሞ ወደ ግዳጁ እንዲመለስ ያደረጉ የግል እና የመንግስት ሆስፒታሎችን ከልብ ማመስገን እወዳለሁ ሲሉ ተናግረዋል።

ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው በነበራቸው የላቀ ግዳጅ አፈፃፀም ከሻለቃ ማዕረግ ወደ ሌ/ኮ ማዕረግ ከፍ እንዲሉ ተደርጓል።

ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ዶክተሮች ቀናቶችን በተጋድሎና በጀብዶቻቸው እያደመቁ በፈታኝ እና ውስብስብ ግዳጆች ሳይበገሩ በሌላ ተልዕኮ ሌላ ገድል ለመፈፀም እራሳቸውን አዘጋጅተዋል። (ዘገባና ፎቶ ፍፁም ከተማ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    May 26, 2022 12:35 pm at 12:35 pm

    ሁሉም በተሰጠው ሙያና ሃላፊነት በፅናት ከሰራ ብሔራዊ ግዴታውን ስለተወጣ ከጀግኖችና በመልካም ታሪክ ይመዘገባል።
    ከሌቦች ኮሌጅ ተመርቀው እንደ አይጥ እየተዟዟሩ የሕዝብ ሓብት ሲዘርፉ የነበሩ ግን ሌቦች በሚል ታሪክ ስማቸው ይመዘገባል። ኢትዮጵያ የተለያዩ ልጆች ወልዳለች በጀግንነት የሚሞቱላት፣ በንቃት የሚጠብቋትና የሚንከባከብዋት፣በደር ቁጭ ብለው የሚመለከትዋትና ኣሰልፈው ለጠላት የሚሰጥዋት ናቸው።
    አገር ወይሞ ሞት የተባለበት ዘመን ነበር። ዛሬ ግን ብር ወይም ሞት ሆኖኣል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule