• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች”

May 26, 2022 08:19 am by Editor 1 Comment

በሙያቸው ብቃት እና በስነ ምግባራቸው በሠራዊታችንም ሆነ በሰቪል ማህበረሰቡ ዘንድ ተመስግነው የማያልፍ ታሪክን ሰርተው ህዝብና ሀገርን አኩርተዋል።

በዋሉበት አውድ ሁሉ በፅናትና በጀግንነት ከጦር ሠራዊቱ ጋር ፊት ለፊት በመሰለፍ ሠራዊቱን አክመዋል ባስ ሲል ደግሞ ጠመንጃቸውን አንስተው ጠላትን እያፍረከረኩ ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ድርብ ኃላፊነት በጀግንነት ተወጥተዋል።

ሰራዊቱ ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር በሚል ቁልፍ እሴት በተግባር ተቃኝቶ በህዝብና በሀገር የመጣን ጠላት ሲፋለም መተከያ የሌላትን ህይወት ለመታደግ እና ከደረሠበት ጉዳት ድኖ ወደ ግንባር እንዲመለስ በማድረግ ጀብዱ ፈፅመዋል ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ዶክተሮች።

ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው እና ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ ይባላሉ።

ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ናቸው። ከህግ ማስከበር እስከ ዘመቻ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት ድረስ ሠራዊቱን እና በአካባቢው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንዴት አገልግሎት ሲሰጡ እንደነበረ ይናገራሉ።

አሸባሪው የህውሃት ቡድን በሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ ጥቃት ባደረሰ ማግስት የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አባላት ከወትሮ በተለየ መልኩ ዘመቻውን ለመደገፍ የሚያስችል አደረጃጀት አድርገን ወደ ግንባር አቅንተናል።

ሠራዊታችን እለት ከእለት ድልን እያስመዘገበ እና የጠላትን ሃይል አከርካሪውን እየሰባበረ ወደ ፊት በሚገሰግስበት ጊዜም ተንቀሳቃሽ ሆስፒታሉ በፍጥነት ከሰራዊቱ ጋር በመንቀሳቀስ የሚጠበቅበትን የጦር ሜዳ አገልግሎት ሠጥቷል።

ተዋጊው ሃይላችን ከተማዎችን እየተቆጣጠረ ወደ ፊት ሲገሰግስ በከተማዎቹ ይኖሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ በማድረግ ህይወታቸውን መታደግ ችለናል። በዚህም ከራስ በፊት ለህዝብ እና ለሀገር የሚለውን ዕሴታችን በተግባር ማሳየት ችለናል።

በማይጠብሪ ግንባር እና በወሎ ግንባር ስንገባም እንደተለመደው ለሠራዊቱ የህክምና አገልግሎት በመስጠት የማድረግ አቅሙን፣ ሞራሉ እና ወታደራዊ ስነ ልቦናው እንዲጠበቅ በማድረግ ሠራዊቱ ወደ ግንባር ተመልሶ ጠላትን እንዲደመስስ ማድረግ ችለናል።

የተለያዩ ከመንግስትና ከሲቪል የህክምና ተቋማት የመጡ ባለሙያዎችም ከእኛ ጋር በግንባር በመሰለፍ ሠራዊቱን በሙያቸው አገልግለዋል። ከልጆቹ እና ከእለት ጉርሱ ቀንሶ ለእኛ ያካፈለን ደጀን ለሆነን ህዝባችን እና በሙያቸው ላገለገሉን የጤና ሙያተኞች ምስጋና አቅርቧል።

ሻ/ል ዶክተር ውበት ደምሴ በምዕራብ ዕዝ በተዘጋጀው የሜዳይ ሽልማት ላይ የሁለተኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ በመሆኑ ደስታኛ ነው። ሽልማቱ ቀጣይ ለሚጠብቀው ግዳጅ ሞራል እና ተነሳሽነትን እንደፈጠረለትም ገልጿል።

ሌላኛው የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አባል ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው፥ ውትድርና ብዙ የሙያ መስኮች የሚገኙበት እና በሀገራችን ህዝቦች ዘንድ ደግሞ ተወዳጅ የሆነ የሙያ ዘርፍ መሆኑን በመግለፅ ተቋሙ ባስተማረው እና ባበቃው የዶክተርነት ሙያ አሸባሪው የህውሃት ቡድን በሰሜን ዕዝ የሠራዊት አባላት ላይ ጥቃት ባደረሰበት ጊዜ ከባልደረቦቼ ጋር በመሆን ሠራዊታችንን በሙያችን በማገልገል የድል ባለቤት እንዲሆን የበኩላችንን ድርሻ መወጣት ችለናል።

ጀግናው ሠራዊታችን የሚያደርገውን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ በመከታተል እና ምሽግ ድረስ በመጓዝ ጤንነቱ የተጠበቀ እና የማድረግ አቅሙ የላቀ እንዲሆን የምዕራብ ዕዝ ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል አሁንም ያልተቆራረጠ ክትትል እያደረገ ይገኛል።

ዕዛችን በተንቀሳቀሰበት የግዳጅ ቀጣናዎች ሁሉ ሠራዊቱ ጉዳት ደርሶበታ ሲመጣ ተኝቶ እንዲታከም በማድረግ እና በፍጥነት አገግሞ ወደ ግዳጁ እንዲመለስ ያደረጉ የግል እና የመንግስት ሆስፒታሎችን ከልብ ማመስገን እወዳለሁ ሲሉ ተናግረዋል።

ሌ/ኮ ዶክተር ጌታሁን የሻነው በነበራቸው የላቀ ግዳጅ አፈፃፀም ከሻለቃ ማዕረግ ወደ ሌ/ኮ ማዕረግ ከፍ እንዲሉ ተደርጓል።

ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ዶክተሮች ቀናቶችን በተጋድሎና በጀብዶቻቸው እያደመቁ በፈታኝ እና ውስብስብ ግዳጆች ሳይበገሩ በሌላ ተልዕኮ ሌላ ገድል ለመፈፀም እራሳቸውን አዘጋጅተዋል። (ዘገባና ፎቶ ፍፁም ከተማ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    May 26, 2022 12:35 pm at 12:35 pm

    ሁሉም በተሰጠው ሙያና ሃላፊነት በፅናት ከሰራ ብሔራዊ ግዴታውን ስለተወጣ ከጀግኖችና በመልካም ታሪክ ይመዘገባል።
    ከሌቦች ኮሌጅ ተመርቀው እንደ አይጥ እየተዟዟሩ የሕዝብ ሓብት ሲዘርፉ የነበሩ ግን ሌቦች በሚል ታሪክ ስማቸው ይመዘገባል። ኢትዮጵያ የተለያዩ ልጆች ወልዳለች በጀግንነት የሚሞቱላት፣ በንቃት የሚጠብቋትና የሚንከባከብዋት፣በደር ቁጭ ብለው የሚመለከትዋትና ኣሰልፈው ለጠላት የሚሰጥዋት ናቸው።
    አገር ወይሞ ሞት የተባለበት ዘመን ነበር። ዛሬ ግን ብር ወይም ሞት ሆኖኣል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule