• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ”

June 5, 2022 06:58 pm by Editor Leave a Comment

መከላከያ ሰራዊታችን በውጊያ ወቅት ሀገርና ህዝብ የሰጠውን ተልዕኮ በጀግንነትና በድል ለመወጣት ሀሩር እና ብርዱ ሳይበግረው በየተራራው በየጥሻው ድንጋይ ተንተርሶ ሙቀቱን በላቡ ዝናቡን በሰውነቱ ሙቀት እየተቋቋመ ግዳጁን በድል ይወጣል።

አንፃራዊ ሰላም ባለበት ደግሞ በደረሰበት ቦታ ሁሉ ህዝባዊ ሰራዊትነቱን በተግባር ያሳያል። ካለው የዕለት ጉርሱ ቀንሶ ለተቸገሩ ወገኖች ያካፍላል። በጉልበቱም በገንዘቡም ይረዳል።

በምዕራብ ዕዝ በሚገኝ ክ/ጦር ሁለተኛ አባይ ሬጅመንት የሆነው እንዲህ ነው።

ህፃን አማኑኤል ሽፈራው ይባላል። የ11አመት ታዳጊ ሲሆን ተወልዶ ያደገው በሰሜን ጎንደር አድዓርቃይ ወረዳ አምበራ አካባቢ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በሚባል ሰፈር ነው ።

ህፃን አማኑኤል እንደሚለው እናቴ ትግራይ ለስራ እንደሄደች አልተመለሰችም። አባቴን አላውቀውም። ከአጎቴ ጋር ነበር የምኖረው። በጦርነቱ ምክንያት ከምንኖርበት መንደር ተፈናቅለን ወጣን። በመሃል ስመለስ አጎቴን ላገኘው አልቻልኩም።

የያኔውን ማረፊያ ማጣቱን ሲናገር ፊቱ ላይ የሚታየው ፍርሃት አሁን ላይ የተከሰተ አንዳች አስደንጋጭ ነገር ያለ እስኪመስል ድረስ በጉልህ ይነበባል።

አማራጮች ሁሉ የጠፋበት ህፃን አማኑኤል ከጎረቤት ተጠግቶ በርካታ ቀናትን አሳለፈ። አንድ ቀን ከሰፈር ጓደኞቼ ጋር እየተጫወትኩ አንድ የወታደር ልብስ የለበሰ ሰው በመሐላችን ተቀላቀለ ይላል ትንሹ ልጅ።

ወታደሩ የሁላችንንም ስም ጠየቀን … የማነህ ልጅ? ….ማነው ስምህ ? እያለ ይጠይቅ ነበር። ጥያቄው እኔ ላይ ሲደርስ ጓደኞቼ እሱኮ ቤተሰብ የለውም አሉት።

ወታደሩ ጓደኞቼ በነገሩት ነገር እንዳዘነና ግን ደግሞ አንተ ጎበዝ ልጅ ነህ። አይዞህ እያለ ፀጉሬን እያሻሸ አፅናናኝ። አብረውኝ የሚሰሩትን ወታደሮች ላማክርና እኛጋ እንድትሆን ጥረት አደርጋለሁ አለኝ።

ወታደሩ ሻ/ባሻ መታደል አለም እንደሚባል እና የሁለተኛ አባይ ሬጅመንት አባል እንደሆነ ነገረኝ።

ሻ/ባሻ መታደል ሬጅመንቷ በተሰበሰበችበት ስለልጁ ሁኔታ ለአባላቱ አስረዳቸው አባላቱም በጣም አዝነው በአንድ ድምፅ እኛ የበላነውን እየበላ ከኛ ጋር እያደረ እንደ ልጃችን እናሳድገዋለን በማለት ተስማሙ።

አማኑኤልንም ወደ ካምፓቸው አስገብተው ልብስ አልብሰው መኝታውን አዘጋጅተው አብሯቸው እንዲኖር አደረጉ ።

አሁን ላይ አማኑኤል ከሰራዊቱ ጋር ይጫወታል፣ ይዝናናል ልክ እንደቤተሰቦቹ ሆኗል።

ሻ/ል ባሻ መታደል እንዳለው ለልጁ የራሱን ገንዘብ እንዲያጠራቅም የሊስትሮ መስሪያ ማቴርያል እንዲገዛለት አድርገናል። በየጊዜው ሰራዊቱ የሚያወጣለትን ገንዘብ እንዲያጠራቅምም አካውንት በስሙ ከፍተንለታል።

እኔም እሱን አግኝቼ ሰራዊቱ ተስማምቶ ወደ ካምፕ ገብቶ ከኛጋ ስለኖረና ደስተኛ ስለሆነ በጣም ደስ ብሎኛል ይለናል።

የሬጅመንቷ አዛዥም መቶ አለቃ ሳፋየ ካራፎ ይህን ታዳጊ ለማሳደግ ሬጅመንቷ ሙሉ ፈቃደኛ ስለሆነች እና የአባላቱ ህዝባዊነትን በተደጋጋሚ ስለማይ ደስታዬ ላቅ ያለ ነው ብለዋል።

ታዳጊው ህፃን አማኑኤል ሽፈራውም እጅግ በጣም ደስተኛ እንደሆነና “እኔም አድጌ እንደእናተ ወታደር ሆኜ ሀገሬን በውትድርና ሙያ ለማገልገል ህልም አለኝ” ሲል ተናግሯል። (ዘገባና ፎቶ: ፍርዱ ሀብቴ – የመከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: amanuel shiferaw, endf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule