• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ”

June 5, 2022 06:58 pm by Editor Leave a Comment

መከላከያ ሰራዊታችን በውጊያ ወቅት ሀገርና ህዝብ የሰጠውን ተልዕኮ በጀግንነትና በድል ለመወጣት ሀሩር እና ብርዱ ሳይበግረው በየተራራው በየጥሻው ድንጋይ ተንተርሶ ሙቀቱን በላቡ ዝናቡን በሰውነቱ ሙቀት እየተቋቋመ ግዳጁን በድል ይወጣል።

አንፃራዊ ሰላም ባለበት ደግሞ በደረሰበት ቦታ ሁሉ ህዝባዊ ሰራዊትነቱን በተግባር ያሳያል። ካለው የዕለት ጉርሱ ቀንሶ ለተቸገሩ ወገኖች ያካፍላል። በጉልበቱም በገንዘቡም ይረዳል።

በምዕራብ ዕዝ በሚገኝ ክ/ጦር ሁለተኛ አባይ ሬጅመንት የሆነው እንዲህ ነው።

ህፃን አማኑኤል ሽፈራው ይባላል። የ11አመት ታዳጊ ሲሆን ተወልዶ ያደገው በሰሜን ጎንደር አድዓርቃይ ወረዳ አምበራ አካባቢ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በሚባል ሰፈር ነው ።

ህፃን አማኑኤል እንደሚለው እናቴ ትግራይ ለስራ እንደሄደች አልተመለሰችም። አባቴን አላውቀውም። ከአጎቴ ጋር ነበር የምኖረው። በጦርነቱ ምክንያት ከምንኖርበት መንደር ተፈናቅለን ወጣን። በመሃል ስመለስ አጎቴን ላገኘው አልቻልኩም።

የያኔውን ማረፊያ ማጣቱን ሲናገር ፊቱ ላይ የሚታየው ፍርሃት አሁን ላይ የተከሰተ አንዳች አስደንጋጭ ነገር ያለ እስኪመስል ድረስ በጉልህ ይነበባል።

አማራጮች ሁሉ የጠፋበት ህፃን አማኑኤል ከጎረቤት ተጠግቶ በርካታ ቀናትን አሳለፈ። አንድ ቀን ከሰፈር ጓደኞቼ ጋር እየተጫወትኩ አንድ የወታደር ልብስ የለበሰ ሰው በመሐላችን ተቀላቀለ ይላል ትንሹ ልጅ።

ወታደሩ የሁላችንንም ስም ጠየቀን … የማነህ ልጅ? ….ማነው ስምህ ? እያለ ይጠይቅ ነበር። ጥያቄው እኔ ላይ ሲደርስ ጓደኞቼ እሱኮ ቤተሰብ የለውም አሉት።

ወታደሩ ጓደኞቼ በነገሩት ነገር እንዳዘነና ግን ደግሞ አንተ ጎበዝ ልጅ ነህ። አይዞህ እያለ ፀጉሬን እያሻሸ አፅናናኝ። አብረውኝ የሚሰሩትን ወታደሮች ላማክርና እኛጋ እንድትሆን ጥረት አደርጋለሁ አለኝ።

ወታደሩ ሻ/ባሻ መታደል አለም እንደሚባል እና የሁለተኛ አባይ ሬጅመንት አባል እንደሆነ ነገረኝ።

ሻ/ባሻ መታደል ሬጅመንቷ በተሰበሰበችበት ስለልጁ ሁኔታ ለአባላቱ አስረዳቸው አባላቱም በጣም አዝነው በአንድ ድምፅ እኛ የበላነውን እየበላ ከኛ ጋር እያደረ እንደ ልጃችን እናሳድገዋለን በማለት ተስማሙ።

አማኑኤልንም ወደ ካምፓቸው አስገብተው ልብስ አልብሰው መኝታውን አዘጋጅተው አብሯቸው እንዲኖር አደረጉ ።

አሁን ላይ አማኑኤል ከሰራዊቱ ጋር ይጫወታል፣ ይዝናናል ልክ እንደቤተሰቦቹ ሆኗል።

ሻ/ል ባሻ መታደል እንዳለው ለልጁ የራሱን ገንዘብ እንዲያጠራቅም የሊስትሮ መስሪያ ማቴርያል እንዲገዛለት አድርገናል። በየጊዜው ሰራዊቱ የሚያወጣለትን ገንዘብ እንዲያጠራቅምም አካውንት በስሙ ከፍተንለታል።

እኔም እሱን አግኝቼ ሰራዊቱ ተስማምቶ ወደ ካምፕ ገብቶ ከኛጋ ስለኖረና ደስተኛ ስለሆነ በጣም ደስ ብሎኛል ይለናል።

የሬጅመንቷ አዛዥም መቶ አለቃ ሳፋየ ካራፎ ይህን ታዳጊ ለማሳደግ ሬጅመንቷ ሙሉ ፈቃደኛ ስለሆነች እና የአባላቱ ህዝባዊነትን በተደጋጋሚ ስለማይ ደስታዬ ላቅ ያለ ነው ብለዋል።

ታዳጊው ህፃን አማኑኤል ሽፈራውም እጅግ በጣም ደስተኛ እንደሆነና “እኔም አድጌ እንደእናተ ወታደር ሆኜ ሀገሬን በውትድርና ሙያ ለማገልገል ህልም አለኝ” ሲል ተናግሯል። (ዘገባና ፎቶ: ፍርዱ ሀብቴ – የመከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: amanuel shiferaw, endf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule