• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው

June 12, 2022 06:21 pm by Editor Leave a Comment

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ በኅልውና ዘመቻ እና በዘመቻ ለሕብረብሔራዊ አንድነት የግዳጅ ወቅት ከፍተኛ ጀግንነት ለፈጸሙ የመምሪያው አባላት የዕውቅናና የምስጋና መርኃግብር አካሂዷል።

በመርኃግብሩ ላይ በመገኘት ሽልማቱን የሰጡት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሙሉዓለም አድማሱ እንደተናገሩት አሸባሪው የትህነግ ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ከፈፀመበት ጊዜ ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ሀገርን ከውድቀት ለመታደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል።

መምሪያው በቀጣይ የሚሰጠውን ሀገራዊ ግዳጅ በጀግንነት ለመወጣት ይበልጥ ዝግጁ መኾን እንደሚገባውም ምክትል አዛዡ አሳስበዋል።

የዕዙ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ወርቅነህ ነዳሳ በበኩላቸው ክፍሉ በግዳጅ አፈጻጸም ወቅት የሠራዊቱ የጀርባ አጥንት በመኾን በርካታ አኩሪ ተግባራትን ፈጽሟል ነው ያሉት። በዚህም አዳዲስ ሞያተኞችን ከነባር የመገናኛ ባለሞያዎች ጋር በማቀናጀት ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወኑን ገልጸዋል።

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ በጦርነቶች ከፍተኛ ልምድ ያካበተ እንደመኾኑ መጠን በዕውቀት እና ቁሳቁስ የሰው ኀይሉን በመገንባት ግዳጅ የመፈጸም አቅሙን አስተማማኝ ደረጃ ላይ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።

ሽልማት ከተበረከተላቸው የመምሪያው አባላት መካከል ሻምበል ዝናቡ በቀለ በአሸባሪው ትህነግ ተበጣጥሶ የነበረውን የግንኙነት መስመር በራሱ ጥረት ቀጥታ አዲስ አበባ ካለው የጦር ክፍል ጋር ግንኙነት የመሰረተ ጓድ በመኾኑ የ1ኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ ኾኗል።

ሌላኛዋ ተሸላሚ አስር አለቃ አገሬ ያለው የዳታ እና ግንኙነት ባለሙያ ናት። የተሰጣትን ኀላፊነት በአስተማማኝ ብቃት የተወጣች በመኾኗ የ3ኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ ለመኾን ችላለች።

በዕውቅናና የምስጋና መርኃግብሩ ሌሎች ተሸላሚ አባላቶችም የተካተቱ ሲኾን በቀጣይም የኢትዮጵያን ኅልውና ከሚፈታተንና ከሚቃጣ ማንኛውም አደጋ ሀገራቸውን ለመታደግ ቁርጠኛ እንደኾኑ መግለጻቸውን ከመከላከያ ሠራዊት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

በሌላ በኩል የአማራ ልዩ ኀይል ተከዜ ክፍለ ጦር አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ቡድን በመደምሰስ ኢትዮጵያን ለማዳን በተደረገው ትግል የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ አመራሮች እና አባላቱ የእውቅናና የማዕረግና እድገት ሽልማት ሥነ ሥርዓት አካሂዷል።

በሥነ ሥርዓቱ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣የአማራ ልዩ ኀይል ረዳት ኮሚሽነርና የክፍለጦሩ አዛዥ፣የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

በመድረኩ የተከዜ ክፈለ ጦር አዛዥ ኮረኔል አብጀው ተፈራ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የአማራን ሕዝብ ለማጥፋት የከፈተውን ጦርነት ለመመከትና የአማራን ሕዝብ ከጥፋት፣ ኢትዮጵያን ከመፍረስ ለመታደግ በተደረገው ተጋድሎ ተከዜ ክፍለ ጦር ከሌሎች አሃዶች፣ ክፍለ ጦሮችና ከመላው የጸጥታ ኀይል ጋር በመጣመር ትልቅ ታሪክ ሠርቷል ብለዋል።

ክፍለ ጦሩ በተሰለፈባቸው አውደ ውጊያዎች ኹሉ ትልልቅ ጀብዱዎችን እየፈጸመ የዘለቀ ነው ያሉት አዛዡ በክፍለ ጦሩ ውስጥ የላቀ ጀብዱ ለፈጸሙ አመራሮችና አባላት የማበረታቻ ኒሻን ሽልማት ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። የተሰጣቸው ሽልማትም በቀጣይ ለሚኖረው ተልዕኮ በሞራል ዝግጁ እንዲኾኑ ያደርጋቸዋል ነው ያሉት።

ለአባላቱ የእውቅናና የማዕረግ እድገት ሽልማቱን ያበረከቱት የአማራ ልዩ ኀይል ረዳት ኮሚሽነር አዳነ አስማረ ማዕረጉ በብዙ ውጣውረድና ከፍተኛ መሥዋእትነት የተገኘ ነው ብለዋል።

“መንግሥት እውቅናና ሽልማቱን የሰጠው አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የአማራን ሕዝብ ለማንበርከክ ለዳግም ወረራ እየተዘጋጀ መኾኑን ተገንዝባችሁ ሊመጣ የሚችለውን ወረራ ለመቀልበስ ዝግጁ እንድትኾኑ አደራ እየሰጣችሁ ነው” ብለዋል ለልዩ ኀይል አባላቱ።

ሽልማት ከተበረከተላቸው የክፍለ ጦሩ አባላት መካከል ኢኒስፔክተር ፍትህአለው ሙሉ በፈጸሙት ጀብዱ በዕለቱ የሻለቃነት ማዕረግ አግኝተዋል።

ሻለቃ ፍትህአለው ‟በብዙ ጓዶች መሥዋእትነት እዚህ መድረሴን ባልዘነጋም በሽልማቱ ደስተኛ ነኝ” ብለዋል።

በቡያ፣ጠለምት፣አድርቃይ፣ብርብራ፣ቦዛ፣ብና ሜዳና ሌሎች አውደውጊያዎች ላይ እንደተሳተፉ ያነሱት ተሸላሚው በቀጣይ ለሚኖረው ማንኛውም ግዳጅ ሽልማቱ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸውና ዝግጁ መኾናቸውን አረጋግጠዋል።

ሌላኛው ተሸላሚ ኢንስፔክተር ጀጀው ፈረደ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይልን ለመደምሰስ በተደረገው ተጋድሎ የአማራ ልዩ ኀይል ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር ተጣምሮ በርካታ ጀብዱውችን ፈጽሟል ብለዋል።በዚህ ውስጥም ተከዜ ክፍለ ጦር ሚናው ከፍተኛ ነበር ነው ያሉት።

ሽልማቱ በብዙ ጀግኖች መሥዋእትነት የተገኘ መኾኑን እረዳለኹ የሚሉት ተሸላሚው ‟የተሰውትን ጀግኖች ቃል ጠብቀን በቀጣይ ለሚኖር ግዳጅ ከፍተኛ መነሳሳትን ፈጥሮልናል” ነው ያሉት።

ክፍለ ጠሩ አሸባሪው የትግራይን ወራሪ ቡድንን ለመደምሰስ ባደረገው ተጋድሎ ከጸጥታ ኀይሉ ጎን ተሰልፎ በስንቅ፣በውጊያና በሞራል ድጋፍ ላደረገው የሰሜን ጎንደር ሕዝብ፣ለፋኖ አባላትና ለሌሎች ግለሰቦች የእውቅና ወረቀት ሽልማት አበርክቷል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara special force, endf, endf western command, mulualem admasu, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule