• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው

June 12, 2022 06:21 pm by Editor Leave a Comment

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ በኅልውና ዘመቻ እና በዘመቻ ለሕብረብሔራዊ አንድነት የግዳጅ ወቅት ከፍተኛ ጀግንነት ለፈጸሙ የመምሪያው አባላት የዕውቅናና የምስጋና መርኃግብር አካሂዷል።

በመርኃግብሩ ላይ በመገኘት ሽልማቱን የሰጡት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሙሉዓለም አድማሱ እንደተናገሩት አሸባሪው የትህነግ ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ከፈፀመበት ጊዜ ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ሀገርን ከውድቀት ለመታደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል።

መምሪያው በቀጣይ የሚሰጠውን ሀገራዊ ግዳጅ በጀግንነት ለመወጣት ይበልጥ ዝግጁ መኾን እንደሚገባውም ምክትል አዛዡ አሳስበዋል።

የዕዙ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ወርቅነህ ነዳሳ በበኩላቸው ክፍሉ በግዳጅ አፈጻጸም ወቅት የሠራዊቱ የጀርባ አጥንት በመኾን በርካታ አኩሪ ተግባራትን ፈጽሟል ነው ያሉት። በዚህም አዳዲስ ሞያተኞችን ከነባር የመገናኛ ባለሞያዎች ጋር በማቀናጀት ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወኑን ገልጸዋል።

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ በጦርነቶች ከፍተኛ ልምድ ያካበተ እንደመኾኑ መጠን በዕውቀት እና ቁሳቁስ የሰው ኀይሉን በመገንባት ግዳጅ የመፈጸም አቅሙን አስተማማኝ ደረጃ ላይ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።

ሽልማት ከተበረከተላቸው የመምሪያው አባላት መካከል ሻምበል ዝናቡ በቀለ በአሸባሪው ትህነግ ተበጣጥሶ የነበረውን የግንኙነት መስመር በራሱ ጥረት ቀጥታ አዲስ አበባ ካለው የጦር ክፍል ጋር ግንኙነት የመሰረተ ጓድ በመኾኑ የ1ኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ ኾኗል።

ሌላኛዋ ተሸላሚ አስር አለቃ አገሬ ያለው የዳታ እና ግንኙነት ባለሙያ ናት። የተሰጣትን ኀላፊነት በአስተማማኝ ብቃት የተወጣች በመኾኗ የ3ኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ ለመኾን ችላለች።

በዕውቅናና የምስጋና መርኃግብሩ ሌሎች ተሸላሚ አባላቶችም የተካተቱ ሲኾን በቀጣይም የኢትዮጵያን ኅልውና ከሚፈታተንና ከሚቃጣ ማንኛውም አደጋ ሀገራቸውን ለመታደግ ቁርጠኛ እንደኾኑ መግለጻቸውን ከመከላከያ ሠራዊት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

በሌላ በኩል የአማራ ልዩ ኀይል ተከዜ ክፍለ ጦር አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ቡድን በመደምሰስ ኢትዮጵያን ለማዳን በተደረገው ትግል የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ አመራሮች እና አባላቱ የእውቅናና የማዕረግና እድገት ሽልማት ሥነ ሥርዓት አካሂዷል።

በሥነ ሥርዓቱ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣የአማራ ልዩ ኀይል ረዳት ኮሚሽነርና የክፍለጦሩ አዛዥ፣የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

በመድረኩ የተከዜ ክፈለ ጦር አዛዥ ኮረኔል አብጀው ተፈራ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የአማራን ሕዝብ ለማጥፋት የከፈተውን ጦርነት ለመመከትና የአማራን ሕዝብ ከጥፋት፣ ኢትዮጵያን ከመፍረስ ለመታደግ በተደረገው ተጋድሎ ተከዜ ክፍለ ጦር ከሌሎች አሃዶች፣ ክፍለ ጦሮችና ከመላው የጸጥታ ኀይል ጋር በመጣመር ትልቅ ታሪክ ሠርቷል ብለዋል።

ክፍለ ጦሩ በተሰለፈባቸው አውደ ውጊያዎች ኹሉ ትልልቅ ጀብዱዎችን እየፈጸመ የዘለቀ ነው ያሉት አዛዡ በክፍለ ጦሩ ውስጥ የላቀ ጀብዱ ለፈጸሙ አመራሮችና አባላት የማበረታቻ ኒሻን ሽልማት ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። የተሰጣቸው ሽልማትም በቀጣይ ለሚኖረው ተልዕኮ በሞራል ዝግጁ እንዲኾኑ ያደርጋቸዋል ነው ያሉት።

ለአባላቱ የእውቅናና የማዕረግ እድገት ሽልማቱን ያበረከቱት የአማራ ልዩ ኀይል ረዳት ኮሚሽነር አዳነ አስማረ ማዕረጉ በብዙ ውጣውረድና ከፍተኛ መሥዋእትነት የተገኘ ነው ብለዋል።

“መንግሥት እውቅናና ሽልማቱን የሰጠው አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የአማራን ሕዝብ ለማንበርከክ ለዳግም ወረራ እየተዘጋጀ መኾኑን ተገንዝባችሁ ሊመጣ የሚችለውን ወረራ ለመቀልበስ ዝግጁ እንድትኾኑ አደራ እየሰጣችሁ ነው” ብለዋል ለልዩ ኀይል አባላቱ።

ሽልማት ከተበረከተላቸው የክፍለ ጦሩ አባላት መካከል ኢኒስፔክተር ፍትህአለው ሙሉ በፈጸሙት ጀብዱ በዕለቱ የሻለቃነት ማዕረግ አግኝተዋል።

ሻለቃ ፍትህአለው ‟በብዙ ጓዶች መሥዋእትነት እዚህ መድረሴን ባልዘነጋም በሽልማቱ ደስተኛ ነኝ” ብለዋል።

በቡያ፣ጠለምት፣አድርቃይ፣ብርብራ፣ቦዛ፣ብና ሜዳና ሌሎች አውደውጊያዎች ላይ እንደተሳተፉ ያነሱት ተሸላሚው በቀጣይ ለሚኖረው ማንኛውም ግዳጅ ሽልማቱ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸውና ዝግጁ መኾናቸውን አረጋግጠዋል።

ሌላኛው ተሸላሚ ኢንስፔክተር ጀጀው ፈረደ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይልን ለመደምሰስ በተደረገው ተጋድሎ የአማራ ልዩ ኀይል ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር ተጣምሮ በርካታ ጀብዱውችን ፈጽሟል ብለዋል።በዚህ ውስጥም ተከዜ ክፍለ ጦር ሚናው ከፍተኛ ነበር ነው ያሉት።

ሽልማቱ በብዙ ጀግኖች መሥዋእትነት የተገኘ መኾኑን እረዳለኹ የሚሉት ተሸላሚው ‟የተሰውትን ጀግኖች ቃል ጠብቀን በቀጣይ ለሚኖር ግዳጅ ከፍተኛ መነሳሳትን ፈጥሮልናል” ነው ያሉት።

ክፍለ ጠሩ አሸባሪው የትግራይን ወራሪ ቡድንን ለመደምሰስ ባደረገው ተጋድሎ ከጸጥታ ኀይሉ ጎን ተሰልፎ በስንቅ፣በውጊያና በሞራል ድጋፍ ላደረገው የሰሜን ጎንደር ሕዝብ፣ለፋኖ አባላትና ለሌሎች ግለሰቦች የእውቅና ወረቀት ሽልማት አበርክቷል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara special force, endf, endf western command, mulualem admasu, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule