• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው

June 12, 2022 06:21 pm by Editor Leave a Comment

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ በኅልውና ዘመቻ እና በዘመቻ ለሕብረብሔራዊ አንድነት የግዳጅ ወቅት ከፍተኛ ጀግንነት ለፈጸሙ የመምሪያው አባላት የዕውቅናና የምስጋና መርኃግብር አካሂዷል።

በመርኃግብሩ ላይ በመገኘት ሽልማቱን የሰጡት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሙሉዓለም አድማሱ እንደተናገሩት አሸባሪው የትህነግ ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ከፈፀመበት ጊዜ ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ሀገርን ከውድቀት ለመታደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል።

መምሪያው በቀጣይ የሚሰጠውን ሀገራዊ ግዳጅ በጀግንነት ለመወጣት ይበልጥ ዝግጁ መኾን እንደሚገባውም ምክትል አዛዡ አሳስበዋል።

የዕዙ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ ኀላፊ ኮሎኔል ወርቅነህ ነዳሳ በበኩላቸው ክፍሉ በግዳጅ አፈጻጸም ወቅት የሠራዊቱ የጀርባ አጥንት በመኾን በርካታ አኩሪ ተግባራትን ፈጽሟል ነው ያሉት። በዚህም አዳዲስ ሞያተኞችን ከነባር የመገናኛ ባለሞያዎች ጋር በማቀናጀት ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወኑን ገልጸዋል።

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮሙኒኬሽንና ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር መምሪያ በጦርነቶች ከፍተኛ ልምድ ያካበተ እንደመኾኑ መጠን በዕውቀት እና ቁሳቁስ የሰው ኀይሉን በመገንባት ግዳጅ የመፈጸም አቅሙን አስተማማኝ ደረጃ ላይ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።

ሽልማት ከተበረከተላቸው የመምሪያው አባላት መካከል ሻምበል ዝናቡ በቀለ በአሸባሪው ትህነግ ተበጣጥሶ የነበረውን የግንኙነት መስመር በራሱ ጥረት ቀጥታ አዲስ አበባ ካለው የጦር ክፍል ጋር ግንኙነት የመሰረተ ጓድ በመኾኑ የ1ኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ ኾኗል።

ሌላኛዋ ተሸላሚ አስር አለቃ አገሬ ያለው የዳታ እና ግንኙነት ባለሙያ ናት። የተሰጣትን ኀላፊነት በአስተማማኝ ብቃት የተወጣች በመኾኗ የ3ኛ ደረጃ ሜዳይ ተሸላሚ ለመኾን ችላለች።

በዕውቅናና የምስጋና መርኃግብሩ ሌሎች ተሸላሚ አባላቶችም የተካተቱ ሲኾን በቀጣይም የኢትዮጵያን ኅልውና ከሚፈታተንና ከሚቃጣ ማንኛውም አደጋ ሀገራቸውን ለመታደግ ቁርጠኛ እንደኾኑ መግለጻቸውን ከመከላከያ ሠራዊት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

በሌላ በኩል የአማራ ልዩ ኀይል ተከዜ ክፍለ ጦር አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ቡድን በመደምሰስ ኢትዮጵያን ለማዳን በተደረገው ትግል የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ አመራሮች እና አባላቱ የእውቅናና የማዕረግና እድገት ሽልማት ሥነ ሥርዓት አካሂዷል።

በሥነ ሥርዓቱ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣የአማራ ልዩ ኀይል ረዳት ኮሚሽነርና የክፍለጦሩ አዛዥ፣የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

በመድረኩ የተከዜ ክፈለ ጦር አዛዥ ኮረኔል አብጀው ተፈራ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የአማራን ሕዝብ ለማጥፋት የከፈተውን ጦርነት ለመመከትና የአማራን ሕዝብ ከጥፋት፣ ኢትዮጵያን ከመፍረስ ለመታደግ በተደረገው ተጋድሎ ተከዜ ክፍለ ጦር ከሌሎች አሃዶች፣ ክፍለ ጦሮችና ከመላው የጸጥታ ኀይል ጋር በመጣመር ትልቅ ታሪክ ሠርቷል ብለዋል።

ክፍለ ጦሩ በተሰለፈባቸው አውደ ውጊያዎች ኹሉ ትልልቅ ጀብዱዎችን እየፈጸመ የዘለቀ ነው ያሉት አዛዡ በክፍለ ጦሩ ውስጥ የላቀ ጀብዱ ለፈጸሙ አመራሮችና አባላት የማበረታቻ ኒሻን ሽልማት ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። የተሰጣቸው ሽልማትም በቀጣይ ለሚኖረው ተልዕኮ በሞራል ዝግጁ እንዲኾኑ ያደርጋቸዋል ነው ያሉት።

ለአባላቱ የእውቅናና የማዕረግ እድገት ሽልማቱን ያበረከቱት የአማራ ልዩ ኀይል ረዳት ኮሚሽነር አዳነ አስማረ ማዕረጉ በብዙ ውጣውረድና ከፍተኛ መሥዋእትነት የተገኘ ነው ብለዋል።

“መንግሥት እውቅናና ሽልማቱን የሰጠው አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የአማራን ሕዝብ ለማንበርከክ ለዳግም ወረራ እየተዘጋጀ መኾኑን ተገንዝባችሁ ሊመጣ የሚችለውን ወረራ ለመቀልበስ ዝግጁ እንድትኾኑ አደራ እየሰጣችሁ ነው” ብለዋል ለልዩ ኀይል አባላቱ።

ሽልማት ከተበረከተላቸው የክፍለ ጦሩ አባላት መካከል ኢኒስፔክተር ፍትህአለው ሙሉ በፈጸሙት ጀብዱ በዕለቱ የሻለቃነት ማዕረግ አግኝተዋል።

ሻለቃ ፍትህአለው ‟በብዙ ጓዶች መሥዋእትነት እዚህ መድረሴን ባልዘነጋም በሽልማቱ ደስተኛ ነኝ” ብለዋል።

በቡያ፣ጠለምት፣አድርቃይ፣ብርብራ፣ቦዛ፣ብና ሜዳና ሌሎች አውደውጊያዎች ላይ እንደተሳተፉ ያነሱት ተሸላሚው በቀጣይ ለሚኖረው ማንኛውም ግዳጅ ሽልማቱ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸውና ዝግጁ መኾናቸውን አረጋግጠዋል።

ሌላኛው ተሸላሚ ኢንስፔክተር ጀጀው ፈረደ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይልን ለመደምሰስ በተደረገው ተጋድሎ የአማራ ልዩ ኀይል ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር ተጣምሮ በርካታ ጀብዱውችን ፈጽሟል ብለዋል።በዚህ ውስጥም ተከዜ ክፍለ ጦር ሚናው ከፍተኛ ነበር ነው ያሉት።

ሽልማቱ በብዙ ጀግኖች መሥዋእትነት የተገኘ መኾኑን እረዳለኹ የሚሉት ተሸላሚው ‟የተሰውትን ጀግኖች ቃል ጠብቀን በቀጣይ ለሚኖር ግዳጅ ከፍተኛ መነሳሳትን ፈጥሮልናል” ነው ያሉት።

ክፍለ ጠሩ አሸባሪው የትግራይን ወራሪ ቡድንን ለመደምሰስ ባደረገው ተጋድሎ ከጸጥታ ኀይሉ ጎን ተሰልፎ በስንቅ፣በውጊያና በሞራል ድጋፍ ላደረገው የሰሜን ጎንደር ሕዝብ፣ለፋኖ አባላትና ለሌሎች ግለሰቦች የእውቅና ወረቀት ሽልማት አበርክቷል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara special force, endf, endf western command, mulualem admasu, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule