• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘመኑን የጠበቀ የወታደራዊ ሬዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ተከፈተ

August 8, 2024 05:24 pm by Editor Leave a Comment

በመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የኤሌክትሮኒክስ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ የራዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣ የጦር ሀይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ  እና የተቋሙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በተገኙበት ነው ተመርቆ የተከፈተው።

የመከላከያ ሰራዊታችን አገራችን በየጊዜው የገጠሟትን ፈተናዎች በሌሎች አገራት ቴክኖሎጂዎች ላይ በመመርኮዝ ግዳጅ እየተወጣ እንደዘለቀ አውስተው የተመረቀው የወታደራዊ ራዲዮ ፋብሪካ የሰራዊቱን የተልዕኮ አፈፃፀምና የግዳጅ ስምሪት የሚያቀላጥፍ እንደሆነ ተናግረዋል።

“ወታደራዊ ራዲዮው በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ የመጨረሻው የዲጅታል ስታንዳርድ ራዲዮ ነው።” ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ይህንኑ እውን በማድረግ ረገድ የቻይናው ሀይቴራ ካምፓኒ እና የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን አመራሮች ላበረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሀይለማርያም በበኩላቸው ፋብሪካው የመካከለኛና የረጅም ርቀት ወታደራዊ ራዲዮኖችን የሚያመርት መሆኑን ጠቅሰው ከወታደራዊ ራዲዮኖች ባለፈ ለሲቪል አገልግሎት የሚውሉ ራዲዮኖችን የሚያመርት ፋብሪካ እንደሆነ ተናግረዋል።

የመከላከያ ተቋም ከዚህ በኋላ ምንም አይነት የግንኙነት ራዲዮ ከውጭ አገር እንደማይገዛና ሙሉ በሙሉ በተመረቀው የራዲዮ ፋብሪካ እንደሚሸፈን ያስታወቁት ዋና ዳይሬክተሩ  አቶ ጌታቸው ሀይለማርያም ፋብሪካው በዓመት 32 ሺህ ራዲዮኖችን የማምረት አቅም እንዳለውም ገልፀዋል።

የኤሌክትሮኒክስ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ስራ አስኪያጅ ኮሎኔል ዘውዱ አለፈ የፋብሪካውን አጠቃላይ ሁኔታ ለመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች ያስቃኙ ሲሆን በፋብሪካው የቴክኖሎጂ ሽግግር የተካሄደበት እና በሜጄር ጄኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተማሩ የቴክኒክ ሙያተኞች በመገጣጠሙ ተግባር ይሳተፉበታል ብለዋል።

ወታደራዊ ራዲዮው እጅግ ዘመናዊ ፣ በአገራችን ማንኛውም የአየር ፀባይ ያለ እንከን የሚሰራ ፣ ለአያያዝ ቀላል፣ ለየትኛውም ግዳጅ የሚመች እንደሆነና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኝ መሆኑም በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል። (የመከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: endf, latest military radio

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule