• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውትድርና ሕይወቴ ነው”

October 26, 2023 12:13 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያዊያን በሀገራችው ሰማይ ስር የመጣን ጠላት በማሽመድመድ ካስመዘገቡት ደማቅ ታሪክ ፊት ለፊት ትልቁን ድርሻ ከሚወስዱት አንዱ ናቸው።  ለሀገራቸው በዋሉት ውለታ ከሚተረክላቸው ቀዳሚ ባለ ታሪኮች ቀድመው ይጠቀሳሉ። ሙሉ ህይወታቸውን ለሀገራቸው የሰጡ ናቸው። ጀግና ተዋጊ፣ የበቁ የጦር መሪ፣ የተሳካላቸው የጦር አዛዥ ሆነው አገልግለዋል። በበርካታ የጦር ሜዳ ውጊያዎች ተሳትፈው የሀገርን ሉዓላዊነት፣ የህዝብን ነፃነት ያስከበረ ደማቅ ድል አስመዝግበዋል። ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያም። 

ጄኔራል መኮንኑ በ1934 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ከቸሀ ወረዳ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሲሰ መንደር ተወለዱ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም እዚያው እምድብር ከተማ ተምረው በ1948 ዓመተ ምህረትም አጠናቀዋል።

ከ1949-1952 ዓ.ም ድረስ አምቦ የእርሻ ልማት ትምህርት ቤት ተምረዋል። በመቀጠልም የምርጥ መኮንኖች ማፍሪያ በነበረው በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ሀረር) የጦር አካዳሚ በመግባት ለ3 ዓመታት ያህል የወታደራዊ ሳይንስና የአካዳሚ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።

ጥቅምት 4 ቀን 1956 ዓ.ም ከሀረር የጦር አካዳሚ ከተመረቁ በኋላ የአየር ወለድ ስልጠናም ለ6 ወራት ያህል ወስደው በምስራቅ ዕዝ 3ኛ ክፍለ ጦር 25ኛ ሻለቃ ልዩ ስሙ ኦጋንዳን /ደጋሃብር/ በተባለ ቦታ ላይ በመቶ አዛዥነት ተመድበው ሰርተዋል።

ከ6 ወራት የኦጋደን ደጋሀቡር ቆይታ በኋላ ደሬድዋ ላይ ለ2 ዓመታት ያህልም የስፔሻል ፎርስ አሰልጣኝ በመሆን ሰርተዋል። በ1960 ዓ.ም የማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ሃላፊ ሆነውም አገልግለዋል።

በ1967 ዓ.ም የመንግስት ለውጥ መደረጉን ተከትሎ ገነት ጦር ትምህርት ቤት በእግረኛ አስተማሪነት ተመድበው ሰርተዋል። በመቀጠልም የኢትጵያን አየር ወለድ ኃይል በሻምበል አዛዥነት መምራት ችለዋል። በወቅቱ የክበር ዘበኛ ክፍለ ጦርና የ3 ብርጌድ አካል የነበረች የ15ኛ ሻለቃ የጦር ከፍል የሳህላ አወራጃ የናቅፋ ከተማን ፀጥታ እስከበረችና ከጠላት ጋር እየተፋለመች ነበር።

ነገሮች እየተካረሩ ሲሄዱም ሻለቃዋን የሚያጠናክር ኃይል መላክ እንዳለበት በመንግስት ታምኖ አየር ወለድም በፓራሹት ወርዶ ድጋፍ እንዲያደርግ ተወሰነ። በወቅቱ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማርያም የአየር ወለድ አዛዥ ነበሩ። የአየር ወለድ አባላቱም አምነውበት ሀላፊነቱን ተቀበልው ከመንደፈራ ወደ አስመራ ከዚያም ወደ ናቅፋ የግዳጅ ቀጠና በረራ አደረጉ።

በቦታው እንደደረሱም የተቀናጀ ስኬታማ ውጊያ አድርገው የሻለቃዋን ማሽግ ተረክበው ለ6 ወራት ያህልም በምግብ፣ በመጠጥ፣ በልብስ፣ በጥይት በህክምና እጥረት መፈተናችውን ያስታውሳሉ። በመጨረሻም ከነበረው መንግስት ከአቅሜ በላይ ስለሆነ ራስህ ወስን የሚል ትዕዛዝ ደረሳቸው። ይህ ሲባልም ለጠላት እጅ መስጠት፣ ራስን ማጥፋት ወይም ሰብሮ መውጣት ከሚሉ 3 ነገሮች አንዱን መምረጥ ግድ ይላል።

ጀግና ታሪክ ይሰራል እንጂ ታሪክ አያበላሽም። ስለጉዳዩ ውይይት ካደረጉ በኋላም የእጅ በእጅ የጨበጣ ውጊያን ምርጫቸው አድርገው ጠላትን ደምስሰው መውጣታቸውን አስታውሰዋል። ከ3ቀናት የ60 ኪሎ ሜትር ጉዞ በኋላ ከወገን ጦር ጋር ሲገናኙም ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ለፈፀሙት ጀብዱ ማበረታቻ ይሆን ዘንድም ሻለቃ ማዕረግ በለበሱ ከጥቂት ወራት በኋላ የሌተናል ኮሎኔል የማዕረግ ዕድገት ተሰጥቷቸዋል።

ሀዋሳ ላይ ተቋቁሞ የነበረውን የፓራ ኮማንዶ ብርጌድ አደራጅተው አሰልጥነዋል። በወቅቱ የብርጌድ አንድ ክፍል በነበረው ጦርነት ክፍላቸውን ይዘው የተሠጣቸውን ግዳጅ በብቃት ተወጥተዋል። በ1970 ዓ.ም  ከምስራቁ የሀገራችን ክፍል ወደ ሰሜን በመመለስ የግብረ ኃይል አዛዥ በመሆን ሰርተዋል። በኤርትራ ምድር ጥይት በጮኸበት ቦታ ሁሉ ያልተሳተፉበት ውጊያ የለም። ለዚህም መስከረም 3 ቀን 1972 ዓ.ም ወደር የሌለው የኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ ተሸላሚ ለመሆን በቅተዋል።

ዘንድሮ በሀገራችን 116ኛው የሠራዊት ቀን ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ይከበራል። የሠራዊት ቀን ማክበር ደግሞ ለሀገር ብለው ለተሰውም ሆነ በህይወት ላሉት እውቅና መስጠት ነው። ሀገራችንም በዚሁ አግባብ ማክበሯ ተገቢ ነው። ለሀገር መከላከያ ሠራዊታችን አሁንም ቅርበት አላቸው። በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ሁኔታ በሠራዊቱ ላይ የደረሰው ጉዳት ጉዳታቸው ሆኖ አሟቸዋል። በጋሸና በአፋርና በጣርማ በር ግንባሮች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። አበረታተዋል።

የውትድርና ህይወት በጣም ከባድ ህይወት ነው። የህይወት መስዋዕትነትን ይጠይቃል። ሰው ሆኖ የማይሞት የለም። መለየት ያለበት የት ሆነህ መሞትን ትመርጣለህ የሚለው ነው። በውትድርና ህይወት ውስጥ መሞት ታሪክ ነው። እንደመኖር ይቆጠራል። ለሀገርና ለህዝብ ደግሞ ህይወትን መስጠት መታደል ነው። ህይወትህን ከፍለህ ህይወት ትሰጥበታለህ። የሀገር ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ፣ ህዝቦች ከቦታ ቦታ በነፃነት ተንቀሳቅሰው መኖር እንዲችሉ ወታደሩ ድንበር ላይ ይቆማል።

ወታደር በወታደራዊ ንድፈ ሀሳብ አእምሮው የጎለበተ መሆን አለበት። ከብረት የጠነከረ የአካል ብቃትና ስነ-ስረዓት ሊኖረው ይገባል። ለችግሮች እጅ የሚሰጥ ሳይሆን ችግርን የሚረታ መሆን አለበት። የዘመናዊነት መነሻው ስህተትን አውቆ ለማስተካከል ጥረት ማድረግ ስለሆነ አሁን እየተወሰደ ያለው ሠራዊቱን የማዘመን ስራ ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። ጠንካራ ሠራዊት ለመፍጠር ስልጠና ወሳኝ ነው። በማሰልጠኛዎች ላይ ሊሰራ ይገባል።

የሠራዊት ፈጣሪ ሞተሮች አሰልጣኞች ናቸው። አሰልጣኞችም መስለው ሳይሆን ሆነው ቆመው ሳይሆን ሰርተው የሚያሳዩ ሊሆኑ ይገባል። ያኔ ሠራዊታችን ብቃትና ዲስፕሊንን ከህዝባዊነት ጋር አጣምሮ ይዟል። የተሻለና ዘመናዊም ይሆናል። ስለሆነም ለእናት ሀገሩና ለዓለም ሰላም ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለ ነው።

ሀገራችን በሰላም ማስከበር ግዳጅ በአለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ዝናና ክብር አላት። ሠራዊቱም ከፍተኛ ፓለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሚናዎችን መጫዎት ችሏል። የጀኔራል መኮንኑ ድንቅ የህይወት ተሞክሮም አሁን ላለው የሠራዊት አመራርና አባላት የሞራል ስንቅ ነውና በዚሁ ልክ ለሀገራችን ልንሰራ ይገባናል። (አደም አሊ የመከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column, Social Tagged With: endf, general tesfaye, Tesfaye Habtemariam

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule