• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”

October 26, 2023 12:57 am by Editor 1 Comment

“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና  የድል ሠራዊት ” በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው ለዘንድሮ ለ116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን።

እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ የረዥም ዓመታት ሀገርን ከጠላት የመከላከል የተጋድሎ ታሪክ ካላቸው ሀገራት መካከል በጀግኖች ልጆቿ የአይበገሬነት ፊት የምትሠለፍ ታሪካዊት ሀገር ናት።

ከቀደመው ዘመን ጀምረን አሁን ላይ ያለውን እውነታ እንኳ ብንቃኝ ኢትዮጵያ በርካታ የውጪ ወራሪ ሀገራት ያሠፈሠፉባት ጥቂት የማይባሉ የውስጥ እርስ በርስ ግጭቶች የተከሰቱባት በባንዳዎች የተፈተነችበትና  በየትኛውም ዘመን ያልተንበረከከች የወራሪዎችን ፈተና አልፋ ዛሬ ላይ የደረሠች ሥለመሆኗ የታሪክ ድርሳናት መዝግቧል።

በሀገራችን የጀግንነት የታሪክ መዝገብ ያልሠፈሩ ግን ደግሞ አለም ያወቃቸው ቱባ ባህሎችና ድንቅ ታሪኮች ያላት ኢትዮጵያ በታሪክ በሠራዊቷ ኮርታ እንጅ አንድም ጊዜ አፍራ እንደማታውቅ ታሪክ ህያው ምስክር ነው ።

ዛሬ ላይም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ሀገረ ጠል በሆኑ ባንዳዎችና የፀረ ሠላም ሀይሎች ችግሮች ቢከሠቱም ጀግንነት ባህል ልምዱ እና የዘወትር ተግባሩ ባደረገው ሠራዊታችንና ህዝባችን የሠላም እንቅፋቶችን ፈተና ተቋቁማ ሀገራችን በልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች።

በመሆኑም በየትኛውም ጊዜ እና በማንኛውም ቦታ ለሠራዊታችን ብርታት ሞራልና የጀርባ አጥንት ከሆነው ህዝባችን ጋር ሆነን ሠላማችንን እያሥቀጠልን እንገኛለን።

116ኛው የመከላከያ ሠራዊት ቀንም ይበልጥ ቃላችንን የምናደስበት በየዘመናቱ ለሀገራችን ሉዓላዊነት ሲሉ መስዋዕት የከፈሉ ጀግኖችን የምንዘክርበትና ከመላው ህዝባችን ጋር ሆነን ለሀገራችን ሠላምና ልማት ማበብ በጋራ የምንቆምበት  ዕለት ጭምር ነው።

እናም እንደ መሪ ቃላችን በተፈተን ጊዜ ሁሉ ፀንተን የድል ሠራዊት ሆነን ዛሬ ላይ እንደደረሥነው ቀጣይም ከመላው ህዝባችን ጋር ለሀገራችን መክፈል ያለብንን ሁሉ ዋጋ  በመክፈል የኢትዮጵያን ሠላም እና ዕድገት አፅንተን እናሥቀጥላለን ።

“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”

ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: 116 anniversary of endf, endf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 26, 2023 01:04 pm at 1:04 pm

    በሃበሻ ፓለቲካ በራስ አስቦ የራስን ሃሳብ ለሌሎች ማካፈል ከመ አሪዎስ ተብሎ ከተወገዘ ዘመን አለፈ። ይኸው አሁን እውቁ ጋዘጠኛ ሲሳይ አጌና ላይ የሚለጠፉ ወልጋዳ ሃሳቦችን ለሰማና ላነበበ የሃበሻው ፓለቲካ የጅምላ ህሳቤን የተላበሰ እንጂ በራስ መቆም የማይቻል መሆኑን ያሳያል። በብዙ መከራ ውስጥ ያለፈው ይህ ምጡቅ ጋዜጠኛ የኢትዮጵያን ሰራዊት ጥንካሬና አንድነት ከሃገሪቱ ልዕልና እና ቀጣይነት ጋር አጣምሮ በማየቱ በዚህም በዚያም ይዘለፋል። ይህ በየወንዙ የሚማማለው የሃበሻ ፓለቲካ የአስረሽ ምቺው ስልት ስለሚከተል ከትላንቱ የሚማር ሳይሆን ለዛሬ ብቻ ኑሮ ዛሬ ላይ የሚከስም ነው። ያለፈ ታሪካችንም የሚያሳየው ይህኑ ነው።
    የኢትዪጵያ ወታደሮች ያኔም ሆነ አሁን የውስጥና የውጭ ጠላትን የተፋለሙት መጭው ትውልድ በሰላምና በደስታ እንዲኖር ነበረ። ያ ግን ሆኖ አያውቅም። የሰው ተንኮል ከመንግስታት ሸፍጥ ጋር እየተላበደ ህዝባችን እየከፋፈለ ዛሬ ላለንበት እኛ ብቻ እንኑር ፓለቲካ አሽጋግሮናል። እንደ ሃምሌ ዝናብ የማይቆመው ይህ የህዝባችን ሰቆቃ ምንጩ እኛም መንግስትም ነው። ሲጀመር ለሰላም ቆመናል የሚሉ ሃይሎች ሁሉ በተንኮልና በሸር የተነከሩ በመሆናቸው የሚታያቸው የእነርሱ መኖር እንጂ የሰፊው ህዝብ ሰቆቃ አይደለም። የየጊዜው የፓለቲካ እንፋሎትና ሆሆታ በሌላ እልቂትና ለቅሶ እየተተካ ሽምድምድ የሃበሻ ፓለቲካ በሃገርም ሆነ በውጭ የስንቱን ቤት እንዳፈረሰና ሰላም እንዳደፈረሰ አሃዛዊ ስሌት አይገልጠውም። ግን አይናችንና ጆሮአችን ይሰማል። እልፎች እርደዋል፤ ሰላማቸው ተነጥቋል!
    ኢትዮጵያዊነት የሚለካው በዘር በተሰፈረ ቁና ሳይሆን እንደ ጣና ሃይቅ በሰፈው ዓለም ውስጥ በሚንሳፈፍ ሚዛን ነው። ነገርን በጭልፋ ይዘው ወራጅ ውሃ አፈለቅን የሚሉን እነዚህ የዘርና የቋንቋ የፓለቲካ ሾተላዪች ቁመንለታል ለሚሉት ህዝብም ቢሆን ያደረጉት ይህ ነው የሚባል አንድም ጠቃሚ ነገር የለም። እንደ ምሳሌ የኤርትራውን ሻቢያን እንዲሁም ሃገር በቀሉን ወያኔን ማየት ብቻ በቂ ይሆናል። ከሰቆቃና ከስደት ሌላ ለምድሪቱና ለሚኖሩባት ምድር ያደረጉት አንድም ነገር የለም። የብልጽግናው መንግስት ከዚህ ተምሮ ራሱን በጊዜ ማሳመርና አፍራሽና አደፍራሽ ነገሮችን ማቆም አለበት። ያ ካልሆነ አፍራሽን አፍራሽ እየተካው ዝንተ ዓለም ከሰቆቃና ከመገዳደል የሚያድነን ምንም ሃይል አይኖርም። እንደሚባለው ሁሉ በእርግጥም በተፈተነ ጊዜ የሚጸና ሰራዊት አንዲት ሃገር ያስፈልጋታል። የአንዲት ሃገር ሰራዊት የህዝብ ልጅ ነው። የመንግስትን ፓሊሲ አለመቀበል በሃገር ሰራዊት ላይ ምንም አይነት ጥላቻና ጥላሸት መቀባት አያስከትልም። የሃገሪቱን ፓሊሲ አስፈጻሚዎችንና መሪዎችን በሃሳብ መሟገት ግን በጎነት ይኖረዋል። መንግስትም ያነጠሰን ሁሉ እያፈሱ ማሰርና መሰወር ነገርን እያከበደ ደርግና ወያኔ በሄድበት የቁልቁለት መንገድ መጓዝ እንጂ ብልህነት ባለመሆኑ ሰው ማሰር፤ ማፈን፤ መግደል እንዲቆም ማድረግ ይኖርበታል። የተካረረ ፓለቲካ ውሉ የጠፋበት በህዋላ ሁሉን የሚጎዳ ዘይቤ ነው። ያም ይሁን ግን አጠፋም፤ አለማም፤ ሞተም፤ ቆመም የሃገሪቱን ሰራዊት አለማድነቅ አይቻልም። ለዪቱቭ የፍራንክ ሽርፍራፊ ተብሎ የሚለጠፈው የውሸትና የፈጠራ ወሬ ሁሉ ሊፈተሽ ይገባዋል እንጂ እንዳለ ሰልቅጦ ማወራራጃ ማጣት ለራስም አይበጅም። የሲሳይ አጌናና የሌሎችም የሲቪል ወገኖቻችን 116ኛው የሰራዊቱ ቀን እውቅና ማግኘታቸው እሰየው ያሰኛል እንጂ አፋፍ ላይ ቆሞ ኡኡታ የሚያሰሙበት ጉዳይ አይደለም። የኢትዮጵያ ሰራዊትም ከእነ ብርታቱና ድካሙ እንኳን ለ 116ኛ የሰራዊቱ ቀን አደረሳችሁ እላለሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule