• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”

October 26, 2023 12:57 am by Editor 1 Comment

“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና  የድል ሠራዊት ” በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው ለዘንድሮ ለ116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን።

እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ የረዥም ዓመታት ሀገርን ከጠላት የመከላከል የተጋድሎ ታሪክ ካላቸው ሀገራት መካከል በጀግኖች ልጆቿ የአይበገሬነት ፊት የምትሠለፍ ታሪካዊት ሀገር ናት።

ከቀደመው ዘመን ጀምረን አሁን ላይ ያለውን እውነታ እንኳ ብንቃኝ ኢትዮጵያ በርካታ የውጪ ወራሪ ሀገራት ያሠፈሠፉባት ጥቂት የማይባሉ የውስጥ እርስ በርስ ግጭቶች የተከሰቱባት በባንዳዎች የተፈተነችበትና  በየትኛውም ዘመን ያልተንበረከከች የወራሪዎችን ፈተና አልፋ ዛሬ ላይ የደረሠች ሥለመሆኗ የታሪክ ድርሳናት መዝግቧል።

በሀገራችን የጀግንነት የታሪክ መዝገብ ያልሠፈሩ ግን ደግሞ አለም ያወቃቸው ቱባ ባህሎችና ድንቅ ታሪኮች ያላት ኢትዮጵያ በታሪክ በሠራዊቷ ኮርታ እንጅ አንድም ጊዜ አፍራ እንደማታውቅ ታሪክ ህያው ምስክር ነው ።

ዛሬ ላይም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ሀገረ ጠል በሆኑ ባንዳዎችና የፀረ ሠላም ሀይሎች ችግሮች ቢከሠቱም ጀግንነት ባህል ልምዱ እና የዘወትር ተግባሩ ባደረገው ሠራዊታችንና ህዝባችን የሠላም እንቅፋቶችን ፈተና ተቋቁማ ሀገራችን በልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች።

በመሆኑም በየትኛውም ጊዜ እና በማንኛውም ቦታ ለሠራዊታችን ብርታት ሞራልና የጀርባ አጥንት ከሆነው ህዝባችን ጋር ሆነን ሠላማችንን እያሥቀጠልን እንገኛለን።

116ኛው የመከላከያ ሠራዊት ቀንም ይበልጥ ቃላችንን የምናደስበት በየዘመናቱ ለሀገራችን ሉዓላዊነት ሲሉ መስዋዕት የከፈሉ ጀግኖችን የምንዘክርበትና ከመላው ህዝባችን ጋር ሆነን ለሀገራችን ሠላምና ልማት ማበብ በጋራ የምንቆምበት  ዕለት ጭምር ነው።

እናም እንደ መሪ ቃላችን በተፈተን ጊዜ ሁሉ ፀንተን የድል ሠራዊት ሆነን ዛሬ ላይ እንደደረሥነው ቀጣይም ከመላው ህዝባችን ጋር ለሀገራችን መክፈል ያለብንን ሁሉ ዋጋ  በመክፈል የኢትዮጵያን ሠላም እና ዕድገት አፅንተን እናሥቀጥላለን ።

“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”

ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: 116 anniversary of endf, endf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 26, 2023 01:04 pm at 1:04 pm

    በሃበሻ ፓለቲካ በራስ አስቦ የራስን ሃሳብ ለሌሎች ማካፈል ከመ አሪዎስ ተብሎ ከተወገዘ ዘመን አለፈ። ይኸው አሁን እውቁ ጋዘጠኛ ሲሳይ አጌና ላይ የሚለጠፉ ወልጋዳ ሃሳቦችን ለሰማና ላነበበ የሃበሻው ፓለቲካ የጅምላ ህሳቤን የተላበሰ እንጂ በራስ መቆም የማይቻል መሆኑን ያሳያል። በብዙ መከራ ውስጥ ያለፈው ይህ ምጡቅ ጋዜጠኛ የኢትዮጵያን ሰራዊት ጥንካሬና አንድነት ከሃገሪቱ ልዕልና እና ቀጣይነት ጋር አጣምሮ በማየቱ በዚህም በዚያም ይዘለፋል። ይህ በየወንዙ የሚማማለው የሃበሻ ፓለቲካ የአስረሽ ምቺው ስልት ስለሚከተል ከትላንቱ የሚማር ሳይሆን ለዛሬ ብቻ ኑሮ ዛሬ ላይ የሚከስም ነው። ያለፈ ታሪካችንም የሚያሳየው ይህኑ ነው።
    የኢትዪጵያ ወታደሮች ያኔም ሆነ አሁን የውስጥና የውጭ ጠላትን የተፋለሙት መጭው ትውልድ በሰላምና በደስታ እንዲኖር ነበረ። ያ ግን ሆኖ አያውቅም። የሰው ተንኮል ከመንግስታት ሸፍጥ ጋር እየተላበደ ህዝባችን እየከፋፈለ ዛሬ ላለንበት እኛ ብቻ እንኑር ፓለቲካ አሽጋግሮናል። እንደ ሃምሌ ዝናብ የማይቆመው ይህ የህዝባችን ሰቆቃ ምንጩ እኛም መንግስትም ነው። ሲጀመር ለሰላም ቆመናል የሚሉ ሃይሎች ሁሉ በተንኮልና በሸር የተነከሩ በመሆናቸው የሚታያቸው የእነርሱ መኖር እንጂ የሰፊው ህዝብ ሰቆቃ አይደለም። የየጊዜው የፓለቲካ እንፋሎትና ሆሆታ በሌላ እልቂትና ለቅሶ እየተተካ ሽምድምድ የሃበሻ ፓለቲካ በሃገርም ሆነ በውጭ የስንቱን ቤት እንዳፈረሰና ሰላም እንዳደፈረሰ አሃዛዊ ስሌት አይገልጠውም። ግን አይናችንና ጆሮአችን ይሰማል። እልፎች እርደዋል፤ ሰላማቸው ተነጥቋል!
    ኢትዮጵያዊነት የሚለካው በዘር በተሰፈረ ቁና ሳይሆን እንደ ጣና ሃይቅ በሰፈው ዓለም ውስጥ በሚንሳፈፍ ሚዛን ነው። ነገርን በጭልፋ ይዘው ወራጅ ውሃ አፈለቅን የሚሉን እነዚህ የዘርና የቋንቋ የፓለቲካ ሾተላዪች ቁመንለታል ለሚሉት ህዝብም ቢሆን ያደረጉት ይህ ነው የሚባል አንድም ጠቃሚ ነገር የለም። እንደ ምሳሌ የኤርትራውን ሻቢያን እንዲሁም ሃገር በቀሉን ወያኔን ማየት ብቻ በቂ ይሆናል። ከሰቆቃና ከስደት ሌላ ለምድሪቱና ለሚኖሩባት ምድር ያደረጉት አንድም ነገር የለም። የብልጽግናው መንግስት ከዚህ ተምሮ ራሱን በጊዜ ማሳመርና አፍራሽና አደፍራሽ ነገሮችን ማቆም አለበት። ያ ካልሆነ አፍራሽን አፍራሽ እየተካው ዝንተ ዓለም ከሰቆቃና ከመገዳደል የሚያድነን ምንም ሃይል አይኖርም። እንደሚባለው ሁሉ በእርግጥም በተፈተነ ጊዜ የሚጸና ሰራዊት አንዲት ሃገር ያስፈልጋታል። የአንዲት ሃገር ሰራዊት የህዝብ ልጅ ነው። የመንግስትን ፓሊሲ አለመቀበል በሃገር ሰራዊት ላይ ምንም አይነት ጥላቻና ጥላሸት መቀባት አያስከትልም። የሃገሪቱን ፓሊሲ አስፈጻሚዎችንና መሪዎችን በሃሳብ መሟገት ግን በጎነት ይኖረዋል። መንግስትም ያነጠሰን ሁሉ እያፈሱ ማሰርና መሰወር ነገርን እያከበደ ደርግና ወያኔ በሄድበት የቁልቁለት መንገድ መጓዝ እንጂ ብልህነት ባለመሆኑ ሰው ማሰር፤ ማፈን፤ መግደል እንዲቆም ማድረግ ይኖርበታል። የተካረረ ፓለቲካ ውሉ የጠፋበት በህዋላ ሁሉን የሚጎዳ ዘይቤ ነው። ያም ይሁን ግን አጠፋም፤ አለማም፤ ሞተም፤ ቆመም የሃገሪቱን ሰራዊት አለማድነቅ አይቻልም። ለዪቱቭ የፍራንክ ሽርፍራፊ ተብሎ የሚለጠፈው የውሸትና የፈጠራ ወሬ ሁሉ ሊፈተሽ ይገባዋል እንጂ እንዳለ ሰልቅጦ ማወራራጃ ማጣት ለራስም አይበጅም። የሲሳይ አጌናና የሌሎችም የሲቪል ወገኖቻችን 116ኛው የሰራዊቱ ቀን እውቅና ማግኘታቸው እሰየው ያሰኛል እንጂ አፋፍ ላይ ቆሞ ኡኡታ የሚያሰሙበት ጉዳይ አይደለም። የኢትዮጵያ ሰራዊትም ከእነ ብርታቱና ድካሙ እንኳን ለ 116ኛ የሰራዊቱ ቀን አደረሳችሁ እላለሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule