የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የምልምል ሰልጣኞች የስልጠና መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል። ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ በሥልጠና መክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ሥልጠናው መጀመሩን በይፋ ያበሰሩት በሰላም ማሰከበር ማዕከል የኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አዛዥ ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ መከላከያ ወድ ህይወቱን ሳይሰስት የሚሰጠውን ሃገራዊ ተልዕኮ በስኬት የሚፈፅም የሀገር ኩራት መሆኑን አንስተዋል። ውትድርና ሀገር ወዳድ የሆነ ኢትዮጵያዊ ለሃገር ዘብ እቆማለሁ ብሎ በፍላጎት በተነሳሽነት በቁርጠኝነት እና በታማኝነት አገልግሎት የሚሰጥበት የሚያኮራ ሙያ መሆኑንም አዛዡ ገልፀዋል፡፡ ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ከመላው የሃገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ተመልምለው መመልመያ መሥፈርቱን አሟልተው የመጡ አዲስ ወጣቶችን እያሠለጠነ የሚያበቃ ነውና … [Read more...] about በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ
hurso contingent training center
የሁርሶ ሠልጣኞች በብቃት እየተዘጋጁ ነው
"ሀገርን ለማዳን እዘምታለሁ የትም መቼም በምንም" በሚል መሪ ቃል ፀረ ሰላም ሀይሎችን ለመፋለም ቆርጠው የተነሱ የቁርጥ ቀን ልጆች በሀገሪቷ በሚገኙ የውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶች በመግባት ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡ የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ከዚህ ቀደም በርካታ የሰራዊት አባላትን በሁለት ዙሮች አሰልጥኖ ያስመረቀ ሲሆን÷ በአሁኑ ጊዜም የ3ኛ ዙር ሰልጣኞችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ አሰልጣኝ የ22ኛ ሻለቃ ዘመቻ ሀላፊ መቶ አለቃ ዲኔ መሀመድ የዚህ ዙር ሰልጣኞች ከሁለቱ ዙር ሰልጣኞች ለየት የሚያደርገው ሀገርን ለማፈራረስ የተነሱት የሀገር ሀዲዎች የህወሓት እና የሸኔ የሽብር ቡድኖችን ለመፋለምና ሀገርን ከመፈራረስ ታድጎ አንድነቷን ለማስቀጠል ለሀገሬ እዘምታለሁ በማለት ሀገራዊ ጥሪውን ተቀብለው ወደ ስልጠናው የተካተቱ መሆናቸው ነው … [Read more...] about የሁርሶ ሠልጣኞች በብቃት እየተዘጋጁ ነው


