* “ዓለም እያዘነብን እየሳቀብን ነው አንድ እንሁን” - ዘመነ ካሤ አርበኛ ዘመነ ካሴ “ዓለም እያዘነብንም እየሳቀብንም ነው” በማለት “መተው ነገሬን ከተተው" እንደሚባለው በመተው "አንድ እንሁን" የሚል ጥሪ አሰማ። ፋኖ ኢትዮጵያን ሠርቶ ምስራቅ አፍሪካን ያረጋጋል ብሏል፤ አንድነት ለመፍጠር “አንድ ማንኪያ ቅንነት” ነው የሚያስፈልገው አለ። በጎጃም እና በደቡብ ጎንደር የተሰማራው የአገር መከላከያ በበኩሉ ስም፣ ቦታና ኃላፊነት ጠቅሶ በፋኖ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን አስታውቋል። የዘመነ መልዕክት የተሰራጨው የመከላከያ መረጃዎች እኩል ቀን ነሐሴ 16 በሪፖርት መልክ ይፋ ከሆነ በኋላ ነው። "የዕለቱ መልዕክት" በሚል የአማራ ፋኖ በጎጃም መሪ ዘመነ ካሴ "በቃ መተው እንልመድ" ሲል የተለያዩትን የፋኖ አመራሮችና አደረጃጀቶች ዘርዝሮ " ... አንድ መሆን አለበት" … [Read more...] about መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ
Zemene Kassie
የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ
የእስክንድር አፋሕድ ጥሪ አቀረበ ለበርካታ ወራት ኅብረት ለመፍጠር ታስቦ ሲሠራበት የቆየው የአማራ ፋኖ ኅብረት በቋራ ጎንደር መመሥረቱ ተሰምቷል። የኅብረቱ ዓላማና ግብ ወደ አንድነትን ለማምጣትና የተቀናጀ ጥቃት ለመሰንዘር ሳይሆን ዓቅምን አስተባብሮ ለድርድር ለመቅረብ የታለመ እንደሆነ እየተነገረ ነው። እስክንድር ነጋ የሚመራው አፋሕድ ባወጣው መግለጫ “ከተቻለ እንዋሃድ፣ ካልሆነም አንቀናጅ ካልሆነ ቢያንስ እናበብ” ብሏል። ከጎንደር፣ ከሸዋ፣ ከወሎና ከጎጃም የተሰባሰቡ የፋኖ አመራሮች ባደረጉት ውይይት አንድ የፋኖ አደረጃጀት መመሥረታቸውን ተናግረዋል። ስሙንም አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በማለት መሰየማቸውን አስታውቀዋል። የወጣው መግለጫ እንደሚለው “የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ - አማራ)፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና የአማራ ፋኖ … [Read more...] about የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ
ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ
* ሸኔም ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል በሁሉም የጎጃም ዞኖች እና በደቡብ ጎንደር የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት ክፍሎች በፋኖ ላይ በወሰዱት እርምጃ አመራሮችን ጨምሮ በርካታዎችን መግደላቸው፣ መማረካቸው እንዲሁም መሥሪያዎችንና ተተኳሾችን መማረካቸውን የመከላከያ ሠራዊት በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል። በሸኔም ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በ6ኛ ዕዝ የኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጋዲሳ ዲሮን ጠቅሶ፤ በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ በፅንፈኛው እና አሸባሪው ሸኔ ላይ የምንወስደውን እርምጃ አጠናክረን ቀጥለናል አመርቂ ውጤትም ተገኝቷል ይላል የወጣው መረጃ። ከዚህም በተጨማሪ ኮሎኔል ጋዲሳ ዲሮ ሰሞኑን በፅንፈኛ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ እርምጃ በመውሰድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሣራ ማድረስ ተችሏል ማለታቸውን ዘግቧል። በፋኖ ላይ የደረሰውን በተመለከተ፤ መረጃው የምስራቅ ዕዝ ዘመቻ መምሪያ … [Read more...] about ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ
ጀብደኛው
አንድ ሽማግሌ የነገሩኝ ታሪክ ትዝ አለኝ። ሰውዬው ጀግና ነኝ፣ አንበሳ በጡጫ ነብርን በእርግጫ እገላለሁ እያለ ይጎርራል። በኋላ ራሱ ደጋግሞ ያወራውን ጉራ እውነት ነው ብሎ ራሱ አመነው። አምኖም አልቀረ በጉራው የተሳቡ፣ በወሬው የተሰባሰቡ፣ አድናቂዎቹን አስከትሎ በረሃ ወረደ። እሱ ጀብድ ሊሠራ ሌላው ጀብድ ሊያወራ፣ ምን ለምን አብረው አዘገሙ። አድናቂዎቹን ከፍ ያለ ኮረብታ ላይ አስቀመጠና "ዛሬ ሶምሶንን በዓይናችሁ ታያላችሁ" አላቸው። እነርሱም አድንቀውና አዳምቀው እንዴት እንደሚያወሩት እያሰቡ ወደ አንበሳ መንጋ የሚወርደውን ጀብደኛ በማዶ ይመለከቱ ያዙ። ወረደ ጀብደኛው። አንበሶች ሰብሰብ ብለው ተኝተዋል። በሩቁ ድንጋይ ወረወረባቸው። ሁሉም አንበሶች ቀና ቀና አሉ። አንዱ በድንጋይ የተመታ ደቦል ዘሎ ወጣበትና በቅጽበት ሌሎች ገነጣጠሉት። ታሪኩም ከጄት ፈጥኖ ከውኃ ቀጥኖ … [Read more...] about ጀብደኛው




