• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ

May 6, 2025 10:40 pm by Editor Leave a Comment

* ሸኔም ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል

በሁሉም የጎጃም ዞኖች እና በደቡብ ጎንደር የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት ክፍሎች በፋኖ ላይ በወሰዱት እርምጃ አመራሮችን ጨምሮ በርካታዎችን መግደላቸው፣ መማረካቸው እንዲሁም መሥሪያዎችንና ተተኳሾችን መማረካቸውን የመከላከያ ሠራዊት በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል። በሸኔም ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በ6ኛ ዕዝ የኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጋዲሳ ዲሮን ጠቅሶ፤ ‎በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ በፅንፈኛው እና አሸባሪው ሸኔ ላይ የምንወስደውን እርምጃ አጠናክረን ቀጥለናል አመርቂ ውጤትም ተገኝቷል ይላል የወጣው መረጃ። ከዚህም በተጨማሪ ኮሎኔል ጋዲሳ ዲሮ ሰሞኑን በፅንፈኛ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ እርምጃ በመውሰድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሣራ ማድረስ ተችሏል ማለታቸውን ዘግቧል።

በፋኖ ላይ የደረሰውን በተመለከተ፤ መረጃው የምስራቅ ዕዝ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ተሾመ አስማማውን ጠቅሶ ሲናገር፤ “የሠራዊታችን ክፍሎች በተሰማሩባቸው ቀጣናዎች የኅብረተሰቡ የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎልና የተጀመሩ መሠረተ-ልማቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማስቻል ፅንፈኛውን የማጥፋት ተልዕኮ” ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።

  • ኮሎኔል ተሾመ አስማማው

ድል የተገኘባቸው አካባቢዎች 

  • በሰሜን ጎጃም ዞን
    • ይልማና ደንሳ ወረዳ
      • ደብረማዊ፣ ሰንቀኛ አዜት፣ ቆቀርና በዜት አብካ ቀበሌዎች
  • በምስራቅ ጎጃም ዞን
    • በሸበል በረንታ ወረዳ
      • ቁጥቋጥና ኪርኩበት ቀበሌ
  • በምዕራብ ጎጃም ዞን
    • በደጋዳሞት ወረዳ
      • ፈላጢት፣ ቋቁቻና ቡና ቀበሌ
    • በአዊ ዞን ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ
      • አሸፋና አጉት ቀበሌ
  • በደቡብ ጎንደር ዞን
    • ሰዴ ሙጃ ወረዳ
      • አዳዲና ወለል ባህር ቀበሌዎች
    • ፎገራ ወረዳ
      • መነጉዘር ቀበሌዎች ላይ የተሰማሩት አሀዱዎችም አመርቂ ግዳጆችን አስመዝግበዋል ብሏል።

መረጃው እርምጃ የተወሰደባቸውን አመራሮች በሚከተለው መልኩ አቅርቧል፤

  • በፅንፈኞች አደረጃጀት የፅንፈኛው ሻለቃ መሪ ፈንታው ሽታው
  • የአገው ምድር ዘመቻ አስተባባሪ ሰለሞን
  • የዘንገና ብርጌድ አዛዥ ፅጋይ አጥናፉ
  • የፅንፈኛው ቡድን ሎጂስቲክስ ኃላፊ መንጌ ይርዳው 
  • የአፄ ፋሲል ተወርዋሪ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ የነበረ ዳንኤል አሰፋ
  • እንዲሁም ሌሎች በርካታ የጽንፈኛው አመራሮች እና አባላቶች ተደምስሰዋል።

በአጠቃላይ የደረሰውን ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሣራ የመከላከያ ሠራዊት መረጃ በሚከተለው መልኩ በዝርዝር አስታውቋል፤ በዚህ ዘመቻ

  • 95 የፅንፈኛውን ኃይል አባላት ሲደመሰሱ
  • 29 ቆስለዋል
  • 2 ተማርከዋል
  • 2ሺህ 354 ልዩ ልዩ ተተኳሽ
  • 15 ኤ ኬ ኤም
  • 36 ኋላ ቀር መሳሪያ
  • ሶስት ቦምብ
  • ስምንት ትጥቅ
  • ስድስት የኤ ኬ ኤም ካዝና
  • አንድ ጄኔሬተርና ሶስት ተሸከርካሪ በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ 50 አባላቱም እጅ ሰጥተዋል።

በአሁኑ ጊዜ በተበታተነ አደረጃጀት ላይ የሚገኘው የፋኖ ሁኔታ ወደ ማኅበራዊ ሽፍታነት እየተቀየረ መምጣቱ ይነገራል። በተለይ በሕዝብ ላይ የሚያደርሰው ግፍ ማኅበረሰቡን ለከፍተኛ ችግር የጋረጠው በመሆኑ መከላከያ በሚወስደው እርምጃ ላይ የየአካባቢው ሕዝብ በንቃት እየተሳተፈ እንደሆነ በስፋት ይነገራል። በዚህ በሁሉም የጎጃም ዞኖች እና በደቡብ ጎንደር ለተገኘውም ድል የኅብረተሰቡ ከሠራዊቱ ጎን መሰለፍ እንደ ማስረጃ የሚጠቀስ ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Amhara Fano, Eskinder Nega, olf shanee, Shene, Zemene Kassie

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule