• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ

May 14, 2025 11:07 pm by Editor Leave a Comment

  • የእስክንድር አፋሕድ ጥሪ አቀረበ

ለበርካታ ወራት ኅብረት ለመፍጠር ታስቦ ሲሠራበት የቆየው የአማራ ፋኖ ኅብረት በቋራ ጎንደር መመሥረቱ ተሰምቷል። የኅብረቱ ዓላማና ግብ ወደ አንድነትን ለማምጣትና የተቀናጀ ጥቃት ለመሰንዘር ሳይሆን ዓቅምን አስተባብሮ ለድርድር ለመቅረብ የታለመ እንደሆነ እየተነገረ ነው። እስክንድር ነጋ የሚመራው አፋሕድ ባወጣው መግለጫ “ከተቻለ እንዋሃድ፣ ካልሆነም አንቀናጅ ካልሆነ ቢያንስ እናበብ” ብሏል።

ከጎንደር፣ ከሸዋ፣ ከወሎና ከጎጃም የተሰባሰቡ የፋኖ አመራሮች ባደረጉት ውይይት አንድ የፋኖ አደረጃጀት መመሥረታቸውን ተናግረዋል። ስሙንም አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በማለት መሰየማቸውን አስታውቀዋል።

የወጣው መግለጫ እንደሚለው “የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ – አማራ)፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና የአማራ ፋኖ በሸዋ ከፍተኛ አመራሮች በጋራ ቋራ-ጎንደር ባደረጉት ቀናትን የወሰደ መስራች ጉባኤ ዛሬ ግንቦት 01 ቀን 2017 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (Amhara Fano National Force) የተሰኘ ድርጅት” መመሥረታቸውን ይፋ አድርጓል።

አወቃቀሩን በተመለከተም፤ “የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል አወቃቀር ጠቅላላ ጉባኤ፣ ማዕከላዊ ምክር ቤት፣ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንዲሁም የአባት አርበኞች ምክር ቤትን አካቶ ሕገ ደንብ በማፅደቅ ተቋቁሟል። የአባት አርበኞች ምክር ቤትን አርበኛ መሳፍንት ተስፉ እንዲመሩት መሥራች ድርጅቶቹ” መስማማታቸውን መግለጫው አስረድቷል።

አዲሱ የፋኖ ኅብረት ትህነግ ይመራበት የነበረውን ዓይነት የጋራ አመራር መርህ የሚከተል መሆኑን በመግለጫው የጠቀሰው መግለጫ ለተግባራዊነቱም 13 መሪዎች ያሉበት የድርጅቱን “ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ የዲፕሎማሲ እና የአስተዳደር ሥራዎች” የሚመራ “ማዕከላዊ ኮማንድ” መመሥረቱን አስታውቋል።

ይህ በ13 መሪዎች የሚመራው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ፤

“1ኛ. አርበኛ ዘመነ ካሴ

2ኛ. አርበኛ ሐብቴ ወልዴ

3ኛ. አርበኛ ምሬ ወዳጆ

4ኛ. አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ

5ኛ. አርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ

6ኛ. አርበኛ ሔኖክ አዲሴ

7ኛ. ጀነራል ተፈራ ማሞ

8ኛ. አርበኛ ዝናቡ ልንገረው

9ኛ. አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ

10ኛ. አርበኛ አስቻለው በለጠ

11ኛ. አርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል

12ኛ. አርበኛ ማርከው መንግሥቴ

13ኛ. አርበኛ አከበር ስመኘው”

ከሥነአስተዳደር መርህ እና በተለይ ጥቅብ የዕዝ ሠንሠለትን መከተል ከሚያስገድደው ወታደራዊ አወቃቀር አኳያ በ13 መሪዎች የሚመራ ድርጅት ተቋማዊ ቁመና ይዞ ለመቀጠል እጅግ እንደሚከብደው አስተያየት ሲሰጥ ተሰምቷል።

ከዚህ ሌላ ግን የፋኖው ኅብረት የተመሠረተው በመንግሥት ላይ ወታደራዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫና ለማሳደር ሳይሆን ዋንኛው ዓላማ ድርድር በሚካሄድበት ጊዜ ወንበር ለማግኘት እንደሆነ የፋኖን አካሄድ በቅርብ የሚከታተሉ ለጎልጉል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በተለይ እስክንድር የሚመራውና አፋሕድ ተብሎ የሚጠራው አደረጃጀት ኅብረት በመፍጠር የቀዳሚነቱን ሥፍራ በመያዙ ለድርድር ጥሩ ወንበር እያመቻቸ እንደሆነ ሲነገር የቆየ ሁኔታ ነው። በቅርብ በማኅበራዊ ሚዲያ በተሰራጨ ድምፅ እስክንድር ወደ ኤርትራ አንድ የድርጅቱን ከፍተኛ ኃላፊ መላኩን እና ከሻዕቢያ ጋር በመነጋገር አስመራ ላይ ቢሮ እንዲከፈትለት ሲጠይቅ ተሰምቷል።

በዚህ የድምፅ መረጃ መሠረት እስክንድር ቢሮ እንዲከፈትለት፣ ኮማንዶ እንዲሰለጥልለት እና ከባድ መሣሪያ ተኳሽ የጠየቀ ሲሆን በምትኩ አሰብን እንደማይጠይቅ እንዲያውም የኤርትራ ሉዓላዊ ግዛት እንደሆነ ተናግሯል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ግን አሁን ካለው የተበታተነ የፋኖ አደረጃጀት እርሱ የሚመራው የተሻለ ቁመና ላይ የሚገኝ፣ ለማንኛውም ጉዳይ የተሰባሰበ መሆኑን በመግለጽ የተናገረው እነ ዘመነ የሚመሩት የተበታተነውን ፋኖ በእጅጉ ያሳሰበና ያስቆጣ ሆኗል።

ከጥቂት ወራት በፊት “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” በማለት ከእስክንድር ጋር አብሮ የሚሠራው አበበ ጢሞ ማስታወቁን ጎልጉል ዘግቦ ነበር።

የእስክንድር የመቅደም አካሄድ የገባቸው የእነ ዘመነ ቡድን ቢሮ በመክፈትም ሆነ ለድርድር ራሳቸውን በማዘጋጀት ወደኋላ መቅረታቸው በመገንዘብ በአፋጣኝ ኅብረት በመፍጠር ለድርድር ራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ስምምነት ላይ በመድረሳቸው አሁን የመሠረቱትን በ13 ሰዎች የሚመራ የፋኖ አደረጃጀት ለመመሥረት በቅተዋል። በዚህ ሁኔታ በቀጣይ ከመንግሥት ጋር በሚደረጉ ድርድሮች ከተቻለ ከእስክንድር ፋኖ ጋር ካልሆነም ራሱን ወክሎ አዲሱ የፋኖ አደረጃጀት ለመቅረብ እየተንደረደ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርብ ከሚከታተሉ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

ከዚህ በተጨማሪ በቅርቡ በአማራ ክልል የተካሄደው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በውጊያ ላይ ከሚገኙት የፋኖ አደረጃጀቶች አንዱ ጋር የተነጋገረ መሆኑ ገልጾ ነበር። ይህም የእስክንድር ፋኖ እንደሆነ በሰፊው የሚታመንበት ሲሆን በዚህም ረገድ እስክንድር ቀዳሚ ሆኖ መገኘቱ የእነ ዘመነን ቡድን የመቀደም መንፈስ ውስጥ እንዳስገባቸው ጫካ ከገቡትም ጭምር ሲነገር ተሰምቷል።

“ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው” በሚል ርዕስ ባጋራነው የዜና ዘገባ ከጦርነት በስተቀር ሁሉንም አማራጭ የተጠቀመው ሻዕቢያ ኢትዮጵያ ላይ ያቀደው ባለመሳካቱ መጨረሻው እና አይቀሬው አማራጭ ዲፕሎማሲና ድርድር እንደሆነ በግምገማው ያመነበት ጉዳይ ነው። የእነ ዘመነ ካሤን ቡድን በሁሉም መስክ የሚያግዘው ሻዕቢያ ዕገዛውን አጠናክሮ መቀጠል ባለመቻሉ ድርድርን ጊዜ መግዣ ወይም እጅ መስጫ አድርጎ አቅርቧል።

መሪ ዓልባው የእነ ዘመነም ቡድን ገና አንድ ሳምንት እንኳን ሳይሞላው ተጠናክሮ ከመሥራት ይልቅ የመፍረስ ወይም የመበታተን አደጋ ውስጥ እንዳለ አፈትልከው የሚወጡ የድምፅ መረጃዎች ይጠቁማሉ። በተለይ ዘመነ የአዲሱ ፋኖ አደረጃጀት መሪ ሆኖ ባለመውጣቱ “በጎንደሬ አንመራም” የሚሉ ድምፆች የተሰሙ ሲሆን ካስፈለገም “ባሕር ዳርን ይዘን እንገነጠላለን” እንጂ ጎጃም ካልመራ በፍጹም በስብስቡ አንቀጥልም ያሉም አሉ።

ባለፈው ወር በአማራ ክልል ከሚገኙ 263 ወረዳዎች በሙሉ የተመረጡ ከ4,500 በላይ ከ10 የማኅበረሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ተወካዮች በሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ልየታ ላይ በመሳተፍ የክልሉን ሕዝብ አንኳር አጀንዳዎች ማቅረባቸው ይታወሳል። በዚህ ወቅት የምክክር ኮሚሺኑ ኃላፊዎች እንደተናገሩት ከፋኖ ታጣቂዎች አንዱ ስብስብ ጋር መነጋገራቸውና የትኛው እንደሆነ ለመግለጽ እንደማይችሉ በመናገር በጠቃሚ ጉዳዮች መምከራቸውን አስታውቀዋል። በብዙዎች ዘንድ እንደሚታመነው ይህ የእስክንድር አፋሕድ እንደሆነ የታመነ ነው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ አፋሕድ አዲስ የተመሠረተውን የፋኖ አደረጃጀት ዜና በደስታ የተቀበለው መሆኑ ገልጾዋል። “ለአንድ ዓመት ጥቂት በቀረው የድርጅታችን ዕድሜ የነበረውን ሂደት ስንገመግም፣ ብዙ ውጣ ዉረድ እንደነበረው የምናስታውሰው ነው። ይህም ያስተማረን አንድ ነገር ቢኖር፣ የሁለት ድርጅቶች መመሥረት ስኬት የሚሆነው፣ ሁለቱ ድርጅቶች ከተቻለ በተዋሃደ፣ ካልሆነም በተቀናጀ፣ ይህም ካልሆነ ቢያንስ ቢያንስ በተናበበ አካሄድ ትግሉን ሲመሩት ብቻ መሆኑን ነው” በማለት በተለይ እኛ ከተመሠረትን “አንድ ዓመት” ሊሞላን ነው የሚለውን በመጥቀስ አሁን ከተመሠረተው የፋኖ ኅብረት አፋሕድ ቀዳሚነት እንዳለው ጠቅሷል።

ከዚህና ከሌሎች ጉዳዮች አንጻር ሲታይ፤ አዲስ የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ወደ ድርድር በሚደረገው ጉዞ የበይ ተመልካች ከመሆን ለመዳንና በድርድር ጠረጴዛው ላይ አንዲትም ብትሆን ወንበር ለማግኘት አስቦ የተመሠረተ ነው ለማለት ይቻላል። ጎልጉል ያነጋገራቸው በትግሉ ውስጥ ያሉትም ሆነ ከትግሉ ውጪ ያሉ የፋኖን አካሄድ የሚከታተሉ የሚናገሩት ይህንኑ የሚያጸና ነው።    

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: Amhara Fano, Amhara Fano National Force, Zemene Kassie

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule