• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ

May 14, 2025 11:07 pm by Editor Leave a Comment

  • የእስክንድር አፋሕድ ጥሪ አቀረበ

ለበርካታ ወራት ኅብረት ለመፍጠር ታስቦ ሲሠራበት የቆየው የአማራ ፋኖ ኅብረት በቋራ ጎንደር መመሥረቱ ተሰምቷል። የኅብረቱ ዓላማና ግብ ወደ አንድነትን ለማምጣትና የተቀናጀ ጥቃት ለመሰንዘር ሳይሆን ዓቅምን አስተባብሮ ለድርድር ለመቅረብ የታለመ እንደሆነ እየተነገረ ነው። እስክንድር ነጋ የሚመራው አፋሕድ ባወጣው መግለጫ “ከተቻለ እንዋሃድ፣ ካልሆነም አንቀናጅ ካልሆነ ቢያንስ እናበብ” ብሏል።

ከጎንደር፣ ከሸዋ፣ ከወሎና ከጎጃም የተሰባሰቡ የፋኖ አመራሮች ባደረጉት ውይይት አንድ የፋኖ አደረጃጀት መመሥረታቸውን ተናግረዋል። ስሙንም አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በማለት መሰየማቸውን አስታውቀዋል።

የወጣው መግለጫ እንደሚለው “የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ – አማራ)፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና የአማራ ፋኖ በሸዋ ከፍተኛ አመራሮች በጋራ ቋራ-ጎንደር ባደረጉት ቀናትን የወሰደ መስራች ጉባኤ ዛሬ ግንቦት 01 ቀን 2017 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (Amhara Fano National Force) የተሰኘ ድርጅት” መመሥረታቸውን ይፋ አድርጓል።

አወቃቀሩን በተመለከተም፤ “የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል አወቃቀር ጠቅላላ ጉባኤ፣ ማዕከላዊ ምክር ቤት፣ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንዲሁም የአባት አርበኞች ምክር ቤትን አካቶ ሕገ ደንብ በማፅደቅ ተቋቁሟል። የአባት አርበኞች ምክር ቤትን አርበኛ መሳፍንት ተስፉ እንዲመሩት መሥራች ድርጅቶቹ” መስማማታቸውን መግለጫው አስረድቷል።

አዲሱ የፋኖ ኅብረት ትህነግ ይመራበት የነበረውን ዓይነት የጋራ አመራር መርህ የሚከተል መሆኑን በመግለጫው የጠቀሰው መግለጫ ለተግባራዊነቱም 13 መሪዎች ያሉበት የድርጅቱን “ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ የዲፕሎማሲ እና የአስተዳደር ሥራዎች” የሚመራ “ማዕከላዊ ኮማንድ” መመሥረቱን አስታውቋል።

ይህ በ13 መሪዎች የሚመራው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ፤

“1ኛ. አርበኛ ዘመነ ካሴ

2ኛ. አርበኛ ሐብቴ ወልዴ

3ኛ. አርበኛ ምሬ ወዳጆ

4ኛ. አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ

5ኛ. አርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ

6ኛ. አርበኛ ሔኖክ አዲሴ

7ኛ. ጀነራል ተፈራ ማሞ

8ኛ. አርበኛ ዝናቡ ልንገረው

9ኛ. አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ

10ኛ. አርበኛ አስቻለው በለጠ

11ኛ. አርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል

12ኛ. አርበኛ ማርከው መንግሥቴ

13ኛ. አርበኛ አከበር ስመኘው”

ከሥነአስተዳደር መርህ እና በተለይ ጥቅብ የዕዝ ሠንሠለትን መከተል ከሚያስገድደው ወታደራዊ አወቃቀር አኳያ በ13 መሪዎች የሚመራ ድርጅት ተቋማዊ ቁመና ይዞ ለመቀጠል እጅግ እንደሚከብደው አስተያየት ሲሰጥ ተሰምቷል።

ከዚህ ሌላ ግን የፋኖው ኅብረት የተመሠረተው በመንግሥት ላይ ወታደራዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫና ለማሳደር ሳይሆን ዋንኛው ዓላማ ድርድር በሚካሄድበት ጊዜ ወንበር ለማግኘት እንደሆነ የፋኖን አካሄድ በቅርብ የሚከታተሉ ለጎልጉል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በተለይ እስክንድር የሚመራውና አፋሕድ ተብሎ የሚጠራው አደረጃጀት ኅብረት በመፍጠር የቀዳሚነቱን ሥፍራ በመያዙ ለድርድር ጥሩ ወንበር እያመቻቸ እንደሆነ ሲነገር የቆየ ሁኔታ ነው። በቅርብ በማኅበራዊ ሚዲያ በተሰራጨ ድምፅ እስክንድር ወደ ኤርትራ አንድ የድርጅቱን ከፍተኛ ኃላፊ መላኩን እና ከሻዕቢያ ጋር በመነጋገር አስመራ ላይ ቢሮ እንዲከፈትለት ሲጠይቅ ተሰምቷል።

በዚህ የድምፅ መረጃ መሠረት እስክንድር ቢሮ እንዲከፈትለት፣ ኮማንዶ እንዲሰለጥልለት እና ከባድ መሣሪያ ተኳሽ የጠየቀ ሲሆን በምትኩ አሰብን እንደማይጠይቅ እንዲያውም የኤርትራ ሉዓላዊ ግዛት እንደሆነ ተናግሯል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ግን አሁን ካለው የተበታተነ የፋኖ አደረጃጀት እርሱ የሚመራው የተሻለ ቁመና ላይ የሚገኝ፣ ለማንኛውም ጉዳይ የተሰባሰበ መሆኑን በመግለጽ የተናገረው እነ ዘመነ የሚመሩት የተበታተነውን ፋኖ በእጅጉ ያሳሰበና ያስቆጣ ሆኗል።

ከጥቂት ወራት በፊት “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” በማለት ከእስክንድር ጋር አብሮ የሚሠራው አበበ ጢሞ ማስታወቁን ጎልጉል ዘግቦ ነበር።

የእስክንድር የመቅደም አካሄድ የገባቸው የእነ ዘመነ ቡድን ቢሮ በመክፈትም ሆነ ለድርድር ራሳቸውን በማዘጋጀት ወደኋላ መቅረታቸው በመገንዘብ በአፋጣኝ ኅብረት በመፍጠር ለድርድር ራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ስምምነት ላይ በመድረሳቸው አሁን የመሠረቱትን በ13 ሰዎች የሚመራ የፋኖ አደረጃጀት ለመመሥረት በቅተዋል። በዚህ ሁኔታ በቀጣይ ከመንግሥት ጋር በሚደረጉ ድርድሮች ከተቻለ ከእስክንድር ፋኖ ጋር ካልሆነም ራሱን ወክሎ አዲሱ የፋኖ አደረጃጀት ለመቅረብ እየተንደረደ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርብ ከሚከታተሉ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

ከዚህ በተጨማሪ በቅርቡ በአማራ ክልል የተካሄደው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በውጊያ ላይ ከሚገኙት የፋኖ አደረጃጀቶች አንዱ ጋር የተነጋገረ መሆኑ ገልጾ ነበር። ይህም የእስክንድር ፋኖ እንደሆነ በሰፊው የሚታመንበት ሲሆን በዚህም ረገድ እስክንድር ቀዳሚ ሆኖ መገኘቱ የእነ ዘመነን ቡድን የመቀደም መንፈስ ውስጥ እንዳስገባቸው ጫካ ከገቡትም ጭምር ሲነገር ተሰምቷል።

“ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው” በሚል ርዕስ ባጋራነው የዜና ዘገባ ከጦርነት በስተቀር ሁሉንም አማራጭ የተጠቀመው ሻዕቢያ ኢትዮጵያ ላይ ያቀደው ባለመሳካቱ መጨረሻው እና አይቀሬው አማራጭ ዲፕሎማሲና ድርድር እንደሆነ በግምገማው ያመነበት ጉዳይ ነው። የእነ ዘመነ ካሤን ቡድን በሁሉም መስክ የሚያግዘው ሻዕቢያ ዕገዛውን አጠናክሮ መቀጠል ባለመቻሉ ድርድርን ጊዜ መግዣ ወይም እጅ መስጫ አድርጎ አቅርቧል።

መሪ ዓልባው የእነ ዘመነም ቡድን ገና አንድ ሳምንት እንኳን ሳይሞላው ተጠናክሮ ከመሥራት ይልቅ የመፍረስ ወይም የመበታተን አደጋ ውስጥ እንዳለ አፈትልከው የሚወጡ የድምፅ መረጃዎች ይጠቁማሉ። በተለይ ዘመነ የአዲሱ ፋኖ አደረጃጀት መሪ ሆኖ ባለመውጣቱ “በጎንደሬ አንመራም” የሚሉ ድምፆች የተሰሙ ሲሆን ካስፈለገም “ባሕር ዳርን ይዘን እንገነጠላለን” እንጂ ጎጃም ካልመራ በፍጹም በስብስቡ አንቀጥልም ያሉም አሉ።

ባለፈው ወር በአማራ ክልል ከሚገኙ 263 ወረዳዎች በሙሉ የተመረጡ ከ4,500 በላይ ከ10 የማኅበረሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ተወካዮች በሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ልየታ ላይ በመሳተፍ የክልሉን ሕዝብ አንኳር አጀንዳዎች ማቅረባቸው ይታወሳል። በዚህ ወቅት የምክክር ኮሚሺኑ ኃላፊዎች እንደተናገሩት ከፋኖ ታጣቂዎች አንዱ ስብስብ ጋር መነጋገራቸውና የትኛው እንደሆነ ለመግለጽ እንደማይችሉ በመናገር በጠቃሚ ጉዳዮች መምከራቸውን አስታውቀዋል። በብዙዎች ዘንድ እንደሚታመነው ይህ የእስክንድር አፋሕድ እንደሆነ የታመነ ነው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ አፋሕድ አዲስ የተመሠረተውን የፋኖ አደረጃጀት ዜና በደስታ የተቀበለው መሆኑ ገልጾዋል። “ለአንድ ዓመት ጥቂት በቀረው የድርጅታችን ዕድሜ የነበረውን ሂደት ስንገመግም፣ ብዙ ውጣ ዉረድ እንደነበረው የምናስታውሰው ነው። ይህም ያስተማረን አንድ ነገር ቢኖር፣ የሁለት ድርጅቶች መመሥረት ስኬት የሚሆነው፣ ሁለቱ ድርጅቶች ከተቻለ በተዋሃደ፣ ካልሆነም በተቀናጀ፣ ይህም ካልሆነ ቢያንስ ቢያንስ በተናበበ አካሄድ ትግሉን ሲመሩት ብቻ መሆኑን ነው” በማለት በተለይ እኛ ከተመሠረትን “አንድ ዓመት” ሊሞላን ነው የሚለውን በመጥቀስ አሁን ከተመሠረተው የፋኖ ኅብረት አፋሕድ ቀዳሚነት እንዳለው ጠቅሷል።

ከዚህና ከሌሎች ጉዳዮች አንጻር ሲታይ፤ አዲስ የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ወደ ድርድር በሚደረገው ጉዞ የበይ ተመልካች ከመሆን ለመዳንና በድርድር ጠረጴዛው ላይ አንዲትም ብትሆን ወንበር ለማግኘት አስቦ የተመሠረተ ነው ለማለት ይቻላል። ጎልጉል ያነጋገራቸው በትግሉ ውስጥ ያሉትም ሆነ ከትግሉ ውጪ ያሉ የፋኖን አካሄድ የሚከታተሉ የሚናገሩት ይህንኑ የሚያጸና ነው።    

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: Amhara Fano, Amhara Fano National Force, Zemene Kassie

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule