• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው  

April 15, 2025 12:32 am by Editor 1 Comment

በትግራይ የተኩስ ማቆም ስምምነት መደረጉን ተከትሎ ያኮረፈው ሻዕቢያ ከግብጽ በወሰደው ውክልና “አንጃ” ከሚባለው የትህነግ ውስን ኃይልና በአማራ ኦሮሚያ ክልል ጠብ መንጃ ካነሱ ኃይሎች ጋር ግንባር ገጥሞ ኢትዮጵያ ምድር ላይ ሊከፍት ያሰበውን ውጊያ በአቅም ማነስና ምድር ላይ ባሉ እውነታዎች አስገዳጅነት ለማራዘም መወሰኑ ተሰማ።

የኤርትራን የጦርነት ዝግጅት ከውስጥና ከውጭ የሚከታተሉ የኢትዮሪቪው የመረጃ ሰዎች እንዳሉት፣ ከግብጽ በወሰደው ውክልናና ከግል ስጋቱ በመነሳት ከኤርትራ ውጭ በኢትዮጵያ ግዛት ሊጀመር ያሰበውን ጦርነት ለማቆየት የወሰነው ምድር ላይ ባሉ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሳቢያ ዓቅሙ እንደማይፈቅድ ተረድቶ ነው።

የኢትዮጵያ መንግሥት “ጦርነት አንፈልግም። ከነኩን ግን ምላሹ የከፋ ይሆናል” ማለቱ የሚታወስ ነው።

እንደ ዜናው ሰዎች ከሆነ የመጀመሪያው ምክንያት በትግራይ አሁን ላይ የተፈጠረው “ጦርነት በቃን” የሚለው የሕዝብ ድምጽ፣ የትግራይ ታጣቂ ኃይሎች “አንዋጋም” በሚል መክዳታቸውና አሁንም እየከዱ መሆናቸው፣ ውስን የታጣቂዎቹ አመራሮች እንጂ ሁሉም ከሻዕቢያ ጋር ያለውን ግንኙነት የሚደግፉ አለመሆናቸው ጦርነቱ ቢጀመር ኢትዮጵያ ምድር ተወስኖ ይቀራል የሚለውን ስሌት መና አድርጎታል።

ግብጽን እየታዘዘ ቀጠናውን የጦርነት ዐውድማ ለማድረግ ሶማሊያንና ሶማሊያ ውስጥ ያሉ የሽብር ቡድኖችን በመያዝ እየተንቀሳቀሰ ያለው ሻዕቢያ ያሰበውን ጦርነት ተባብረው የሚገፉበት ከሆነ አሜሪካ ማዕቀብ ለማድረግ እያጤነች መሆኑ ሌላ ምክንያት እንደሆነ ታውቋል።

እስከ ዛሬ ድረስ በአሸባሪዎች ሊስት ውስጥ ያለው ትህነግ አዛውንት አመራሮች በስጋት ፍሬን በመያዛቸው ሳቢያ በግለት የተጀመረው የጦርነት ሩጫ አባርዶታል። ይህንኑ ተከትሎ ትህነግ ውስጥ ማፈግፈግ መታየቱ ከሻዕቢያ በኩል ቅሬታ በማነሳቱ የድርድር አማራጭ ለመያዝ ማሰቡ ተሰምቷል።

ጦርነቱን በትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል፣ ሱዳን አቅጣጫ ለጥጦ በዘመቻ በአንድ ላይ ለማካሄድና የመንግሥትን ኃይል ለመበተን ካይሮ ላይ የተነደፈው የማጥቃት ስልት፣ ሙሉ መረጃ ከጦርነቱ አሰላለፍ ጋር መንግሥት እጅ መግባቱን የገለጹት የዜናው አቀባዮች፣ በኦሮሚያ የሸኔ ኃይል በሚፈለገው ደረጃ አለመሆኑ፣ ከጎጃም የፋኖ እንቅስቃሴ ውጭ በሌሎች አካባቢ ያሉት የፋኖ መሪዎች ለጥሪው ሙሉ ምላሽ አለመስጠታቸውና መቃወማቸው፣ በሱዳን በኩልም ያልተጠበቀ ምክንያት መቅረቡ ሻዕቢያ ካለው አቅም ጋር ተዳምሮ ጦርነት ስለማያዋጣ ከተገኘ የዲፕሎማሲውን አግባብ መከተል ወደሚለው አማራጭ ለመዞር እያማተረ መሆኑን ገልጸዋል።

በግብጽ፣ ኤርትራና ሱዳን በመሸገ የትህነግ ተዋጊዎች የሚደገፈው የሱዳን ጦር ኃይሎች አዛዥ አብደል ፈታህ አል ቡርሃን ካርቱም ነጻ መውጣቷን ቢያውጁም፣ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ያለ ውጊያ ለቅቆ መውጣቱ ኃይሉን ባሻው ወቅት መልሶ ሊያንቀሳቅስ እንሚችል ስጋት አለ።

ካርቱምን ጨምሮ በርካታ አካባቢዎችን የለቀቀው ለስልታዊ ማፈግፈግ እንደሆነ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ እየገለጸ ከመሆኑ አንጻር ሱዳን ሻዕቢያ በሚፈልገው መጠን ምቹ አልሆነችም። እንደ መረጃ ምንጮቹ ቀደም ሲል በተገለጸው ምክንያት ሱዳን ግብጽ በሻዕቢያ በኩል እንድተተገብረው የታቀደላት ዕቅድ መፈጸም አትችልም። በአስመራ የሰሞኑ የሁለቱ መሪዎች ውይይት እዚሁ ላይ ያተኮረ ነበር።

ከዚህም በተጨማሪ የሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልከቶ አፍሪካ ኅብረት ባስራጨው መግለጫ፤ በሱዳን እልቂቱ አሳሳቢ ሆኗል። ግጭቱም እየተባባሰ ነው። በተለይም በኤል ፋሸር፣ በሰሜን ዳርፉር እና በዘምዘም የሚባሉ አካባቢዎችን በመጥቀስ አፍሪካ ህብረት በሊቀመንበሩ አማካይነት ስጋቱን አኑሯል። በዚህ መሰሉ የዕርስ በዕርስ ጦርነት እየታመሰች ያለች አገር የኢሳያስን አጀንዳ ጀርባ ለመሸከም አለመቻሏ ሻዕቢያን አቅም አልባ እንዳደረገው ተጨባጭ ያሉትን ምክንያት ገልጸው የዜናው ሰዎች ተናግረዋል።

“ከሱዳንና ከምዕራብ የትግራይ አቅጣጫ ወልቃይትን ለማስለቀቅ ጊዜው አሁን ነው” የሚሉ ወገኖች አሁን ላይ ጋብ ያሉበት ትክክለኛ ምክንያት ባይታወቅም ከዚሁ ጋር ሊገናኝ እንደሚችል የዜናው ሰዎች ገልጸዋል።

ሆርን ሪቪው ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጨክነው ሀገራቸውን ወደ ጦርነት ውስጥ ከከተቱ ሊከሰት የሚችለውን ሲተነብይ ወታደራዊ ሽንፈትን ብቻ ሳይሆን ሊቀለበስ የማይችል የግዛት ለውጥ ወይም አሁን የያዙትን ቅርጽ የጠበቀች ኤርትራ እንደማትኖራቸው ነው።

በድፍን ዓለም የተደገፈችውንና ሩሲያ ያጥለቀለቀቻትን ዩክሬን ጠቅሶ ኤርትራ ብቻዋን የቆመች አገር መሆኗን ያወሳው ሆርን አፍሪካ በዘገባው ኢሳያስ ጦርነቱን ከለኮሱ ለሚደርስባቸው ሁሉ ተከራካሪ ድምጽ እንደሌላቸው አመልክቷል።

ከሶስት አስርት ዓመት በላይ ኤርትራን በወታደራዊ አስተዳደር ጨምድዶ፣ ኢኮኖሚውን አንቆ፣ የያዘው የኢሳያስ አገዛዝ ቀደም ባለው የጦርነት ሙቀትና ጥድፊያ መቀጠል ያልቻለበትን ምክንያት ጠቅሰው ዜናውን ያጋሩን እንዳሉት ሻዕቢያ አሁን ላይ አቅሙ እንደማይችል አምኗል። በርካታ ለሻዕቢያና ለአለቃቸው ግብጽ “አመቺ” ተብለው የነበሩ ጉዳዮች መልካቸውን ቀይረዋል። በዚህም ላይ ኢትዮጵያ ግዙፍ ሠራዊት፣ ዘመናዊ መሣሪያና ከፍተኛ የተባለ የአየር ላይ ብልጫ ስላላት ሻዕቢያ ጦርነቱን እንደማይቋቋም በስፋት አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ሰሞኑን መግለጫ ያወጣው የኢትዮጵያ የጸጥታና የደህንነት ምክር ቤት ስም ባይጠቅስም በማኅበራዊ ሚዲያ አዝማቾች ፕሮፓጋንዳ የታጀቡት የውጭና የውስጥ ኃይሎችን ማጽዳት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማስታወቁ፣ የባህር በር የማግኘትን መብትን በተጀመረው ግለት እንደሚቀጥል ማስታወቁና በሳምንት ውስጥ ከመቶ ሃያ ሺህ በላይ ሰራዊት ማስመረቁ፣ ይፋ ባይሆንም የአገሪቱ የወታደር አቅም መቶ ሺዎችን መዝለሉ የሻዕቢያን ስጋት አጉልቶታል።

ሻዕቢያ በጅምላ ለውትድርና ክተት ማጥራቱን ፣የጉዞ እገዳ በመጣልና መጠባበቂያ ክምችት በማሰባሰብ ወታደራዊ ዝግጅቱን አስቀድሞ ማጠናከሩ ከወራት በፊት ይፋ መደረጉ አይዘነጋም። ከዝግጅቱ ጎን ለጎን ከስደት የተረፈው አነስተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ባለቤት መሆኗ ተተኪ አቅማ ስላሳጣው፣ ዘመን ያለፈባቸው የሶቪየት ሰራሽ መሳሪያዎች በዘለለ ዘመናዊ ትጥቅ ስለሌለው፣ ኢኮኖሚው የደቀቀ በመሆኑ፣ ከአጠቃላይ አገራዊ አቅም ጋር ተዳምሮ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ጦርነትን የመሸከም አቅም አልባ መሆንና የውስጥ አፈናው የፈጠረው መሰላቸት አንድ ላይ ተዳምሮ ጦርነቱ ከተከፈተ ሽንፈት ብቻ ሳይሆን የካርታ ቅርጽ የሚያስቀይር ውጤት ሊኖረው እንደሚችል የሚሰጠው አስተያየት እንደቀጠለ ነው።

መንግሥት ከትህነግ ጋር የፕሪቶሪያው ስምምነት መፈራረማቸውን ተከትሎ በይፋ ቅር መሰነታቸው በሚቀርቧቸው የአማርኛ ሚዲያዎች በስፋት መገለጹ አይዘነጋም። በጦርነቱም ወቅት በትግራይ ከፍተኛ ወንጀል፣ ዝርፊያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ የጅማላና የተናጠል ግድያ ከፈጸመ ኃይል ጋር ዛሬ ላይ እየተደረገ ያለው ስምምነት በትግራይ ክፈተኛ ተቃውሞ እያስነሳ እንደሆነ የሚታውቀ ነው።

ድርድርም ሆነ ማናቸውም የንግድ ስምምነት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆነ ያስታወቀው የኢትዮጵያ መንግሥት ሻዕቢያ እየከጀለ ላለው የውይይት ጥያቄ በሩ ክፍት እንደሆነ የዜናው ምንጮች አመልክተዋል። ይሁን እንጂ የባህር በር ህጋዊ መብት ጉዳይ ግን የንግግሩ የማይቀየር ቁልፍ አጀንዳ ነው። ኢትዮጵያ የባህር በሯን በሤራ ተዘርፋለች የሚለውን የኖረ ቁጭት አጀንዳ ያደርገው መንግሥት በያዘው አቋም ሕዝብ ድጋፍ እየሰጠው ነው።

በተቃራኒ ልክ እንደ ሻዕቢያ ሁሉ ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ አኩርፈው መንግሥት ላይ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የጀመሩ በግልጽ “አብይን ለመጣል ከኤርትራም ሆነ ከማናቸውን አካላት ጋር እንሰራለን” እያሉ ነው። እነዚህ ክፍሎች የኢትዮጵያ ህልውናና ቁልፍ ብሔራዊ ጥቅሟ ላይ እየተማማሉ ያሉ ጥቂት የሚዲያና የታጣቂ ኃይል አመራሮች ናቸው።

በተመሳሳይ ዜና አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መሪነታቸው ሙሉ የሻዕቢያን ዕቅድና ግንኙነት ጠንቀቀው ያውቁ እንደነበርና፣ ከበቂ በላይ ማስረጃና መረጃ እንደነበራቸው የሚያውቁ ሌላው ሻዕቢያን ያበሳጨ ጉዳይ ነው። አቶ ጌታቸው በረሃ ሆነው ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲመሩ ትህነግ በሱዳን፣ በጅቡኢና ሶማሊያ የነበረውን ሴል እንዴት ይጠቀም እንደነበር ስለሚያውቁ ይህም ሌላ ስጋት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። (ኢትዮሪቪው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Right Column Tagged With: eplf, Isayas Afewerki, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. አሰፋ says

    April 17, 2025 03:15 pm at 3:15 pm

    ከኤርትራ ጋር በወደብ ፍለጋ ምክንያት ጦርነት ከመሄድ በፊት፤ ለመገነጣጠል ተዘጋጅተን የተቀመጥን ስዎች ስለሆን፣ መጀመሪያ አብሮ የመኖራችን ጉዳይ ቢረጋገጥ አይሻልም ነበር? በሕግ ተፈቅዶላቸው በግላጭ የሚታገሉ የነጻነት ግምባሮች ወደ 10 የሚጠጉ ያሉ መኖራቸውንም አለመርሳት ነው። ሌላው ጉዳይ ደግሞ፤ ጠ/ሚንስትሩ እንደሚሉትም 20 ዓመትም ቢሆን መዋጋት እችላለሁ የሚዋጋልኝ ሰው ሞልቶኛል ቢሉም፣ ጦርነቱ የማይቀር ከሆነ፣ ከትግራይ ጋር ባደረጉት ጦርነት ጊዜ ስለጦርነቱ አጀማመር ሲተርኩ፣”የትግሬዎች ነጻ አውጭ ግንባር እስከሚጨፈጭፈን ድረስ ምንም አላደረገነውም” (እስከምትጨፈጭፍ ድረስ የማንን ጎፈሬ ታበጥር ነበር? ብሎ የጠየቀ አንድ ነፍስ ባይኖርም) ያሉትን እንዳይደግሙ ቢነገራቸ ጥሩ ነው። እስከምጨፈጨፍ ጠብቄ ተዋጋሁ ማለት የሚወራ ሙያ አልመሰለኝም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule