ሻዕቢያና ትህነግ ጽምዶ ሲመሠርቱ ሻዕቢያ ለትህነግ ሰዎች እንደ ቅድመ ሁኔታና እንደ ትዕዛዝ የሰጠው ሁለት ነጥቦች ያካተተና አፋችሁን ዝጉ የሚል ነበር። አንደኛው ሻዕቢያ በትግራይ ሕዝብ ላይ የዘር ፍጅት ወይም ጄኖሳይድ ፈጽሟል ብላችሁ መናገር አቁሙ፤ ሁለተኛው የሻዕቢያ ታጣቂ የትግራይን ሴቶች ደፍሯል የሚለውን ትንፍሽ ስትሉ እንዳንሰማ የሚሉ ነበር። ሌሎችም አሉ፤ እነዚህ ግን ዋንኞቹ ናቸው። ትህነጋውያንም ጌታና ፈጣሪያቸው ለሆነው ሻዕቢያ መታዘዝ ተፈጥሮአዊ ግዴታቸው ነውና “ጌታ ሻዕቢያ ሆይ! ፍላጎትህ ለኛ ትዕዛዝ ነው፤ እንደ ፈቃድህ ይሁንልህ” ብለው "ጄኖሳይድ" የሚለው ቃል ትግሪኛ እስኪመስል ድረስ ሲጮኹበት የነበረው ልሳናቸው ተዘጋ፤ ሚዲያቸው ጸጥ እረጭ አለ፤ ሻዕቢያም መልካም ነው፤ አሁን ወደ ጽምዶ እንቀጽል አለ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በትላንቱ የፓርላማ ውሎ ከዚህ … [Read more...] about ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …”
eplf
Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women
Warning: this article contains extremely graphic and distressing testimony and images For two years, Tseneat carried her rape inside her. The agony never faded. It attacked her from the inside out. The remnants of the attack stayed in Tseneat’s womb – not as a memory or metaphor, but a set of physical objects: Eight rusted screws. A steel pair of nail clippers. A note, written in ballpoint pen and wrapped in plastic. “Sons of Eritrea, we are brave,” the note reads. “We have … [Read more...] about Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women
ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው
በትግራይ የተኩስ ማቆም ስምምነት መደረጉን ተከትሎ ያኮረፈው ሻዕቢያ ከግብጽ በወሰደው ውክልና “አንጃ” ከሚባለው የትህነግ ውስን ኃይልና በአማራ ኦሮሚያ ክልል ጠብ መንጃ ካነሱ ኃይሎች ጋር ግንባር ገጥሞ ኢትዮጵያ ምድር ላይ ሊከፍት ያሰበውን ውጊያ በአቅም ማነስና ምድር ላይ ባሉ እውነታዎች አስገዳጅነት ለማራዘም መወሰኑ ተሰማ። የኤርትራን የጦርነት ዝግጅት ከውስጥና ከውጭ የሚከታተሉ የኢትዮሪቪው የመረጃ ሰዎች እንዳሉት፣ ከግብጽ በወሰደው ውክልናና ከግል ስጋቱ በመነሳት ከኤርትራ ውጭ በኢትዮጵያ ግዛት ሊጀመር ያሰበውን ጦርነት ለማቆየት የወሰነው ምድር ላይ ባሉ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሳቢያ ዓቅሙ እንደማይፈቅድ ተረድቶ ነው። የኢትዮጵያ መንግሥት “ጦርነት አንፈልግም። ከነኩን ግን ምላሹ የከፋ ይሆናል” ማለቱ የሚታወስ ነው። እንደ ዜናው ሰዎች ከሆነ የመጀመሪያው ምክንያት በትግራይ … [Read more...] about ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው
“አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ
አሁን ፊታቸውን ያዞሩበት ጓደኞቹ አራጋቢዎቹ “ዜናን አንተ ጻፋት፤ አንተ አንብባት” እያሉ ሲያሞካሹት ነበሩ። እንዲህ እንዲሉ ያበቃቸው ደግሞ መሳይ የግንቦት ሰባት/ኢሳት ሁለገብ ሠራተኛ በነበረበት ወቅት ኤርትራ ምድር ሄዶ እንደ አንድ የጦር አዛዥ “ዘመነ ካሤ” የሚመራውን “ጦር” ሲጎበኝ ፎቶ ተነስቶ ሲያዩት፤ የሻዕቢውን መሪ በልዩ ጥሪ አስመራ ድረስ ሄዶ ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ሲያዩት፣ የብልፅግናን ድሎች አዲሳባ ድረስ ሄዶ ሲዘግብ በምላሹም ለከፈለው መስዋዕትነት ተብሎ ትንሽዬ ጉልት ሲቸረው ሲያዩት፣ አዲሳባ በሄደበት ወቅት የሹማምንትን ስልክ ቁጥሮች ሰብስቦ ከመጣ በኋላ ከምግብ ቤቱ ሆኖ የሚያወራበትን አንከር ብሎ የሚጠራውን ዩትዩብ ሲከፍት ሲያዩት ነበር። የመሳይ “ድሎች” እንዲህ በቀላሉ ተወርተው የሚያልቁ አይደሉምና እዚሁ ላይ ላብቃ። አንዳንዶች ሲቀልዱ እንደሰማሁት መሳይ በወኔ … [Read more...] about “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ
ኢመደበኛነት – አገር አፍራሽ የዘመኑ ባንዳነት
ኢመደበኛ አደረጃጀቶች ምንም ጊዜ የማይቀየር፣ ሊስተባበል የማይችልና ልዩ የሆነ መለያ አላቸው። ይህም ለክህደትና ለመሸጥ፣ በኢትዮጵያውያን አገላለጽ ለባንዳነት የተጋለጡ ወይም መደምደሚያቸው ባንዳነት ነው። ሌሎቹን እንተዋቸውና በአገራችን ዋና ምስክር የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትህነግን) ማንሳት ይበቃል። ጥሩም መከራከሪያ የሚቀርብበት የዘመኑ አፍላ ታሪክ ነው። ቃለ ምልልሱ ከተካሄደ ቆይቷል። ሰሞኑን ግን የሩሲያ መንግሥት ቲቪ በድጋሚ ሲያሳየው ነበር። ጋዜጠኛው ቭላዲሚር ፑቲንን ይጠይቃል። ይህን የቆየ ቃለ መጠይቅ ማስተላለፍ የተፈለገው በቀድሞ ወጥ ቀቃይ የሚመራውና አሁን ቫግነር የተባለው ኢመደበኛ አደረጃጀት ከሩስያ መከላከያ ጋር የገባበትን መፈታተን ተከትሎ ነው። ጥያቄ - ይቅርታ ታደርጋለህ?ፑቲን - አዎ፤ ግን ለሁሉም አይደለም፤ጥያቄ - ይቅር ለማለት የማይቻለው … [Read more...] about ኢመደበኛነት – አገር አፍራሽ የዘመኑ ባንዳነት





