“ትዕይንተ ሕዝብ አዘጋጅ ግብረ-ኃይል የቴክኒክ ኮሚቴ” በሚል ልደቱና ነዓምን በሻዕቢያ ምሪት በመሠረቱት ቡድን ውስጥ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መሪ ጃልመሮ በአማካሪው በኩል ጃዋር መሀመድን እንደተካ ልደቱ አረጋገጠ። ይህ ይፋ ይሆነው ከሦስት ቀን በፊት በተደረገው የቡድኑ ስብሰባ ላይ “ጃዋር ስብሰባ የማይገኝበት ምክንያት ምንድን ነው፧” በሚል ከተሰብሳቢዎች ለቀረበ ጥያቄ ልደቱ መልስ ሲሰጥ ነው። ብረት ያነሳውና አሸባሪው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በስብሰቡ ውስጥ እንዲገባ የተወሰነበትን ውሳኔ ልደቱ በስብሰባው ይፋ አላደረገም። ልደቱ ባያብራራም ውሳኔው ግን ነዓምንና ጃዋር በሻዕቢያና እንደ ግብፅ ያሉ ሌሎች የውጭ ኃይሎች ምሪት እያደራጁት ያለው ስብሰብ ውሳኔ መሆኑ ታውቋል። በዚህ ስብሰባ ላይ ግን የጃልመሮ ሠራዊትና ድርጅት በከፍተኛ ደረጃ ክስ ቀርቦበት ነበር። “አብረን … [Read more...] about “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል
wolaitta
ኢመደበኛነት – አገር አፍራሽ የዘመኑ ባንዳነት
ኢመደበኛ አደረጃጀቶች ምንም ጊዜ የማይቀየር፣ ሊስተባበል የማይችልና ልዩ የሆነ መለያ አላቸው። ይህም ለክህደትና ለመሸጥ፣ በኢትዮጵያውያን አገላለጽ ለባንዳነት የተጋለጡ ወይም መደምደሚያቸው ባንዳነት ነው። ሌሎቹን እንተዋቸውና በአገራችን ዋና ምስክር የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትህነግን) ማንሳት ይበቃል። ጥሩም መከራከሪያ የሚቀርብበት የዘመኑ አፍላ ታሪክ ነው። ቃለ ምልልሱ ከተካሄደ ቆይቷል። ሰሞኑን ግን የሩሲያ መንግሥት ቲቪ በድጋሚ ሲያሳየው ነበር። ጋዜጠኛው ቭላዲሚር ፑቲንን ይጠይቃል። ይህን የቆየ ቃለ መጠይቅ ማስተላለፍ የተፈለገው በቀድሞ ወጥ ቀቃይ የሚመራውና አሁን ቫግነር የተባለው ኢመደበኛ አደረጃጀት ከሩስያ መከላከያ ጋር የገባበትን መፈታተን ተከትሎ ነው። ጥያቄ - ይቅርታ ታደርጋለህ?ፑቲን - አዎ፤ ግን ለሁሉም አይደለም፤ጥያቄ - ይቅር ለማለት የማይቻለው … [Read more...] about ኢመደበኛነት – አገር አፍራሽ የዘመኑ ባንዳነት
የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮች ፍርድ ቤት ውሎ
የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን ጨምሮ ለ20 ተጠርጣሪዎች የእስር ፍርድ ቤት በፈቀደው ዋስትና ላይ እና ፖሊስ በጠየቀው የምርመራ ቀናት ላይ ብይን ለመስጠት ለመስከረም 27/2013 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ ዛሬ በነበረው ችሎት በዋስትናው ጉዳይ እና ተጠርጣሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ላይ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በጹሁፍ ያቀረበውን የመልስ መልስ ተቀብሏል። ዛሬ በነበረው ችሎት ማናቸውም ተጠርጣሪዎች በፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን የ6ቱ ጠበቃ ተመስገን ዋጃና ተናግረዋል። በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ከተደረጉ 15 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አስራ 2ቱ በዛሬው ችሎት የተወከሉት፤ በ3 ጠበቆች መሆኑንም ገልጸዋል። ቀሪዎቹ 3 ተጠርጣሪዎች በራሳቸው የሚከራከሩ ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ማክሰኞ በነበረው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት፤ … [Read more...] about የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮች ፍርድ ቤት ውሎ
የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን በእስር እንዲቆዩ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ
የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ የቀድሞ የወላይታ ዞን አመራሮች የነበሩ ግለሰቦችን ጨምሮ 20 ተጠርጣሪዎች በወላይታ ሶዶ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ፤ ለተጠርጣሪዎች ተፈቅዶ በነበረው ዋስትና ላይ ፖሊስ የመልስ መልስ ይዞ እንዲቀርብ ለመጪው ሳምንት ማክሰኞ መስከረም 19 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ጠበቃ ተመስገን ዋጃና ለ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የተጠርጣሪዎችን አቆያየት በተመለከተ በትላንትናው ዕለት ከሰዓት ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ይዞ የነበረ ቢሆንም በጠዋት ችሎት ቀርበው የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች አልተገኙም በሚል ብይኑን ለዛሬ ማሳደሩን ጠበቃው ገልጸዋል። እስከ ምሽት አንድ ሰዓት ድረስ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ሲጠብቁ የቆዩ ሰባት ተጠርጣሪዎችም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በሐዋሳ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ … [Read more...] about የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን በእስር እንዲቆዩ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ




