* ሚስጥረ፤ “ወደ ምርጫው የገባኹት አምኜበት አይደለም” የኢህአፓና የትብብሩ ዋና ጸሐፊ የሆነችው ሚስጥረሥላሴ ታምራት ከአዲስ ኢንሳይደር ጋር ባደረገችው ውይይት ወደ ምርጫው የገባችው አምናበት እንዳልሆነ ተናገረች። ትብብሩ የተከፋፈለ መሆኑን ያልካደችው ሚስጥረ የአውሮጳ ኅብረትና ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ምርጫውን አስመልክቶ የሰጡት መግለጫ “ለእኛ” ከነገሩን ጋር የተለያየ ነው በማለት ኅብረቱ የሐሰት መግለጫ እንዳወጣ እንደምታ የሚሰጥ አስተያየት ሰጥታለች። ከምርጫው በፊት ቅድመ ሁኔታ እንዳስቀመጡና እነዚያ ቅድመ ሁኔታዎች ሳይሟሉ ወደ ምርጫ መግባታቸውን በተመለከተ ስትመልስ እንዲህ ብላለች፤ “ወደ ሰባት የሚሆኑ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠን እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ካልተሟሉ የሚደረግ ምርጫ አምባገንነትን ነው እንጂ የሚያዋልደው በፍጹም የዲሞክራሲ መገለጫ ሊሆን አይችልም በሚል … [Read more...] about እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር
nebe
“ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ
ስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከቀደምቶቹ አምስት ምርጫዎች ለየት ያለና ሕዝቡ በምርጫ ሒደት እምነት እንዲያገኝ የሚያስችለው እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ እንዲሁም መንግሥት በተደጋጋሚ ሲያስተጋቡ ቆይተዋል፡፡ ይኼ ምርጫ በመንግሥት ትኩረት እንደተሰጠው ከሚያሳዩ ጉዳዮች አንዱ የተመደበለት በጀት መጠን ሲሆን፣ በአገሪቱ የምርጫ ታሪክ ከፍተኛ የሆነው 2.5 ቢሊዮን ብር ለምርጫ ዝግጅት በፓርላማ ፀድቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ ምርጫው በአንድ ዓመት እንዲራዘም ከተደረገ በኋላ፣ ቦርዱ ለፓርላማ የ1.1 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ይኼ ከመንግሥት የቀረበለት በጀት ሲሆን፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር የምርጫ ድጋፍ አማካይነት ደግሞ፣ በዓይነት የሚደረግ 1.8 ቢሊዮን ብር ገደማ … [Read more...] about “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ
ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አገር አቀፍ ምርጫን ለማከናወን በጊዜ ሰሌዳው ላይ ካስቀመጣቸው ተግባራት መካከል አንዱ በሆነውና የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ምልክቶቻቸውን የሚመርጡበት/ የሚያስገቡበት መርሃ ግብር መሰረት ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን የመረጡ ሲሆን በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፀድቋል። በዚህም መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን መውሰዳቸውን የኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡ (ኢትዮ ኤፍ ኤም የኢትዮጵያዊያን) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ
የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ
የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የመሥራች አባላት ጉዳይን አስመልክቶ ፓርቲው ያቀረበው የመሥራች አባላት ዝርዝር ላይ ቦርዱ 50 የሚሆን ናሙና በመውሰድ ያደረገው ማጣራት ስለ ትክክለኛነቱ ከፍተኛ ጥርጣሬ ውስጥ ያስገባው በመሆኑ፤ ቦርዱ ጉዳዩን ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ልኮት እንደነበር ይታወሳል። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽንም ባደረገው የማጣራት ሥራ ከሶማሌ ክልል 1145 መሥራች አባላት፣ ከአፋር ክልል 72 መሥራች አባላት፣ ከኦሮሚያ ክልል 23 መሥራች አባላት፣ ከአ.አ. ከተማ አስተዳደር 58 መሥራች አባላት በጠቅላላው የ1298 መሥራች አባላት በተጠቀሱት አድራሻ ያለመኖራቸውን ማረጋገጡን የሚያስረዳ መግለጫ በመስጠቱ የቦርዱም ሆነ የፖሊስ ኮሚሽኑ የማጣራት ሥራ የሚያሣየው ፓርቲው እያወቀ ወይም ማወቅ እየተገባው በቃለመኃላ በተረጋገጠ ሰነድ ያቀረበው የመሥራች አባላት ሥም ዝርዝር … [Read more...] about የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ




