ሀገር ሙሉ ሕዝብ በሴፍቲኔት እየተረዳ አይደለም የዓለም ባንክ የሰጠው ዕርዳታ ለ700 ሺህ ሕዝብ ብቻ የሚውል ነው ሰላሳ ዓመት ሞላኝ የሚለውና ብዙዎችም የሚዲያ ጽናት፣ አውራ፣ ወዘተ እያሉ የሚጠሩት አውሬው ሪፖርተር ሀገር ለማፍረስ ቀስ እያለ በመሸርሸር ሥራ ላይ እንደተሠማራ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ በርካታ መረጃዎች አውጥቶበታል፤ ማውጣቱንም ይቀጥላል። አፍቃሪ ትህነግ የሆነው ሪፖርተርና ባለቤቱ አማረ አረጋዊ ዜና መቀሸብ የተካኑበት ሞያቸው ነው። አካሄዱ ግልጽና ጽንፈኛ የመቃወም ስልት የተከተለ ሳይሆን እንደ ምስጥ ከውስጥ የመቦርቦርና ቀፎ አድርጎ የማስቀረት ነው። በዚህ ስልት የሚዘገቡትን የዜና ዘገባዎችን ማሰራጨት ለሪፖርተር አይጠበቅበትም፤ አፈ-ሰማይ የሆነው የማኅበራዊ ሚዲያ ተቀላቢ፤ ይህ ሁሉንም ማለትም በመንግሥትም፣ በግልም፣ በግብፅም፣ በሻዕቢያም፣ ወዘተ … [Read more...] about ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ
Feeding the Fox
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢ ስለሆኑት የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት ሲነሳ ግንኙነታቸው “በሬ ካራጁ” እንደሚሉት ዓይነት መሆኑን መጠቆም ጉዳዩን ምን አልባትም ማሳነስ ካልሆነ በቀር አይበዛም። ምክንያቱም አውሬው ኦሮሚያ ላይ በተቀመጡ የትህነግ ቅምጦች አማካይነት መረጃ እየተቅበለ በተሰጠው የቤት ሥራ መሠረት ኃላፊዎችን እያንገዋለለ ያስጠበጥብ ስለነበር ነው። በዘመነ ት ህነግ ሪፖርተር ኦሮሚያ ላይ የሠራው ሤራና አሻጥር በዚህ አጭር ጽሑፍ የሚገለጽ አይደለም። ትህነግ ኦሮሚያን የተቆጣጠረው በሪፖርተር አማካኝነት ነበር ቢባል ምንም ማጋነን አይሆንም። በኦሮሚያ ላይ የሚከናወኑ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ፣ የኢኮኖሚ ጉዳዮች መረጃ ይጠባ የነበረው ሪፖርተር ነበር። ለምሳሌ፤ ኢህአዴግ ሥልጣን ላይ በነበረ ጊዜ፤ በተዋረድ የተቀመጡ የትህነግ ካድሬዎችና ሰላዮች ጥይት በማቀበል … [Read more...] about የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
የሪፖርተርን እና የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ“በሬ ካራጁ” አዋዋል በአንድ ታሪክ እናብራራው … አንድ አውራ ዶሮ የነበረው አንድ ሰነፍ ገበሬ ነበር፤ ገበሬው ይህንን አውራ ዶሮ ከገዛበት ቀን ጀምሮ ዶሮውን ለመብላት የሚመኝ አንድ ኮሳሳ ቀበሮ በገበሬው ቤት ሁልጊዜ ያንዣብባል፤ በሰፈሩ እየዞረም “ዶሮው ታምሟል፤ ጠዋት ይሞታል” እያለ ቀበሮው ለሰፈረተኛው በሙሉ ያወራል፤ የሚወራበትን ያልሰማው ወይም ጆሮ ዳባ ያለው ሰነፍ ገበሬም ጉዳዩን ከመጠየቅና ከማጣራት ይልቅ “ቀበሮው መዞር ከጀመረ አንድ ቀን ሆነው፤ አንድ ሳምንት ሆነው፤ 15 ቀን ሆነው፤ … መቼም ቢርበው ነው” እያለ ያገኘውን ሥጋ ሲመግበውና የዙረቱን “በዓል” ሲያከብርለት ከሰነበተ በኋላ ቀበሮው በደንብ ሲጠበድል ዶሮውንም ያበላውን ገበሬም ሰለቀጣቸው። በኢትዮጵያ በነጻ ሚዲያ ስም በነጻነት እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ሪፖርተር … [Read more...] about የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን



