• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ

February 4, 2026 12:14 pm by Editor Leave a Comment

* በስጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉት የትግራይ ተወላጆች ቤታቸው ሳይፈርስ፣ ንብረታቸው ሳይጎድል ለዓመታት ጠብቋቸዋል

በትላንትናው የፓርላማ ውሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢሉባቦር ዞን ሁሩሙ ወረዳ ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን አስመልክቶ የተናገሩ የብዙዎችን ልብ የነካና ኢትዮጵያዊነትን አድምቆ ያሳየ መረጃ ነበር።

“ለምሳሌ ጦርነት ሲጀመር” አሉ ዐቢይ “ከኢሉባቡር ሸሽተው ትግራይ የሄዱ አርሶ አደሮች ነበሩ። ከዛ የመጣችሁ ሰዎች አጥኑ ይሄን ጉዳይ ትክክለኛ መረጃ ነው።

“ሰዎቹ ሸሽተው ትግራይ ገብተዋል፤ ኢሉባቡር ያሉ አርሶአደሮች ከእነርሱ ማሳ ቡና ለቅመው ሸጠው ገንዘቡን በአካውንታቸው ያስገባሉ፤ ሰዎቹ የሉም። ከእርሻቸው ላይ የተመረተ ምርት ሸጠው ገንዘቡን በራሳቸው አካውንት ያስገባሉ።

“ሰዎቹ ‘የኛ ሰዎች በሌለንበት ሰርተው አካውንታችን እያስገቡ ነውና በቃ እንመለስ’ ብለው ተመልሰው ኢሊሉባቡር አሉ አሁን፣ እየኖሩ ነው” ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፓርላማ ማብራሪያቸው ላይ የጠቀሱት ይህ የአብሮነት እሴት፣ ኢትዮጵያ በፈተናዎች ውስጥም ጠንካራ መሰረት እንዳላት ማሳያ ሆኗል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ጦርነቱ ሲጀመር በኢሉአባቦር የነበሩ አርሶ አደሮች ከአካባቢው ሸሽተው ትግራይ ከገቡ የትግራይ ተወላጆች ማሳ ላይ ቡና ለቅመው፣ ሸጠው ገንዘቡን በአካውንታቸው ያስገቡ እንደነበር ገልፀዋል።

ይህንን ያዩት አርሶአደሮችም ተመልሰው ከቤታቸው ገብተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚነስትሩ በራያ፣ በፀለምት እና በኦሮሚያ አካባቢዎች ሌሎችም ወደ ቄያቸው ተመልሰው እየኖሩ ነው ብለዋል።

ከዓመታት በፊት በኢሉአባቦር ዞን ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆች በጸጥታ ስጋት ምክንያት ንብረታቸውን ጥለው ወደ ትግራይ ተሰደው ነበር።

ከእነዚህም መካከል አቶ መሀሪ ወልዴ እና አቶ መኮንን በርሄ ይገኙበታል። ተፈናቃዮቹ አርሶ አደሮች ከዓመታት በኋላ ወደ ቀደመ መኖሪያቸው ሲመለሱ የጠበቃቸው ነገር እጅግ አስገራሚ ነበር።

ቤታቸው አልፈረሰም፤ አደራቸውም ተጠብቋል፤ ገቢያቸውም አልተቋረጠም። ቤት ንብረታቸውን ጥለው ወደ ትግራይ የተሰደዱት ተፈናቃዮች የመኖሪያቸው “ቆርቆሮው ጥርኝ ሳይነካ፣ አጥራቸው ሳይነቃነቅ” ጠብቋቸዋል።

በስደት በነበሩበት ወቅትም የቡና ምርታቸውና የቤት ኪራይ ገቢያቸው አቶ አዲሱ አወቀ እና አቶ ታምራት አረጋን በመሰሉ የአካባቢው ነዋሪዎች አማካኝነት በባንክ ከነበሩበት ድረስ በታማኝነት ይላክላቸውም እንደነበር ይናገራሉ።

“በኦሮሞ ማህበረሰብ ዘንድ አደራ መጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት ነው” የሚሉት ነዋሪዎቹ፣ የወንድሞቻቸውን ንብረት እንደራሳቸው ጠብቀው አደራቸውን በታማኝነት በመወጣት አስረክበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፓርላማ በሰጡት ማብራሪያ፣ ይህንን የኢሉአባቦርን ታሪክ በማንሳት፤ ኢትዮጵያውያን በፖለቲካ ትኩሳት ሳይበገሩ በአብሮነት የመኖር ጥልቅ እሴት እንዳላቸውና ይህንንም ማጠናከር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውበታል። የሁሩሙ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ቸርነት እንዳሉት፣ ዛሬ በወረዳው ሁሉም ኢትዮጵያውያን በፍቅርና በአንድነት እየኖሩ ነው። (EBC)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Social Tagged With: DDR, Illubabor, tigray

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule