እሑድ ነሐሴ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ባካሄደው የውይይት መድረክ “ፖለቲካ ማለት” በሚል ርዕስ ሰፊ ጥናት ያቀረቡት የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)፣ “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን፣ በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መቋቋም አቅቶናል” አሉ። ፕሮፌሰሩ አክለውም “ያኔ በእኛ ዘመን ዕድገት በኅብረት እንደሚባለው፣ ዛሬ ላይ ደግሞ እብደት በኅብረት የታወጀ ይመስላል” በማለት አሁን ላይ እየታየ ስላለው አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ሁኔታ ተናግረዋል። አሁን የሚታየው ውዝግብ የበዛበት የዓለም ሁኔታ የሥልጣኔ ቀውስ መሆኑንና ኢትዮጵያን ጭምር ሰለባ ማድረጉን አስረድተዋል። “የዓለም ሁኔታ ምን እየሆነ ነው? የሰው ልጅስ ወዴት እየገባ ነው?” በሚሉ ጥያቄዎች ዙሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥልቀት ሲያሰላስሉ መቆየታቸውን የተናገሩት ብርሃኑ … [Read more...] about “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል”
berhanu nega
በኢትዮጵያ ካሉ 47 ሺህ ት/ቤቶች ውስጥ ተፈላጊውን “ከፍተኛ ደረጃ” የሚያሟሉት አራት ብቻ ናቸው
በኢትዮጵያ ካሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ “ከፍተኛ” የሚባለውን ደረጃ ያሟሉ፤ አራት ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በኢትዮጵያ በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ካሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተፈላጊውን “ከፍተኛ ደረጃ” የሚያሟሉት አራቱ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ወላጆች፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና መምህራንን የሚያሳትፍ፤ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ያለመ ሀገር አቀፍ የትምህርት ዘመቻ በአንድ ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 15፤ 2015 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው። ሪፖርቱን ለፓርላማ አባላት ያቀረቡት … [Read more...] about በኢትዮጵያ ካሉ 47 ሺህ ት/ቤቶች ውስጥ ተፈላጊውን “ከፍተኛ ደረጃ” የሚያሟሉት አራት ብቻ ናቸው
“አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው
በ2014 የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከ50 በመቶ በላይ ያመጡት ተፈታኞች 3.3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ የ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሪፖርት እና ዋና ዋና ግኝቶች ዙሪያ መግለጫ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ የዘንድሮው የ12 ከፍል ፈተና ውጤት አስደንጋጭ እንደሆነ እንረዳለን ብለዋል። በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለፈተና የተመዘገቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጠቅላላ 985ሺ 354 ተማሪዎች እንደነበሩ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡ ከዚህ ውስጥም ለፈተና የቀረቡት ተማሪዎች 908ሺ ሺህ 256 (92.2%) ሲሆኑ 77ሺህ 98 ተማሪዎች ፈተና አልወሰዱም ተብሏል። በትምህርት ዘርፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከማህበራዊ ሳይንስ በተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን የተፈጥሮ ሳይንስ 31.63 ከመቶ … [Read more...] about “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው
በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት መምህራን አያስፈልጉም
የትምህርት ሚኒስቴር አካሄዱኩት ባለው የዳሰሳ ጥናት፣ በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከ30 በመቶ በላይ መምህራን እንደማያስፈልጉ መታወቁን ሚኒስትሩ አስታወቁ፡፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የተቋማቸውን የ2015 ዓ.ም. ሩብ ዓመት አፈጻጸም ማክሰኞ ኅዳር 20 ቀን 2015 ዓ.ም. ለፓርላማ ሲያቀርቡ፣ ዩኒቨርሲቲዎች በአማካይ በሴሚስተር አራት ኮርስ ወይም 12 ክፍለ ጊዜ መያዝ እንዳለባቸው ቢጠበቅባቸውም፣ ብዙዎቹ መምህራን በሴሚስተር አንድ ኮርስ አስተምረው የሙሉ ጊዜ መምህራን ተብለው እንደሚጠሩ ተናግረዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ መሆን ከበጀታቸው ጋር አብሮ ሊሄድ የሚችል የመምህራን ቁጥር በመያዝ፣ በልካቸው ሊራመዱ እንደሚገባ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲዎች ከሌሎች የገንዘብ ምንጮች በሚያገኙዋቸው ገቢዎች ተወዳዳሪና ተመራጭ … [Read more...] about በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት መምህራን አያስፈልጉም
በሁሉም ክልል 50 የልህቀት ት/ቤቶች ይገነባሉ፤ ለወደሙትም 1.6 ቢሊዮን ብር ተበጅቷል
በሁሉም ክልሎች በችሎታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው 50 ትምህርት ቤቶች ሊገነቡ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በሁሉም ክልሎች በዓይነታቸው ልዩ የሆኑና የልህቀት ማዕከል የሚሆኑ 50 ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ ብለዋል። ትምህርት ቤቶቹ ቀጣይ የአገር መሪ የሚሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎች የሚፈልቁበት በችሎታቸው ብቻ የሚመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው መሆናቸውንም ተናግረዋል። በትምህርት ቤቶቹ የ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መሠረት ባደረገና የትምህርት ሚኒስቴር በሚያወጣውን መመዘኛ የሚያሟሉ ተማሪዎች የሚማሩባቸው እንደሆኑም ተገልጿል። በሁሉም ክልሎች በሚገነቡት እነዚህ የልህቀት ማዕከላት ከሁሉም የአገሪቱ ክልሎች የሚመለመሉ ተማሪዎችን ተቀብለው የሚያስተምሩ ናቸው። በተያያዘ ዜና የትምህርት ሚኒስቴር … [Read more...] about በሁሉም ክልል 50 የልህቀት ት/ቤቶች ይገነባሉ፤ ለወደሙትም 1.6 ቢሊዮን ብር ተበጅቷል