• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት መምህራን አያስፈልጉም

December 5, 2022 09:36 am by Editor 1 Comment

የትምህርት ሚኒስቴር አካሄዱኩት ባለው የዳሰሳ ጥናት፣ በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከ30 በመቶ በላይ መምህራን እንደማያስፈልጉ መታወቁን ሚኒስትሩ አስታወቁ፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የተቋማቸውን የ2015 ዓ.ም. ሩብ ዓመት አፈጻጸም ማክሰኞ ኅዳር 20 ቀን 2015 ዓ.ም. ለፓርላማ ሲያቀርቡ፣ ዩኒቨርሲቲዎች በአማካይ በሴሚስተር አራት ኮርስ ወይም 12 ክፍለ ጊዜ መያዝ እንዳለባቸው ቢጠበቅባቸውም፣ ብዙዎቹ መምህራን በሴሚስተር አንድ ኮርስ አስተምረው የሙሉ ጊዜ መምህራን ተብለው እንደሚጠሩ ተናግረዋል፡፡

በዚህም የተነሳ የዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ መሆን ከበጀታቸው ጋር አብሮ ሊሄድ የሚችል የመምህራን ቁጥር በመያዝ፣ በልካቸው ሊራመዱ እንደሚገባ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲዎች ከሌሎች የገንዘብ ምንጮች በሚያገኙዋቸው ገቢዎች ተወዳዳሪና ተመራጭ የትምህርት ተቋም የሚያደርጓቸው ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ፣ ውድድርን መሠረት አድርገው ለመምህራኖቻቸው የተሻለ ደመወዝ ሊከፍሉ እንደሚችሉ አስረድተዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ የተሻለ የደመወዝ ክፍያ መፈጸም ምንም ጥያቄ የሌለው ጉዳይ ቢሆንም፣ ባለው አገራዊ ሁኔታ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በሲቪል ሰርቪስ ሕጉ እስከተገዙ ድረስ፣ መንግሥት ደመወዝ ልጨምር ቢል ጭማሪው ለዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ሳይሆን፣ ለሁሉም ተቋማት መጨመር ስላለበት ይህ የማይቻል ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡

“አገሪቱ አሁን ካለችበት የጦርነት ድባብ ውስጥ ወጥታ የደመወዙ ጉዳይ በድጋሚ ታይቶ እንዲታሰብና መምህራን የተከበሩ እንዲሆኑ እናደርጋለን፡፡ ድሮ ‹ሙሽሪት ኩሪ ኩሪ ወሰደሽ አስተማሪ› ይባል ነበር፡፡ አሁን ግን መምህርነት በገቢ ልክ ከሆነ መምህርነት ሚስትም የሚያስገኝ አይመስለኝም” ብለዋል፡፡

በመሆኑም ይህ አሠራር መቀየር እንዳለበት የገለጹት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ መምህር የተማሪዎቹ ወላጆች ጓሮ ውስጥ ተከራይቶ እየኖረ “መምህር ተከብሮ ይኑር” ማለት ከባድ በመሆኑ መስተካከል እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲ መምህራን ከጥቂት ወራት በፊት የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ባቋቋሟቸው ማኅበራት አማካይነት፣ መንግሥት የደመወዝ ጭማሪና የእርከን ዕድገት እንዲያደርግ በተደጋጋሚ ሲጠይቁ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: berhanu nega, minister of education

Reader Interactions

Comments

  1. Berelea says

    January 12, 2023 01:01 am at 1:01 am

    አይ ብሬ ማይክ በያዝክ ቁጥር ቀልድህ ይጨምራል ምን እንደምትናገር ስለማታውቀው እላይ የተናገርከውን ከታች ታፈርሰዋለህ መገለባበጥ የተሰራህበት ስለሆነ ለመከርበት ችግር የለብህም ለስርአቱ በጣም አስፈላጊ ሰው ነህ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule