• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል”

September 7, 2023 01:31 am by Editor 1 Comment

እሑድ ነሐሴ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ባካሄደው የውይይት መድረክ “ፖለቲካ ማለት” በሚል ርዕስ ሰፊ ጥናት ያቀረቡት የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)፣ “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን፣ በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መቋቋም አቅቶናል” አሉ። ፕሮፌሰሩ አክለውም “ያኔ በእኛ ዘመን ዕድገት በኅብረት እንደሚባለው፣ ዛሬ ላይ ደግሞ እብደት በኅብረት የታወጀ ይመስላል” በማለት አሁን ላይ እየታየ ስላለው አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ሁኔታ ተናግረዋል። አሁን የሚታየው ውዝግብ የበዛበት የዓለም ሁኔታ የሥልጣኔ ቀውስ መሆኑንና ኢትዮጵያን ጭምር ሰለባ ማድረጉን አስረድተዋል።

“የዓለም ሁኔታ ምን እየሆነ ነው? የሰው ልጅስ ወዴት እየገባ ነው?” በሚሉ ጥያቄዎች ዙሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥልቀት ሲያሰላስሉ መቆየታቸውን የተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ ከዚህ በመነሳት አሁን ያለውን የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታም ሥልታዊ ፍቺ ለመስጠት መሞከራቸውን በመግለጽ ነበር ወደ ጥናታቸው የተንደረደሩት።

ፖለቲካ ለእሳቸው ምን ማለት እንደሆነ ሲናገሩ “ለእኔ ፖለቲካ በጋራ ውሳኔ የመስጠት ሒደት ነው። የፖለቲካ ሥርዓት ደግሞ ይህን በጋራ (በቡድን) ውሳኔ የመስጠት ሒደት ሕግና ተቋም አበጅተው ሲያካሂዱት የሚመጣ ነው፤” በማለት ፍቺ ሰጥተዋል።

“ፖለቲካ ለእኔ ማኅበረሰብን ወደ ተሻለ ደረጃ ለመውሰድ ጥረት ማድረግ ነው፤” የሚል ፍቺ የሰጡት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሁን ባለው የኢትዮጵያም ሆነ የዓለም ተጨባጭ ሁኔታ እርግጠኝነት የጠፋበትና በውዝግብ የተሞላ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል። የሰው ልጅ ሕይወቱን ለማሻሻልና መተባበሩን ለማጠናከር ብሎ በፈጠራቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እየተዋጠ መምጣቱን አመልክተዋል። “ሰዎች በተፈጥሮ የማይጠረቁ መሆናቸው ገንዘብና ቁስ አምላኪነትን ፈጥሯል፤” ብለዋል።

መጠላላትና መገፋፋት የሞላበት የዓለም ሁኔታ መፈጠሩን የተናገሩት ፕሮፌሰሩ፣ “አላዋቂዎች የአደባባይ ተናጋሪ ሆነውና መድረኩን ሞልተው አዋቂዎች ግን ተሸማቀው ዝም ያሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤” ብለው፣ ቴክኖሎጂ በተለይም ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ዓለምን የሁካታ ገበያ እንዳደረጓትም አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የሰው ልጆች ከሌሎች ፍጥረታት በተለየ ሁኔታ ዓለምን ለመቆጣጠር ስለቻሉበት መነሻ ጠለቅ ያለ ሐሳብ የሰነዘሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ “መተባበር” ሰዎችን ታላቅ ፍጡር ማድረጉን ጠቁመዋል።

“ሰው ከሌሎች ፍጡራን በልጦና ገኖ መውጣት የቻለው ከራሱና በአካባቢው ካሉ ሰዎች ውጪ ሰፊ ትብብር መመሥረት በመቻሉ ነው፤” ሲሉ ገልጸውታል። “የለበስነው ልብስ፣ የእጅ ስልክ፣ የምንነዳው መኪና ወይም በየዕለቱ የምንገለገልበት ቁስአካል ተመርቶ ተጠቃሚው ጋር እስኪደርስ እጅግ የበዙ የማይተዋወቁ ሰዎችን መተባበር ይጠይቃል፤” ሲሉም አክለዋል።

“ሰዎች በትብብር ለመኖር የሚያስችሏቸው ብዙ ዓይነት ትርክት ፈጥረዋል። እነዚህ ትርከቶች ደግሞ ለትብብሩ መሠረት ሆነዋል። ገንዘብ አንዱ ትርክት ነው። ሃይማኖት፣ ኮርፖሬሽንና ሌላም ፈጥረዋል። የሰው ልጅ እነዚህን ትርክቶች ከመፍጠር አልፎ ተፈጥሯዊ ናቸው ብሎ እስኪያምናቸውና መልሰው ራሱን እስኪቆጣጠሩት ድረስ ይሄዳል፤” በማለት ነበር ወደ ዋና ጉዳያቸው የገቡት።

የሰው ልጆች መተባበር በመካከላቸው ከሌለ እንደሚጠፉ በምሳሌ ያብራሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ ከረዥም ዘመናት ጦርነት በኋላ በአውሮፓ እ.ኤ.አ. በ1641 የዌስትፋሊያ ስምምነት ላይ መደረሱን አውስተዋል። ይህም የአገሮችን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መፍጠሩን አስረድተዋል። የኔሽን፣ የስቴት፣ እንዲሁም የኔሽን ስቴት ዕሳቤዎችንና ልዩነት ከዚያ በተጨማሪም በየጊዜው የመጡ ርዕዮተ ዓለሞች መውጣትና መውረድን አለፍ ገደም እያሉ ጠቃቅሰዋል።

“አሁን ያለው የዓለም ሁኔታ በርዕዮተ ዓለም ከመመራት ይልቅ፣ በጩኸትና ሁከት የተሞላ ነው። በአጠቃላይ ዓለማችን የሥልጣኔ ቀውስ ገጥሟታል፤” ሲሉ በይነውታል። በሌላ በኩል ነባራዊው የዓለም ሥርዓት መቀየር አለበት የሚል የጂኦ ፖለቲካ ፍጭት ተደራቢ ችግር መሆኑን አመላክተዋል። ብሪክስ የተባለ ማኅበር መፍጠርና ማጠናከር የመጣው የዓለም ሥርዓትን ለመፎካከር መሆኑን አስታውሰዋል።

“እኛ ያለነው የት ጋ ነው?” የሚል ጥያቄ ያነሱት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ በለውጡ ማግሥት ተፈጠረ ያሉትን ቀውስ ገልጸዋል። “በለውጥ ማግሥት በብሔር የሚያስቡ ሰዎች ተራው የእኛ ነው አሉ። አንዳንዶች እኛ በታገልነው የቀደሙት ኃይሎች ሊገቡ አይገባም አሉ። የተበድለናል ትርክት የሚያነሳውም በርካታ ሆነ፤” በማለት በለውጡ ማግሥት ድብልቅልቅ ያለ ጎራ መፈጠሩን አስረድተዋል።

አሁን አሁን ምክንያታዊ ውይይት እየቀረ በየአቅጣጫው መጮህ እየበዛ መሄዱን የተናገሩት የኢዜማ መሪ፣ በተቻለ መጠን ጥሞናና መረጋጋት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ኢዜማ ቢያንስ የችግሩ አካል ላለመሆን ይህንኑ መንገድ መምረጡን አመልክተዋል።

ዓለምን የመምራት ሚና ሊኖራቸው የሚገባ እንደ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያሉ ተቋማት ሚናቸውን እንዲወጡ እየተደረገ አለመሆኑን፣ እንደ ፍራንሲስ ፋኩያማ ያሉ ምዕራባዊያን ምሁራን “የሥልጣኔ መጨረሻ” (The End of Civilization) ብለው የፎከሩለት ሊበራሊዝም ዛሬ ዓለምን የተረጋጋች አድርጎ ለመቀጠል ጥያቄ እየተነሳበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

አሁን በርዕዮተ ዓለም የመሠለፍ ጉዳይም ሳይሆን “የገደል ማሚቱ” (Eco Chamber) መሆን ባህል እየሆነ መምጣቱን፣ መደማመጥ በሌለበት የመጮህ አባዜ በዓለም ላይ መግነኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ነባራዊ ቀውስ ራሱን የቻለ ጠባይ ቢኖረውም፣ ከዚሀ የዓለም ሁኔታ ፍፁም የተለየ ግን አለመሆኑን ሞግተዋል። (ሪፖርተር)

ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የኢዜማ መሪ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: berhanu nega, ezema

Reader Interactions

Comments

  1. Miherete Tibebe says

    September 8, 2023 08:23 am at 8:23 am

    OK!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule