• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል”

September 7, 2023 01:31 am by Editor 1 Comment

እሑድ ነሐሴ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ባካሄደው የውይይት መድረክ “ፖለቲካ ማለት” በሚል ርዕስ ሰፊ ጥናት ያቀረቡት የፓርቲው መሪ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)፣ “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን፣ በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መቋቋም አቅቶናል” አሉ። ፕሮፌሰሩ አክለውም “ያኔ በእኛ ዘመን ዕድገት በኅብረት እንደሚባለው፣ ዛሬ ላይ ደግሞ እብደት በኅብረት የታወጀ ይመስላል” በማለት አሁን ላይ እየታየ ስላለው አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ሁኔታ ተናግረዋል። አሁን የሚታየው ውዝግብ የበዛበት የዓለም ሁኔታ የሥልጣኔ ቀውስ መሆኑንና ኢትዮጵያን ጭምር ሰለባ ማድረጉን አስረድተዋል።

“የዓለም ሁኔታ ምን እየሆነ ነው? የሰው ልጅስ ወዴት እየገባ ነው?” በሚሉ ጥያቄዎች ዙሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥልቀት ሲያሰላስሉ መቆየታቸውን የተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ ከዚህ በመነሳት አሁን ያለውን የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታም ሥልታዊ ፍቺ ለመስጠት መሞከራቸውን በመግለጽ ነበር ወደ ጥናታቸው የተንደረደሩት።

ፖለቲካ ለእሳቸው ምን ማለት እንደሆነ ሲናገሩ “ለእኔ ፖለቲካ በጋራ ውሳኔ የመስጠት ሒደት ነው። የፖለቲካ ሥርዓት ደግሞ ይህን በጋራ (በቡድን) ውሳኔ የመስጠት ሒደት ሕግና ተቋም አበጅተው ሲያካሂዱት የሚመጣ ነው፤” በማለት ፍቺ ሰጥተዋል።

“ፖለቲካ ለእኔ ማኅበረሰብን ወደ ተሻለ ደረጃ ለመውሰድ ጥረት ማድረግ ነው፤” የሚል ፍቺ የሰጡት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሁን ባለው የኢትዮጵያም ሆነ የዓለም ተጨባጭ ሁኔታ እርግጠኝነት የጠፋበትና በውዝግብ የተሞላ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል። የሰው ልጅ ሕይወቱን ለማሻሻልና መተባበሩን ለማጠናከር ብሎ በፈጠራቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እየተዋጠ መምጣቱን አመልክተዋል። “ሰዎች በተፈጥሮ የማይጠረቁ መሆናቸው ገንዘብና ቁስ አምላኪነትን ፈጥሯል፤” ብለዋል።

መጠላላትና መገፋፋት የሞላበት የዓለም ሁኔታ መፈጠሩን የተናገሩት ፕሮፌሰሩ፣ “አላዋቂዎች የአደባባይ ተናጋሪ ሆነውና መድረኩን ሞልተው አዋቂዎች ግን ተሸማቀው ዝም ያሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤” ብለው፣ ቴክኖሎጂ በተለይም ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ዓለምን የሁካታ ገበያ እንዳደረጓትም አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የሰው ልጆች ከሌሎች ፍጥረታት በተለየ ሁኔታ ዓለምን ለመቆጣጠር ስለቻሉበት መነሻ ጠለቅ ያለ ሐሳብ የሰነዘሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ “መተባበር” ሰዎችን ታላቅ ፍጡር ማድረጉን ጠቁመዋል።

“ሰው ከሌሎች ፍጡራን በልጦና ገኖ መውጣት የቻለው ከራሱና በአካባቢው ካሉ ሰዎች ውጪ ሰፊ ትብብር መመሥረት በመቻሉ ነው፤” ሲሉ ገልጸውታል። “የለበስነው ልብስ፣ የእጅ ስልክ፣ የምንነዳው መኪና ወይም በየዕለቱ የምንገለገልበት ቁስአካል ተመርቶ ተጠቃሚው ጋር እስኪደርስ እጅግ የበዙ የማይተዋወቁ ሰዎችን መተባበር ይጠይቃል፤” ሲሉም አክለዋል።

“ሰዎች በትብብር ለመኖር የሚያስችሏቸው ብዙ ዓይነት ትርክት ፈጥረዋል። እነዚህ ትርከቶች ደግሞ ለትብብሩ መሠረት ሆነዋል። ገንዘብ አንዱ ትርክት ነው። ሃይማኖት፣ ኮርፖሬሽንና ሌላም ፈጥረዋል። የሰው ልጅ እነዚህን ትርክቶች ከመፍጠር አልፎ ተፈጥሯዊ ናቸው ብሎ እስኪያምናቸውና መልሰው ራሱን እስኪቆጣጠሩት ድረስ ይሄዳል፤” በማለት ነበር ወደ ዋና ጉዳያቸው የገቡት።

የሰው ልጆች መተባበር በመካከላቸው ከሌለ እንደሚጠፉ በምሳሌ ያብራሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ ከረዥም ዘመናት ጦርነት በኋላ በአውሮፓ እ.ኤ.አ. በ1641 የዌስትፋሊያ ስምምነት ላይ መደረሱን አውስተዋል። ይህም የአገሮችን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መፍጠሩን አስረድተዋል። የኔሽን፣ የስቴት፣ እንዲሁም የኔሽን ስቴት ዕሳቤዎችንና ልዩነት ከዚያ በተጨማሪም በየጊዜው የመጡ ርዕዮተ ዓለሞች መውጣትና መውረድን አለፍ ገደም እያሉ ጠቃቅሰዋል።

“አሁን ያለው የዓለም ሁኔታ በርዕዮተ ዓለም ከመመራት ይልቅ፣ በጩኸትና ሁከት የተሞላ ነው። በአጠቃላይ ዓለማችን የሥልጣኔ ቀውስ ገጥሟታል፤” ሲሉ በይነውታል። በሌላ በኩል ነባራዊው የዓለም ሥርዓት መቀየር አለበት የሚል የጂኦ ፖለቲካ ፍጭት ተደራቢ ችግር መሆኑን አመላክተዋል። ብሪክስ የተባለ ማኅበር መፍጠርና ማጠናከር የመጣው የዓለም ሥርዓትን ለመፎካከር መሆኑን አስታውሰዋል።

“እኛ ያለነው የት ጋ ነው?” የሚል ጥያቄ ያነሱት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ በለውጡ ማግሥት ተፈጠረ ያሉትን ቀውስ ገልጸዋል። “በለውጥ ማግሥት በብሔር የሚያስቡ ሰዎች ተራው የእኛ ነው አሉ። አንዳንዶች እኛ በታገልነው የቀደሙት ኃይሎች ሊገቡ አይገባም አሉ። የተበድለናል ትርክት የሚያነሳውም በርካታ ሆነ፤” በማለት በለውጡ ማግሥት ድብልቅልቅ ያለ ጎራ መፈጠሩን አስረድተዋል።

አሁን አሁን ምክንያታዊ ውይይት እየቀረ በየአቅጣጫው መጮህ እየበዛ መሄዱን የተናገሩት የኢዜማ መሪ፣ በተቻለ መጠን ጥሞናና መረጋጋት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ኢዜማ ቢያንስ የችግሩ አካል ላለመሆን ይህንኑ መንገድ መምረጡን አመልክተዋል።

ዓለምን የመምራት ሚና ሊኖራቸው የሚገባ እንደ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያሉ ተቋማት ሚናቸውን እንዲወጡ እየተደረገ አለመሆኑን፣ እንደ ፍራንሲስ ፋኩያማ ያሉ ምዕራባዊያን ምሁራን “የሥልጣኔ መጨረሻ” (The End of Civilization) ብለው የፎከሩለት ሊበራሊዝም ዛሬ ዓለምን የተረጋጋች አድርጎ ለመቀጠል ጥያቄ እየተነሳበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

አሁን በርዕዮተ ዓለም የመሠለፍ ጉዳይም ሳይሆን “የገደል ማሚቱ” (Eco Chamber) መሆን ባህል እየሆነ መምጣቱን፣ መደማመጥ በሌለበት የመጮህ አባዜ በዓለም ላይ መግነኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ነባራዊ ቀውስ ራሱን የቻለ ጠባይ ቢኖረውም፣ ከዚሀ የዓለም ሁኔታ ፍፁም የተለየ ግን አለመሆኑን ሞግተዋል። (ሪፖርተር)

ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የኢዜማ መሪ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: berhanu nega, ezema

Reader Interactions

Comments

  1. Miherete Tibebe says

    September 8, 2023 08:23 am at 8:23 am

    OK!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule