• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ፲፪ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት የዘንድሮና የአምናው መጠነኛ ንጽጽር

September 11, 2024 09:01 am by Editor Leave a Comment

በ2016 ዓም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 684 ሺህ 205 ተማሪዎች ያለፉት 36 ሺህ 409 ወይም 5.4 በመቶ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከትላንት በስቲያ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ከዚህ በታች ያለውን መረጃ ያሰባሰብነው ከመንግሥታዊ ሚዲያና ከቲክቫህ ነው።

  • በአጠቃላይ 1 ሺህ 363 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ሲሆን በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ 4 ትምህርት ቤቶች ከሐረሪ ክልል ውጭ ሁሉም ክልሎች ላይ አንድም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን አመላክተዋል።
  • በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ከ500 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ባለፈው ዓመት 273 የነበሩ ሲሆን በአሁኑ 1ሺ 220 ተማሪዎች ከ500 በላይ ያመጡ ናቸው ተብሏል።
  • እንዲሁም በዘንድሮ 12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 5.4 በመቶ ፈተናውን አልፈዋል ይህም ማለት 36 ሺ 4 መቶ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል፡፡
  • የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛው ውጤት የተመዘገበው በትግራይ ነው፡፡
    • በክልሉ ቓላሚኖ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነ ልጅ ከ700 ፈተና 675 በማምጣት ከፍተኛውን ውጤት ማስመዝገቡ ተነግሯል፡፡
  • በአዲስ አበባ የካቴድራል ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነች ልጅ ከ600 ውጤት 575 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች።
  • ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡት ሴቶች ሲሆኑ በተፈጥሮ ሳይንስ ካቴድራል ትምህርት ቤት 575 ከ600 እና በማኅበራዊ ሳይንስ ኢትዮ ፓረንትስ ትምህርት ቤት 538 ማስመዝገባቸው ተጠቁሟል፡፡
  • ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 21 በመቶ (ከ10ሺ በላይ) ተማሪዎችን ከክልሎች ደግሞ ሐረር 337 እና ኦሮሚያ 8ሺ በላይ ተማሪዎች ማለፋቸውን እንዲሁም ሁሉም ክልሎች ከአምናው የተሻለ ተማሪዎችን ማሳለፋቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
  • በዘንድሮ ዓመትም የሬሜዲያል ፈተና የሚኖር ሲሆን የተፈታኞች ቁጥር ግን ከአምናው ቁጥር እንደሚቀንስ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡
  • ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ሀገራዊ አማካኝ ውጤት (mean) 29.76 በመቶ መሆኑን ጠቅሰው÷ የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት ከ700ው 675 መሆኑን እና ይህም በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘ ከፍተኛ ውጤት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
  • ከፍተኛ አማካይ ውጤት (66.1 በመቶ) የተመዘገበው በአዳሪ ትምህርት ቤቶች መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡
  • ከፍተኛ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ትምህርት ቤቶች፤
    • አዳሪ ትምህርት ቤቶች
    • ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች
    • የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች
    • መንግሥታዊ ያልሆኑ ትምህርት ቤቶች
  • የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በኦንላይን እና በወረቀት የተሰጠ ሲሆን፤ ፈተናውን በኦንላይን ከወሰዱት መካከል 26.6 በመቶ የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት አምጥተዋል።
  • ዘንድሮ 30 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን የወሰዱ ሲሆን፤ በቀጣይ ዓመት እስከ 150 ሺህ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናውን እንዲወስዱ ለማድረግ ዕቅድ ይዘናል።
  • “በ2016 ትምህርት ዘመን በወረቀትና በበይነ መረብ የተሰጠው ፈተና ውጤት እንድምታው ሲታይ ከ2014 ዓ/ም 30,034 (3.3%) ፣ ከ2015 ዓ/ም 27,267 (3.2%) … (ዘንድሮ 5.4%) መሆኑ እያሽቆለቆለ እየሄደ ያለው ጉዞ የተገታ እና መጠነኛ የመሻሻል አዝማሚያ ያሳየ ቢሆንም አሁንም 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተፈታኞች ቁጥር በጣም ዝቅተኛ ነው” በማለት ሚኒስትሩ በመግለጫቸው ተናግረዋል።
  • በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የነበረው የደንብ መተላለፍ ከአለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ እንደነበርም አንስተዋል፡፡
    • የደንብ ጥሰት የፈጸሙ 313 ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ውጤታቸው እንደተሰረዘ ገልጸዋል።
  • በአማራ ክልል በተለያዩ ምክንያቶች ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች ከመስከረም 13 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ፈተና እንደሚወስዱ የትምህርት ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Social Tagged With: berhanu nega, ESLCE, Exam result 12th grade, ministry of education, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule