• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ፲፪ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት የዘንድሮና የአምናው መጠነኛ ንጽጽር

September 11, 2024 09:01 am by Editor Leave a Comment

በ2016 ዓም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 684 ሺህ 205 ተማሪዎች ያለፉት 36 ሺህ 409 ወይም 5.4 በመቶ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከትላንት በስቲያ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ከዚህ በታች ያለውን መረጃ ያሰባሰብነው ከመንግሥታዊ ሚዲያና ከቲክቫህ ነው።

  • በአጠቃላይ 1 ሺህ 363 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ሲሆን በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ 4 ትምህርት ቤቶች ከሐረሪ ክልል ውጭ ሁሉም ክልሎች ላይ አንድም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን አመላክተዋል።
  • በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ከ500 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ባለፈው ዓመት 273 የነበሩ ሲሆን በአሁኑ 1ሺ 220 ተማሪዎች ከ500 በላይ ያመጡ ናቸው ተብሏል።
  • እንዲሁም በዘንድሮ 12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 5.4 በመቶ ፈተናውን አልፈዋል ይህም ማለት 36 ሺ 4 መቶ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል፡፡
  • የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛው ውጤት የተመዘገበው በትግራይ ነው፡፡
    • በክልሉ ቓላሚኖ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነ ልጅ ከ700 ፈተና 675 በማምጣት ከፍተኛውን ውጤት ማስመዝገቡ ተነግሯል፡፡
  • በአዲስ አበባ የካቴድራል ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነች ልጅ ከ600 ውጤት 575 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች።
  • ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡት ሴቶች ሲሆኑ በተፈጥሮ ሳይንስ ካቴድራል ትምህርት ቤት 575 ከ600 እና በማኅበራዊ ሳይንስ ኢትዮ ፓረንትስ ትምህርት ቤት 538 ማስመዝገባቸው ተጠቁሟል፡፡
  • ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 21 በመቶ (ከ10ሺ በላይ) ተማሪዎችን ከክልሎች ደግሞ ሐረር 337 እና ኦሮሚያ 8ሺ በላይ ተማሪዎች ማለፋቸውን እንዲሁም ሁሉም ክልሎች ከአምናው የተሻለ ተማሪዎችን ማሳለፋቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
  • በዘንድሮ ዓመትም የሬሜዲያል ፈተና የሚኖር ሲሆን የተፈታኞች ቁጥር ግን ከአምናው ቁጥር እንደሚቀንስ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡
  • ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ሀገራዊ አማካኝ ውጤት (mean) 29.76 በመቶ መሆኑን ጠቅሰው÷ የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት ከ700ው 675 መሆኑን እና ይህም በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘ ከፍተኛ ውጤት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
  • ከፍተኛ አማካይ ውጤት (66.1 በመቶ) የተመዘገበው በአዳሪ ትምህርት ቤቶች መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡
  • ከፍተኛ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ትምህርት ቤቶች፤
    • አዳሪ ትምህርት ቤቶች
    • ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች
    • የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች
    • መንግሥታዊ ያልሆኑ ትምህርት ቤቶች
  • የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በኦንላይን እና በወረቀት የተሰጠ ሲሆን፤ ፈተናውን በኦንላይን ከወሰዱት መካከል 26.6 በመቶ የሚሆኑት የማለፊያ ውጤት አምጥተዋል።
  • ዘንድሮ 30 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን የወሰዱ ሲሆን፤ በቀጣይ ዓመት እስከ 150 ሺህ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናውን እንዲወስዱ ለማድረግ ዕቅድ ይዘናል።
  • “በ2016 ትምህርት ዘመን በወረቀትና በበይነ መረብ የተሰጠው ፈተና ውጤት እንድምታው ሲታይ ከ2014 ዓ/ም 30,034 (3.3%) ፣ ከ2015 ዓ/ም 27,267 (3.2%) … (ዘንድሮ 5.4%) መሆኑ እያሽቆለቆለ እየሄደ ያለው ጉዞ የተገታ እና መጠነኛ የመሻሻል አዝማሚያ ያሳየ ቢሆንም አሁንም 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተፈታኞች ቁጥር በጣም ዝቅተኛ ነው” በማለት ሚኒስትሩ በመግለጫቸው ተናግረዋል።
  • በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የነበረው የደንብ መተላለፍ ከአለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ እንደነበርም አንስተዋል፡፡
    • የደንብ ጥሰት የፈጸሙ 313 ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ውጤታቸው እንደተሰረዘ ገልጸዋል።
  • በአማራ ክልል በተለያዩ ምክንያቶች ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች ከመስከረም 13 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ፈተና እንደሚወስዱ የትምህርት ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Social Tagged With: berhanu nega, ESLCE, Exam result 12th grade, ministry of education, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule