• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም

October 10, 2023 01:51 pm by Editor Leave a Comment

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የ2015 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አስመልክተው ትላንት መግለጫ ሰጥተዋል።

  • በአጠቃላይ በ2015 ዓ.ም ከተፈተኑ ተማሪዎች 3.2 በመቶ ብቻ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት አምጥተዋል።
  • በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ ለፈተና ከተቀመጡ በድምሩ 845,677 ተማሪዎች 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡት 27, 267 ተማሪዎች ብቻ ናቸው።
  • በዚህም 160 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎችን በሬሜዲያል ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚቀበሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል።
  • የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች፤ 1,328 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አለመቻላቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
  • 376 ተፈታኞች በቡድን፤ 483 ተፈታኞች ደግሞ በግል ጥፋት ፈጽመዋል
  • ጥፋቶቹም፤
    ለሌላ ሰው ለመፈተን መሞከር
    የፈተና ወረቀት ቀይሮ ለማስገባት መሞከር
    መኮራረጅ
    በግልና በቡድን መረበሽ
    ያለፈቀዱ ቁሳቁሶች ይዞ መግባት ናቸው።
  • ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ2014 ዓም 20,170 ተፈታኞች ጥሰት የፈጸሙት ሲሆኑ በ2015 ዓም ግን 859 ተፈታኞች ብቻ ናቸው
  • የታየው ለውጥ የሚበረታታ ነው (95% ነው የሌብነት ቁጥሩ የቀነሰው)
  • ተማሪዎችም ሌብነት እንደማያዋጣ የተገነዘቡ መሆናቸውን ያመላከተ ነው
  • “አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ አሳልፈዋል።”
  • “ሌሎች አምስት ትምህርት ቤቶች ድግሞ ካስፈተኗቸው ውስጥ 95 ከመቶ ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል።”

ከፍተኛ አፈጻጻም ያሳዩ አስር ትምህርት ቤቶች (በደረጃ)፦
1. አዲስ አለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት (ደብረ ማርቆስ)
2. ደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት
3. ባህርዳር ስቴም (STEM) ትምህርት ቤት
4. ሀይራንዚ አዳሪ ትምህርት ቤት (ስልጤ ዞን)
5. ሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት (ሀድያ)
6. ኦዳ አዳሪ ትምህርት ቤት (ናዝሬት)
7. ኮተቤ ሼርድ ካምፓስ
8. የኔታ አካዳሚ
9. ወላይታ ሊቃ አዳሪ ትምህርት ቤት
10. ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት

  • በተፈጥሮ ሳይንስ መስክ 200 ተማሪዎች ከ600 በላይ ውጤት አምጥተዋል።
  • በማህበራዊ ሳይንስ መስክ 15 ተማሪዎች ብቻ ከ500 በላይ ውጤት አምጥተዋል።
  • በተፈጥሮ ሳይንስ ከፍተኛው ውጤት 649 ሲሆን በአዲስ አበባ የልደታ ክሩዝ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት።
  • በማህበራዊ ሳይንስ ከፍተኛው ውጤት 533 ሲሆን የደብረ ማርቆስ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ነው።
  • በከተማ ደረጃ አዲስ አበባ፣ ሀረሪ እና ድሬዳዋ የተሻለ አፈጻጸም ያሳዩ ከተሞች ናቸው።
  • በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው አማካይ ውጤት 28.65 ከመቶ ነው። አንድ ተማሪ በአማካኝ ከመቶ ያገኘው ውጤት ማለት ነው።ይህ ማለት አንድ ተማሪ በአቦ ሰጥ ምንም ሳያስብ ፈተናውን ቢሠራ የሚያመጣው ውጤት ነው።
  • ከፍተኛው ውጤት 30.99 ከመቶ በኬሚስትሪ ትምህርት ሲሆን ዝቅተኛው 25.62 በመቶ በማህበራዊ ሳይንስ ሒሳብ ትምህርት የተመዘገበ ነው።
  • ሀገራዊ አማካይ ውጤቱ ከጾታ አንጻር ሲታይ የወንዶች አማካይ ውጤት 29.55 ከመቶ ሲሆን የሴቶች ደግሞ 27.64 ከመቶ ሆኗል።

ሀናን ናጂ አህመድ

በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው የክሩዝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት።

ተማሪ ሀናን ናጂ አህመድ በተፈጥሮ ሳይንስ 649 ውጤት በማስመዝገብ ከዘንድሮ ተፈታኞች በቀዳሚነት ተቀምጣለች።

ባስመዘገበችው ውጤት በጣም ደስተኛ መሆኗን የገለጸችው ተማሪ ሀናን፤ በቀጣይም ለበለጠ ውጤት እንደመትተጋ ተናግራለች።

ክሩዝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኝ የግል ትምህርት ቤት ነው።

ወላይታ ሊቃ

ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ካስመዘገቡ አስር ትምህርት ቤቶች መካከል 9ኛ ደረጃ አጊኝቷል።

ትምህርት ቤቱ በ2015 ዓ.ም ካስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ውጤት ያመጡት፦
• ከ600-623 ➧3 ተማሪዎች
• ከ500-599 ➧ 26 ተማሪዎች
• ከ400-499 ➧ 31 ተማሪዎች
• ከ350-399 ➧ 12 ተማሪዎች
• ከ324-345 ➧ 4 ተማሪዎች

  • በትምህርትትምህርት ቤቱ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 623 መሆኑ ተግልጿል።
  • “የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ግንቦት ወር ይሠጣል።”
  • “ከሰኔ ጀምሮ ለሦሥት ወራት ዩኒቨርሲቲዎች የክረምት ትምህርት ይሰጣሉ።”

“በሚቀጥለው ዓመት የሚሰጠው ፈተና ድብልቅ ፈተና ይሆናል። ግማሹን በኦንላይን፣ የኢንተርኔት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ደግሞ በአካል ይሰጣል።” @tikvahuniversity

ይህ ያለንበትን ሁኔታ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ፤ ለምን በማሰብ እና በዕውቀት እንደማንመራ የሚያሳይ፤ ለምን ሌብነት የተንሰራፋባት አገር እንደሆንን፤ ዘረኝነት ለምን የሙጢኝ ብለን እንደያዝን፤ በማኅበራዊ ሚዲያ በየዕለቱ የሚዋሹንን ሳናገናዝብ እንደምንሰማ፤ የወሬ ሰለባ ለምን እንደሆንን፤ ወዘተ ባጠቃላይ የማንነታችን መገለጫ ይህ በያመቱ የሚወጣ ፈተና ውጤት ነው። ጥያቄው ያ ሁሉ በመቶ ሺህ የሚቆጠር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት አጠናቀቀ ተብሎ በየዩኒቨርሲቲው ተመርቆ ሲወጣ የነበረባት አገር ምነው አሁን ከምታስፈትነው ውስጥ ከ3በመቶ ያላለፈ ተማሪ ለዪኒቨርሲቲ ማብቃት አቃታት?

መዘንጋት የሌለበት ሐቅ ይህ ሁኔታ ጀመረ እንጂ አያቆምም፤ ላለፉት 30 ዓመታት ሲፈርስ የነበረ ተቋም ባንድ ጀምበር ተዓምር አይሠራም፤ የሚቀጥለው ዓመትም ውጤት ከዚህ የሚለይ አይደለም። አሁን ዘጠነኛ ክፍል ያሉት ተማሪዎች ወደ 10ኛ ክፍል ሲደርሱ ነው ለውጥ ማየት የምንጀምረው። የትሕነግ ወንበዴዎችን መርቶ ለሥልጣን ያበቃው የምዕራባውያን ድጋፍና የ30 ዓመታት የትሕነግ የክፋት መርዝ በቶሎ የሚለቅ አይደለም። በትንሹ አንድ ትውልድ አክሽፎ እና ቀጣይ ትውልዶችን መርዞ ነው ያለፈው። ይህ እስከሚጸዳ ዓመታት የግድ መውሰዱ አይቀርም። የተጀመረው ተሃድሶ ሳይደናቀፍ ማስቀጠል መቻል በራሱ ታላቅ ዕድል ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Social Tagged With: berhanu nega, ESLCE, Ethiopian Education, Ethiopian School Leaving Certificate Exam, ministry of education

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule