• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም

October 10, 2023 01:51 pm by Editor Leave a Comment

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የ2015 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አስመልክተው ትላንት መግለጫ ሰጥተዋል።

  • በአጠቃላይ በ2015 ዓ.ም ከተፈተኑ ተማሪዎች 3.2 በመቶ ብቻ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት አምጥተዋል።
  • በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ ለፈተና ከተቀመጡ በድምሩ 845,677 ተማሪዎች 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡት 27, 267 ተማሪዎች ብቻ ናቸው።
  • በዚህም 160 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎችን በሬሜዲያል ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚቀበሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል።
  • የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች፤ 1,328 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አለመቻላቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
  • 376 ተፈታኞች በቡድን፤ 483 ተፈታኞች ደግሞ በግል ጥፋት ፈጽመዋል
  • ጥፋቶቹም፤
    ለሌላ ሰው ለመፈተን መሞከር
    የፈተና ወረቀት ቀይሮ ለማስገባት መሞከር
    መኮራረጅ
    በግልና በቡድን መረበሽ
    ያለፈቀዱ ቁሳቁሶች ይዞ መግባት ናቸው።
  • ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ2014 ዓም 20,170 ተፈታኞች ጥሰት የፈጸሙት ሲሆኑ በ2015 ዓም ግን 859 ተፈታኞች ብቻ ናቸው
  • የታየው ለውጥ የሚበረታታ ነው (95% ነው የሌብነት ቁጥሩ የቀነሰው)
  • ተማሪዎችም ሌብነት እንደማያዋጣ የተገነዘቡ መሆናቸውን ያመላከተ ነው
  • “አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ አሳልፈዋል።”
  • “ሌሎች አምስት ትምህርት ቤቶች ድግሞ ካስፈተኗቸው ውስጥ 95 ከመቶ ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል።”

ከፍተኛ አፈጻጻም ያሳዩ አስር ትምህርት ቤቶች (በደረጃ)፦
1. አዲስ አለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት (ደብረ ማርቆስ)
2. ደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት
3. ባህርዳር ስቴም (STEM) ትምህርት ቤት
4. ሀይራንዚ አዳሪ ትምህርት ቤት (ስልጤ ዞን)
5. ሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት (ሀድያ)
6. ኦዳ አዳሪ ትምህርት ቤት (ናዝሬት)
7. ኮተቤ ሼርድ ካምፓስ
8. የኔታ አካዳሚ
9. ወላይታ ሊቃ አዳሪ ትምህርት ቤት
10. ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት

  • በተፈጥሮ ሳይንስ መስክ 200 ተማሪዎች ከ600 በላይ ውጤት አምጥተዋል።
  • በማህበራዊ ሳይንስ መስክ 15 ተማሪዎች ብቻ ከ500 በላይ ውጤት አምጥተዋል።
  • በተፈጥሮ ሳይንስ ከፍተኛው ውጤት 649 ሲሆን በአዲስ አበባ የልደታ ክሩዝ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት።
  • በማህበራዊ ሳይንስ ከፍተኛው ውጤት 533 ሲሆን የደብረ ማርቆስ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ነው።
  • በከተማ ደረጃ አዲስ አበባ፣ ሀረሪ እና ድሬዳዋ የተሻለ አፈጻጸም ያሳዩ ከተሞች ናቸው።
  • በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው አማካይ ውጤት 28.65 ከመቶ ነው። አንድ ተማሪ በአማካኝ ከመቶ ያገኘው ውጤት ማለት ነው።ይህ ማለት አንድ ተማሪ በአቦ ሰጥ ምንም ሳያስብ ፈተናውን ቢሠራ የሚያመጣው ውጤት ነው።
  • ከፍተኛው ውጤት 30.99 ከመቶ በኬሚስትሪ ትምህርት ሲሆን ዝቅተኛው 25.62 በመቶ በማህበራዊ ሳይንስ ሒሳብ ትምህርት የተመዘገበ ነው።
  • ሀገራዊ አማካይ ውጤቱ ከጾታ አንጻር ሲታይ የወንዶች አማካይ ውጤት 29.55 ከመቶ ሲሆን የሴቶች ደግሞ 27.64 ከመቶ ሆኗል።

ሀናን ናጂ አህመድ

በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው የክሩዝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት።

ተማሪ ሀናን ናጂ አህመድ በተፈጥሮ ሳይንስ 649 ውጤት በማስመዝገብ ከዘንድሮ ተፈታኞች በቀዳሚነት ተቀምጣለች።

ባስመዘገበችው ውጤት በጣም ደስተኛ መሆኗን የገለጸችው ተማሪ ሀናን፤ በቀጣይም ለበለጠ ውጤት እንደመትተጋ ተናግራለች።

ክሩዝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኝ የግል ትምህርት ቤት ነው።

ወላይታ ሊቃ

ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ካስመዘገቡ አስር ትምህርት ቤቶች መካከል 9ኛ ደረጃ አጊኝቷል።

ትምህርት ቤቱ በ2015 ዓ.ም ካስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ውጤት ያመጡት፦
• ከ600-623 ➧3 ተማሪዎች
• ከ500-599 ➧ 26 ተማሪዎች
• ከ400-499 ➧ 31 ተማሪዎች
• ከ350-399 ➧ 12 ተማሪዎች
• ከ324-345 ➧ 4 ተማሪዎች

  • በትምህርትትምህርት ቤቱ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 623 መሆኑ ተግልጿል።
  • “የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ግንቦት ወር ይሠጣል።”
  • “ከሰኔ ጀምሮ ለሦሥት ወራት ዩኒቨርሲቲዎች የክረምት ትምህርት ይሰጣሉ።”

“በሚቀጥለው ዓመት የሚሰጠው ፈተና ድብልቅ ፈተና ይሆናል። ግማሹን በኦንላይን፣ የኢንተርኔት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ደግሞ በአካል ይሰጣል።” @tikvahuniversity

ይህ ያለንበትን ሁኔታ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ፤ ለምን በማሰብ እና በዕውቀት እንደማንመራ የሚያሳይ፤ ለምን ሌብነት የተንሰራፋባት አገር እንደሆንን፤ ዘረኝነት ለምን የሙጢኝ ብለን እንደያዝን፤ በማኅበራዊ ሚዲያ በየዕለቱ የሚዋሹንን ሳናገናዝብ እንደምንሰማ፤ የወሬ ሰለባ ለምን እንደሆንን፤ ወዘተ ባጠቃላይ የማንነታችን መገለጫ ይህ በያመቱ የሚወጣ ፈተና ውጤት ነው። ጥያቄው ያ ሁሉ በመቶ ሺህ የሚቆጠር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት አጠናቀቀ ተብሎ በየዩኒቨርሲቲው ተመርቆ ሲወጣ የነበረባት አገር ምነው አሁን ከምታስፈትነው ውስጥ ከ3በመቶ ያላለፈ ተማሪ ለዪኒቨርሲቲ ማብቃት አቃታት?

መዘንጋት የሌለበት ሐቅ ይህ ሁኔታ ጀመረ እንጂ አያቆምም፤ ላለፉት 30 ዓመታት ሲፈርስ የነበረ ተቋም ባንድ ጀምበር ተዓምር አይሠራም፤ የሚቀጥለው ዓመትም ውጤት ከዚህ የሚለይ አይደለም። አሁን ዘጠነኛ ክፍል ያሉት ተማሪዎች ወደ 10ኛ ክፍል ሲደርሱ ነው ለውጥ ማየት የምንጀምረው። የትሕነግ ወንበዴዎችን መርቶ ለሥልጣን ያበቃው የምዕራባውያን ድጋፍና የ30 ዓመታት የትሕነግ የክፋት መርዝ በቶሎ የሚለቅ አይደለም። በትንሹ አንድ ትውልድ አክሽፎ እና ቀጣይ ትውልዶችን መርዞ ነው ያለፈው። ይህ እስከሚጸዳ ዓመታት የግድ መውሰዱ አይቀርም። የተጀመረው ተሃድሶ ሳይደናቀፍ ማስቀጠል መቻል በራሱ ታላቅ ዕድል ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, Social Tagged With: berhanu nega, ESLCE, Ethiopian Education, Ethiopian School Leaving Certificate Exam, ministry of education

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule