በኢትዮጵያ ጥልቅ አሳቢና ሩቅ አላሚ ትውልድ ለመፍጠር የንባብ ባህልን ማዳበር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥበባትና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሳ ገለጹ። የንባብ ባህልን ለማጎልበት ጥረት ቢደረግም የአንባቢው ቁጥር እስካሁን የሚታሰበውን ያክል አልደረሰም ብለዋል። “ንባብ ለሠላምና ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል” መሪ ሃሳብ በአብርኆት ቤተ-መጻሕፍት ከየካቲት 9 እስከ የካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም የሚቆይ የንባብ ባህል ሳምንት ተጀምሯል። ለ4ተኛ ጊዜ በተካሄደው የንባብ ባህል ሳምንት ላይ የተገኙት ዶ/ር ሂሩት ካሳ፤ የንባብ ባህልን ለማጎልበት ጥረት ቢደረግም የአንባቢው ቁጥር የሚታሰበውን ያክል አልጨመረም ብለዋል። በንባብ ሳምንት ዝግጅቱ ላይ በርካታ አንባቢያን እንዲሳተፉ የተለያዩ ማነቃቂያዎች ቢደረጉም በርካታ አንባቢዎችን ለማፍራት አለመቻሉን … [Read more...] about የትግሬ ወራሪ ለ፳፯ ዓመት ያደነቆረውን ትውልድ ለመታደግ አዲስ የጸረ መሃይምነት ዘመቻ ሊጀመር ይገባል