• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትግሬ ወራሪ ለ፳፯ ዓመት ያደነቆረውን ትውልድ ለመታደግ አዲስ የጸረ መሃይምነት ዘመቻ ሊጀመር ይገባል

February 17, 2022 12:22 pm by Editor 1 Comment

በኢትዮጵያ ጥልቅ አሳቢና ሩቅ አላሚ ትውልድ ለመፍጠር የንባብ ባህልን ማዳበር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥበባትና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሳ ገለጹ።

የንባብ ባህልን ለማጎልበት ጥረት ቢደረግም የአንባቢው ቁጥር እስካሁን የሚታሰበውን ያክል አልደረሰም ብለዋል።

“ንባብ ለሠላምና ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል” መሪ ሃሳብ በአብርኆት ቤተ-መጻሕፍት ከየካቲት 9 እስከ የካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም የሚቆይ የንባብ ባህል ሳምንት ተጀምሯል።

ለ4ተኛ ጊዜ በተካሄደው የንባብ ባህል ሳምንት ላይ የተገኙት ዶ/ር ሂሩት ካሳ፤ የንባብ ባህልን ለማጎልበት ጥረት ቢደረግም የአንባቢው ቁጥር የሚታሰበውን ያክል አልጨመረም ብለዋል።

በንባብ ሳምንት ዝግጅቱ ላይ በርካታ አንባቢያን እንዲሳተፉ የተለያዩ ማነቃቂያዎች ቢደረጉም በርካታ አንባቢዎችን ለማፍራት አለመቻሉን ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የፓርትነርሺፕና የምርምር ግራንት አማካሪ ፕሮፌሰር ሐረገወይን አሰፋ በበኩላቸው፤ ንባብ የሰው ልጅ ታሪኩን፣ ማኅበራዊና ባህላዊ አኗኗሩን የሚገልፅበት መንገድ እንደሆነ ገልጸዋል።

በመሆኑም ማንበብ ሙሉ ሰው ስለሚያደርግ ሰዎች የንባብ ባህልን ማዳበርና ልምድ ማድረግ አለባቸው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። (አዲስ ሚዲያ)

በቀድሞው አገዛዝ ዘመን ከተደረጉ ዋንኛ ስኬቶች መካከል የጸረ መሃይምነት ዘመቻ ዋና ተጠቃሽ ነው። ይህ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖችን ከመሃይምነት ጥቁር መጋረጃ ነጻ ያወጣ ዘመቻ አሁንም ላለፉት ፳፯ ዓመታት የትግሬ ወራሪ ቡድን ራሱ ደንቁሮ የአገራችንን ሕዝብ ለከፋ የመሃይምነት አደጋ እንዳጋለጠው ጎልጉል ያምናል። ይህም ድንቁርና አሁን ለሚታየው የአስተሳሰብ፣ የአመለካከት መቀንጨር እንዳጋለጠን ማስረጃ አቅርቦ መሞገት ይቻላል። ስለዚህ መንግሥትም ሆን የከተማ እና የክልል መስተዳድሮች በዚህ ላይ በመምከር አንድ ወጥ አገራዊ ዘመቻ እንዲያስተባብሩ ጎልጉል ጥሪ ያቀርባል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Right Column Tagged With: Ethiopian Education, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Assefa says

    March 20, 2022 06:59 pm at 6:59 pm

    Subscribe me

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule