ባንኮች በኢኮኖሚው ላይ እያደረጉ ካሉት አስተዋጽኦ ባሻገር ዘመናዊ ህንጻ በመገንባትም የላቀ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ተናገሩ። ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በ2 ቢሊየን ብር ያስገነባውን ዘመናዊ ህንጻ ዶ/ር ይናገር ደሴ በተገኙበት ዛሬ አስመርቋል። ብሔራዊ ባንክ ለባንኮች ውጤታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የተናገሩት ገዥው ቢዘገይም የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው ስለማይቀር ከአሁኑ ጠንካራ መሆንና ተወዳዳሪ ለመሆን መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በፋይናንሥ ዘርፉ የሚጠበቅበትን ለማበርከት የጀመረውን ፕሮጀክት በታሠበው ጊዜና ወጭ ማጠናቀቁን የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ ገነነ ሩጋ ተናግረዋል። የተገነባው ባለ 37 ወለል ዘመናዊ ህንጻ የንብ ባህላዊ ቀፎና የማር እንጀራን ቅርጽ እንዲኖረው … [Read more...] about ባንኮች ከኢኮኖሚው አበርክቶ ባለፈ በህንጻ ግንባታም የላቀ ሚና እየተጫወቱ ነው ተባለ
national bank of ethiopia
ከ69 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከመመሪያ ውጪ ከኢትዮጵያ ባንክ መባከኑ በሰነድ ተረጋገጠ
* የመለስ ፋውንዴሽን 100 ሺ ዶላር ወስዷል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ሥልጣን በያዙ ማግስት የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ካዝና ክፉኛ ተመዝብሮ ባዶ እንደነበር ተናግረው ነበር። እርሳቸውም ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ ደንብና መመሪያ ውጭ ሲባክን እንደ ነበር ሸገር ያገኘው አንድ ሰነድ ያስረዳል። ከለውጡ ወዲህ ባሉ ጊዜያትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ ውጭ ለማይፈቀድላቸው እንደሰጠ ሸገር ካገኘው ሰነድ ተረድቷል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአቶ በቃሉ ዘለቀ ይመራ በነበረበት በ2010 ዓመት ከግንቦት እስከ ነሐሴ ከባንኩ በትንሹ ከ69 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ (የውጭ ምንዛሪ) ከመመሪያ ውጪ ለተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች እንደተሰጡ ከሰነዱ አንብበናል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ … [Read more...] about ከ69 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከመመሪያ ውጪ ከኢትዮጵያ ባንክ መባከኑ በሰነድ ተረጋገጠ