• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ69 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከመመሪያ ውጪ ከኢትዮጵያ ባንክ መባከኑ በሰነድ ተረጋገጠ

September 18, 2020 10:16 am by Editor Leave a Comment

* የመለስ ፋውንዴሽን 100 ሺ ዶላር ወስዷል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ሥልጣን በያዙ ማግስት የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ካዝና ክፉኛ ተመዝብሮ ባዶ እንደነበር ተናግረው ነበር።

እርሳቸውም ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ ደንብና መመሪያ ውጭ ሲባክን እንደ ነበር ሸገር ያገኘው አንድ ሰነድ ያስረዳል።

ከለውጡ ወዲህ ባሉ ጊዜያትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ ውጭ ለማይፈቀድላቸው እንደሰጠ ሸገር ካገኘው ሰነድ ተረድቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአቶ በቃሉ ዘለቀ ይመራ በነበረበት በ2010 ዓመት ከግንቦት እስከ ነሐሴ ከባንኩ በትንሹ ከ69 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ (የውጭ ምንዛሪ) ከመመሪያ ውጪ ለተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች እንደተሰጡ ከሰነዱ አንብበናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ ድልድልን አስመልክቶ በተጠቀሰው ጊዜ ከ3 ዓመት በፊት ያወጣውን መመሪያ ንግድ ባንኩ በከፍተኛ ደረጃ ሲጥስ እንደነበር ይኸው ሰነድ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጪ ሀገር ገንዘብ ወይም የውጪ ምንዛሪ ድልድልን አስመልክቶ ያወጣው መመሪያ ቁጥር FXD/51/2017 ለኮንስትራክሽን ድርጅቶች የግንባታ ማሽኖች መለዋወጫ ለማስገባት ለአንድ የግዢ ማቅረቢያ ከ50,000 የማይበልጥ የአሜሪካ ዶላር እንዲመደብ ቢፈቅድም መመሪያው ከወጣ በኋላ በተለያዩ ጊዜያት ማለትም በ1ኛው ወቅት በቁጥር 36 ለሚሆኑ በሌላኛ ወቅት ደግሞ 46 ለሚሆኑ የውጭ  ምንዛሪ ጠያቂዎች ለእያንዳንዳቸው ከመመሪያው ውጪ ከ50,000 የአሜሪካ ዶላር በላይ ተመድቦላቸው ወይም ተሰጥቷቸው እንደነበር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ከራሱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወጣውና በባንኩ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ ባጫ ጊና የተፈረመበት ይኸው ሰነድ እንደሚያስረዳው ከሆነ እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በመጋቢት 2018፤

ሠላሳ ስድስት ለሚሆኑ የውጪ ምንዛሪ ጠያቂዎች ለእያንዳንዳቸው ከመመሪያ ውጪ ከ50,000 ዶላር በላይ በድምሩ 19 ሚሊዮን 886 ሺ 137 የአሜሪካ ዶላር፤

በነሐሴ ወር 2018 ደግሞ ለ46 የውጪ ምንዛሪ ጠያቂዎች በድምሩ 27 ሚሊዮን 648 ሺ 788 የአሜሪካ ዶላር እንደተመደበላቸው ያሳያል፤

በዚሁ ዓመት በግንቦት ወር 2018 መመሪያው የውጪ ምንዛሪ እንዳያገኙ ከፈቀደላቸው የስራ ዘርፍ ውጪ ላሉ ወይም መመሪያው ለማይመለከታቸው ቢያንስ ሸገር የሚያውቃቸው 5 ድርጅቶች በድምሩ 11 ሚሊዮን 847 ሺ 583 የአሜሪካ ዶላር እንደተሰጠ ሰነዱ ያስረዳል።

ከእነዚህ ድርጅቶች ውስጥ፤

  • ለመለስ ፋውንዴሽን 100 ሺ ዶላር፣
  • ለኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ 66 ሺህ 750 ዶላር ፣
  • ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ሴንተር 500 ሺ የአሜሪካ ዶላር
  • ለኢዮሃ ፕሪንተር 27 ሺህ ዶላር እና
  • ለብርሃኔ ወልዱ 140 ሺ 800 ዶላር መፈቀዱን ሸገር ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ባንኩ በተመሳሳይ ጊዜ ማለትም በግንቦት 2010 በቁጥር 10 ለሚሆኑ መኪና አቅራቢዎች ከብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ ድልድል መመሪያው ውጪ ለመለዋወጫ ማስመጫ አስር ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ንግድ ባንኩ እንደሰጠ በዚሁ ሰነድ ተመልክተናል።

በአቶ በቃሉ ዘለቀ እግር አቶ ባጫ ጊና ከተተኩ በኋላ የተፈፀመው አሰራር እና የውጭ ምንዛሪ ብክነት ተጣርቶ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ በየካቲት ወር 2011 ለጠቅላይ አቃቤ ህግ ማሳወቃቸውን  ሸገር ካገኘው ሰነድ ተመልክቷል።

ሸገር የተፈፀመውን ህገ ወጥ የውጪ ምንዛሪ ብክነት አስመልክቶ ጉዳዩ የሚመለከተው ህግ አስፈፃሚ አካል አስፈላጊውን ምርመራ እንዲያካሂድ ባንኩ ደብዳቤ የፃፈው በየካቲት ወር 2011 ማለትም ከዛሬ 1 ዓመት ከ6 ወር በፊት መሆኑን ታሳቢ በማድረግ፤ በጉዳዩ ላይ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ምን እርምጃ ወስዶ ይሆን? ሲል የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግን ጠይቋል።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ም/ል አቃቤ ህግ ለሆኑት አቶ ፍቃዱ ፀጋ ጉዳዩን አብራርተን ምን እርምጃ እየተወሰደ ነው ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ እሳቸው በምክትል አቃቤ ህግ ማዕረግ የተሾሙት በቅርቡ መሆኑን ተናግረው ጉዳዩ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አጣርቼ እነግራችኋለሁ ብለውናል።

ሸገር በዚሁ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖን መልስ አካቶ በሌላ የወሬ ግዜ ለመመለስ ይጥራል።

ይህ ከ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ  ውጭ ተፈፀመ የተባለው የውጭ ምንዛሪ  ብክነት ተግባራዊ በተደረገበት ወቅት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ይመሩ የነበሩት አቶ በቃሉ ዘለቀ እንደነበሩ ሸገር ለማወቅ ችሏል። (@ ተህቦ ንጉሴ፤ ሸገር 102.1)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: commercial bank of ethiopia, meles foundation, national bank of ethiopia, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule