• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ69 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከመመሪያ ውጪ ከኢትዮጵያ ባንክ መባከኑ በሰነድ ተረጋገጠ

September 18, 2020 10:16 am by Editor Leave a Comment

* የመለስ ፋውንዴሽን 100 ሺ ዶላር ወስዷል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ሥልጣን በያዙ ማግስት የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ካዝና ክፉኛ ተመዝብሮ ባዶ እንደነበር ተናግረው ነበር።

እርሳቸውም ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ ደንብና መመሪያ ውጭ ሲባክን እንደ ነበር ሸገር ያገኘው አንድ ሰነድ ያስረዳል።

ከለውጡ ወዲህ ባሉ ጊዜያትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ ውጭ ለማይፈቀድላቸው እንደሰጠ ሸገር ካገኘው ሰነድ ተረድቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአቶ በቃሉ ዘለቀ ይመራ በነበረበት በ2010 ዓመት ከግንቦት እስከ ነሐሴ ከባንኩ በትንሹ ከ69 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ (የውጭ ምንዛሪ) ከመመሪያ ውጪ ለተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች እንደተሰጡ ከሰነዱ አንብበናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ ድልድልን አስመልክቶ በተጠቀሰው ጊዜ ከ3 ዓመት በፊት ያወጣውን መመሪያ ንግድ ባንኩ በከፍተኛ ደረጃ ሲጥስ እንደነበር ይኸው ሰነድ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጪ ሀገር ገንዘብ ወይም የውጪ ምንዛሪ ድልድልን አስመልክቶ ያወጣው መመሪያ ቁጥር FXD/51/2017 ለኮንስትራክሽን ድርጅቶች የግንባታ ማሽኖች መለዋወጫ ለማስገባት ለአንድ የግዢ ማቅረቢያ ከ50,000 የማይበልጥ የአሜሪካ ዶላር እንዲመደብ ቢፈቅድም መመሪያው ከወጣ በኋላ በተለያዩ ጊዜያት ማለትም በ1ኛው ወቅት በቁጥር 36 ለሚሆኑ በሌላኛ ወቅት ደግሞ 46 ለሚሆኑ የውጭ  ምንዛሪ ጠያቂዎች ለእያንዳንዳቸው ከመመሪያው ውጪ ከ50,000 የአሜሪካ ዶላር በላይ ተመድቦላቸው ወይም ተሰጥቷቸው እንደነበር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ከራሱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወጣውና በባንኩ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ ባጫ ጊና የተፈረመበት ይኸው ሰነድ እንደሚያስረዳው ከሆነ እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በመጋቢት 2018፤

ሠላሳ ስድስት ለሚሆኑ የውጪ ምንዛሪ ጠያቂዎች ለእያንዳንዳቸው ከመመሪያ ውጪ ከ50,000 ዶላር በላይ በድምሩ 19 ሚሊዮን 886 ሺ 137 የአሜሪካ ዶላር፤

በነሐሴ ወር 2018 ደግሞ ለ46 የውጪ ምንዛሪ ጠያቂዎች በድምሩ 27 ሚሊዮን 648 ሺ 788 የአሜሪካ ዶላር እንደተመደበላቸው ያሳያል፤

በዚሁ ዓመት በግንቦት ወር 2018 መመሪያው የውጪ ምንዛሪ እንዳያገኙ ከፈቀደላቸው የስራ ዘርፍ ውጪ ላሉ ወይም መመሪያው ለማይመለከታቸው ቢያንስ ሸገር የሚያውቃቸው 5 ድርጅቶች በድምሩ 11 ሚሊዮን 847 ሺ 583 የአሜሪካ ዶላር እንደተሰጠ ሰነዱ ያስረዳል።

ከእነዚህ ድርጅቶች ውስጥ፤

  • ለመለስ ፋውንዴሽን 100 ሺ ዶላር፣
  • ለኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ 66 ሺህ 750 ዶላር ፣
  • ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ሴንተር 500 ሺ የአሜሪካ ዶላር
  • ለኢዮሃ ፕሪንተር 27 ሺህ ዶላር እና
  • ለብርሃኔ ወልዱ 140 ሺ 800 ዶላር መፈቀዱን ሸገር ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ባንኩ በተመሳሳይ ጊዜ ማለትም በግንቦት 2010 በቁጥር 10 ለሚሆኑ መኪና አቅራቢዎች ከብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ ድልድል መመሪያው ውጪ ለመለዋወጫ ማስመጫ አስር ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ንግድ ባንኩ እንደሰጠ በዚሁ ሰነድ ተመልክተናል።

በአቶ በቃሉ ዘለቀ እግር አቶ ባጫ ጊና ከተተኩ በኋላ የተፈፀመው አሰራር እና የውጭ ምንዛሪ ብክነት ተጣርቶ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ በየካቲት ወር 2011 ለጠቅላይ አቃቤ ህግ ማሳወቃቸውን  ሸገር ካገኘው ሰነድ ተመልክቷል።

ሸገር የተፈፀመውን ህገ ወጥ የውጪ ምንዛሪ ብክነት አስመልክቶ ጉዳዩ የሚመለከተው ህግ አስፈፃሚ አካል አስፈላጊውን ምርመራ እንዲያካሂድ ባንኩ ደብዳቤ የፃፈው በየካቲት ወር 2011 ማለትም ከዛሬ 1 ዓመት ከ6 ወር በፊት መሆኑን ታሳቢ በማድረግ፤ በጉዳዩ ላይ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ምን እርምጃ ወስዶ ይሆን? ሲል የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግን ጠይቋል።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ም/ል አቃቤ ህግ ለሆኑት አቶ ፍቃዱ ፀጋ ጉዳዩን አብራርተን ምን እርምጃ እየተወሰደ ነው ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ እሳቸው በምክትል አቃቤ ህግ ማዕረግ የተሾሙት በቅርቡ መሆኑን ተናግረው ጉዳዩ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አጣርቼ እነግራችኋለሁ ብለውናል።

ሸገር በዚሁ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖን መልስ አካቶ በሌላ የወሬ ግዜ ለመመለስ ይጥራል።

ይህ ከ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ  ውጭ ተፈፀመ የተባለው የውጭ ምንዛሪ  ብክነት ተግባራዊ በተደረገበት ወቅት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ይመሩ የነበሩት አቶ በቃሉ ዘለቀ እንደነበሩ ሸገር ለማወቅ ችሏል። (@ ተህቦ ንጉሴ፤ ሸገር 102.1)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: commercial bank of ethiopia, meles foundation, national bank of ethiopia, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule