ሃራ ወይም ነጻ ተብሎ በሚጠራው መሬት ላይ ሠፍሮ የሚገኘው "የትግራይ የሰላም ኃይሎች" (TPF) ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ኃይል በያዝነው ዓመት መጨረሻ ሙሉ ትግራይን እንደሚቆጣጠር አስታወቀ። "ጸጥተኛ" ብለው ለሚጠሩት አቢዮት ሠራዊቱ እየተዘጋጀ እንደሆነም ተነግሯል። ይህ የተገለጸው በፈረንሳይኛ ቋንቋ በድረገጽ የሚታተመውና አፍሪክ XXI (Afrique XXI) የተባለው ጋዜጣ ከጥቂት ቀናት በፊት በትግራይ ላይ በሠራው ዘገባ ነው። ዘገባው በሃራ ምድር የሰፈሩትን የትግራይ የሰላም ኃይል/ቲፒኤፍ ተብለው ከሚጠሩት ታጣቂዎች ጋር ቃለ ምልልስ ካደረገ በኋላ ነው። የሰላም ኃይሉ አባላት በአብዛኛው ከዚህ በፊት በትህነግ ሥር ከነበረው የትግራይ መከላከያ ኃይል ወይም ቲዲኤፍ (TDF) ከሚባለው ከድተው የወጡ ናቸው። በተለይ ካለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ በብዛት ከቲዲኤፍ እየኮበለሉ ወደ አፋር … [Read more...] about “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ
afar
በጋምቤላ በ10 ሺህዎች በጎርፍ መጥለቅለቅ ተፈናቅለዋል
ከ18ሺህ በላይ ሰዎች ጋምቤላ ክልል ላሬ ወረዳ ውስጥ በጎርፍ መፈናቀላቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታወቁ። የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ የተከሰተበት ወረዳው ኢትዮጵያን ከሱዳን በሚያዋስን አካባቢ ነው። የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽ/ ቤት ከተፈናቃዮች መካከል ወ/ሮ ኛዳክ ፓችን ጠቅሶ እንደዘገበው ሰሞኑን እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ በፈጠረው ጎርፍ ምክናያት ቤት ንብረታቸውን ጥለው ከነቤተሰቦቻቸው በትምህርት ቤት አጥር ጊቢ ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ። መንግሥት የአልባሳትና የምግብ አቅርቦት ባለማድረጉም ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን ወ/ሮ ኛዳክ ተናግረዋል። በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን የላሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጋርዊች ቢየል በስልክ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ ሱዳንንና ኢትዮጵያን የሚያዋስነው ጂካዎ ወንዝ ሞልቶ በተፈጠረው ችግር ከ18ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል፣ የሚኖሩትም … [Read more...] about በጋምቤላ በ10 ሺህዎች በጎርፍ መጥለቅለቅ ተፈናቅለዋል
አፋር የመንግሥትንና የሕዝብን አስቸኳይ ድጋፍና እርዳታ ይሻል!
ይህን ከባድ የተፈጥሮ አደጋ በቸልታ የሚታለፍ አይደለም። አፋር የሃገራችን ዳር ድንበር ለዘመናት እየጠብቁ የቆዩ፣ የሰው ልጆችን ሁሉ በእኩልነት እና በክብር ተቀብለው የሚያስተናግዱ እንግዳ ተቀባይ እና ከሌሎች ጋር ተካፍለው መብላት ህይወታቸው የሆነ የኢትዮጵያ ውድ ህዝቦች ናቸው። እነዚህ ወገኖቻችን ባጋጠማቸው ከፍተኛ የሆነ የጎርፍ አደጋ ከ200 ሺህ ህዝብ በላይ ተፈናቅሎ የመንግስትን እና የህዝብን ድጋፍ እየጠበቁ ነው። ሰብዓዊነት ሁሉም ሊሰማው ይገባል። አንድ አካላችን ሲታመም ሁሉም አካላችን እንደሚታመም ሁሉ የአፋር ወገኖቻችን ጉዳት እና ህመም እኛንም ሊያመን ይገባል። በሌላ በኩል ፦ ጣና ሐይቅ በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩ የተነሳ ውሃው ተመልሶ በሐይቁ ዙሪያ ያሉ ቀበሌዎችን እያጥለቀለቀ ይገኛል። በዚሁ ምክንያት እስካሁን ድረስ በደንቢያ ወረዳ … [Read more...] about አፋር የመንግሥትንና የሕዝብን አስቸኳይ ድጋፍና እርዳታ ይሻል!



