• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ

March 15, 2023 12:52 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ መሰረት መንግሥት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በየዓመቱ የበጀት ድጎማ ያደርጋል፡፡ በዚሁ መሠረት የ2015 በጀት ለፖለቲካ ፓርቲዎች ለማከፋፈል በምርጫ ቦርድ ቀመር መሰረት የገንዘብ ክፍፍሉ መደልደሉን ቦርዱ አስታውቋል፡፡

ቦርዱ ይህንኑ አስመልክቶ ቅዳሜ መጋቢት 2/2015 ከፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ውይይት በአገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፓርቲዎች 65 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ መደበኛ በጀት የበጀት ሲሆን፣ ፓርቲዎች ለሚያከናውኑት የሲቪል ትምህርት 41 ሚሊዮን ብር መመደቡን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ ተናግረዋል፡፡

ፓርቲዎች የሚደርሳቸው ገንዘብ በዋና ዋና መስፈርቶች የሚመዘን ሲሆን፣ በሴት አባል ብዛት፣ በሴት አመራር ብዛት፣ በአካል ጉዳተኛ አባል ብዛትና በአካል ጉዳተኛ አመራር ብዛት ተሰልቶ የሚመደብ መሆኑ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም በእኩልነት የሚከፈልባቸው መስፈርቶች በቀድሞ ጠቅላላ ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ያላቸው ፓርቲዎች ናቸው ተብሏል፡፡

በበጀት ዓመቱ የገንዘብ ክፍፍል ውስጥ ያልገቡ ፓርቲዎች መኖራቸውን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡ በገንዘብ ክፍሉ ያልተካተቱ ፓርቲዎች ከዚህ በፊት የወሰዱትን ገንዘብ ምንም ጥቅም ላይ ያላዋሉ፣ ቦርዱ ላቀረበው የበጀት ድልድል ጥያቄ ፍላጎት ምላሽ ያልሰጡ እና የፓርቲ ገንዘብ ምዝበራ ተፈጽሞባቸዋል የተባሉ ፓርቲዎች ይገኙበታል፡፡

ፓርቲዎቹ ከዚህ በፊት የተሰጣቸውን ገንዘብ በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋላቸውን የሚያረጋግጥ እውቅና ባለው ኦዲተር አረጋግጠው ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ ገንዘቡን በአግባቡ ያልተጠቀሙ ፓርቲዎች መኖራቸውም ተጠቁሟል፡፡

ለቦርዱ የኦዲት ሪፖርት ካቀረቡ ፓርቲዎች መካከል፣ እስከ 25 በመቶ ለሚደርሰው ውጪ ማስረጃ ያላቀቡ መገኘታቸው ብርቱካን ጠቁመዋል፡፡ እንዲሁም አሳማኝ የውጪ ምክንያት ያላቀረቡ ፓርቲዎች መኖራቸውም የተጠቆመ ሲሆን፣ ከመንግሥት የተመደበን ገንዘብ በአግባቡ አለመጠቀም ቅጣት እንደሚያስከትልም ተጠቅሷል፡፡

የዘንድሮው ገንዘብ ድልድል የበጀት ዓመቱ ከሰባት ወራት በላይ ካለቀ በኋላ የሚከፋፈል ነው፡፡

በመድረኩም ፓርቲዎቹ በበጀት ድልድሉ ላይ ያላቸውን ጥያቄ ያነሱ ሲሆን፣ የገንዘብ ሥርጭቱ ዘግይቶ መምጣቱ ገንዘቡን በአግባቡ ሥራ ላይ ለማዋል እንቅፋት እንደሚሆን በማንሳት፣ ከዚህ በኋላ በበጀት ዓመት መጀመሪያ እንዲሰራጭ ጠይቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ፓርቲዎቹ ከመንግሥት የተመደበላቸውን ገንዘበ በአግባቡ ለመጠቅም የሚያስችል ነጻ የፓርቲ እንቅስቃሴ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታዎች አለመኖራቸውን እንደ ችግር አንስተዋል፡፡ በተለይም ገዥው ፓርቲ በተፎካካሪ ፓርቲዎች ላይ የሚፈጥረው የነጻነት ገደብ ፓርቲዎቹ ገንዘቡን ተጠቅመው ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ እንቅፋት መሆኑም ተነስቷል፡፡(አዲስ ማለዳ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: birtukan midekssa, Election Board

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule