• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ

March 15, 2023 12:52 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ መሰረት መንግሥት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በየዓመቱ የበጀት ድጎማ ያደርጋል፡፡ በዚሁ መሠረት የ2015 በጀት ለፖለቲካ ፓርቲዎች ለማከፋፈል በምርጫ ቦርድ ቀመር መሰረት የገንዘብ ክፍፍሉ መደልደሉን ቦርዱ አስታውቋል፡፡

ቦርዱ ይህንኑ አስመልክቶ ቅዳሜ መጋቢት 2/2015 ከፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ውይይት በአገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፓርቲዎች 65 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ መደበኛ በጀት የበጀት ሲሆን፣ ፓርቲዎች ለሚያከናውኑት የሲቪል ትምህርት 41 ሚሊዮን ብር መመደቡን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ ተናግረዋል፡፡

ፓርቲዎች የሚደርሳቸው ገንዘብ በዋና ዋና መስፈርቶች የሚመዘን ሲሆን፣ በሴት አባል ብዛት፣ በሴት አመራር ብዛት፣ በአካል ጉዳተኛ አባል ብዛትና በአካል ጉዳተኛ አመራር ብዛት ተሰልቶ የሚመደብ መሆኑ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም በእኩልነት የሚከፈልባቸው መስፈርቶች በቀድሞ ጠቅላላ ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ያላቸው ፓርቲዎች ናቸው ተብሏል፡፡

በበጀት ዓመቱ የገንዘብ ክፍፍል ውስጥ ያልገቡ ፓርቲዎች መኖራቸውን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡ በገንዘብ ክፍሉ ያልተካተቱ ፓርቲዎች ከዚህ በፊት የወሰዱትን ገንዘብ ምንም ጥቅም ላይ ያላዋሉ፣ ቦርዱ ላቀረበው የበጀት ድልድል ጥያቄ ፍላጎት ምላሽ ያልሰጡ እና የፓርቲ ገንዘብ ምዝበራ ተፈጽሞባቸዋል የተባሉ ፓርቲዎች ይገኙበታል፡፡

ፓርቲዎቹ ከዚህ በፊት የተሰጣቸውን ገንዘብ በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋላቸውን የሚያረጋግጥ እውቅና ባለው ኦዲተር አረጋግጠው ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ ገንዘቡን በአግባቡ ያልተጠቀሙ ፓርቲዎች መኖራቸውም ተጠቁሟል፡፡

ለቦርዱ የኦዲት ሪፖርት ካቀረቡ ፓርቲዎች መካከል፣ እስከ 25 በመቶ ለሚደርሰው ውጪ ማስረጃ ያላቀቡ መገኘታቸው ብርቱካን ጠቁመዋል፡፡ እንዲሁም አሳማኝ የውጪ ምክንያት ያላቀረቡ ፓርቲዎች መኖራቸውም የተጠቆመ ሲሆን፣ ከመንግሥት የተመደበን ገንዘብ በአግባቡ አለመጠቀም ቅጣት እንደሚያስከትልም ተጠቅሷል፡፡

የዘንድሮው ገንዘብ ድልድል የበጀት ዓመቱ ከሰባት ወራት በላይ ካለቀ በኋላ የሚከፋፈል ነው፡፡

በመድረኩም ፓርቲዎቹ በበጀት ድልድሉ ላይ ያላቸውን ጥያቄ ያነሱ ሲሆን፣ የገንዘብ ሥርጭቱ ዘግይቶ መምጣቱ ገንዘቡን በአግባቡ ሥራ ላይ ለማዋል እንቅፋት እንደሚሆን በማንሳት፣ ከዚህ በኋላ በበጀት ዓመት መጀመሪያ እንዲሰራጭ ጠይቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ፓርቲዎቹ ከመንግሥት የተመደበላቸውን ገንዘበ በአግባቡ ለመጠቅም የሚያስችል ነጻ የፓርቲ እንቅስቃሴ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታዎች አለመኖራቸውን እንደ ችግር አንስተዋል፡፡ በተለይም ገዥው ፓርቲ በተፎካካሪ ፓርቲዎች ላይ የሚፈጥረው የነጻነት ገደብ ፓርቲዎቹ ገንዘቡን ተጠቅመው ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ እንቅፋት መሆኑም ተነስቷል፡፡(አዲስ ማለዳ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: birtukan midekssa, Election Board

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule