• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ

March 15, 2023 12:52 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ መሰረት መንግሥት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በየዓመቱ የበጀት ድጎማ ያደርጋል፡፡ በዚሁ መሠረት የ2015 በጀት ለፖለቲካ ፓርቲዎች ለማከፋፈል በምርጫ ቦርድ ቀመር መሰረት የገንዘብ ክፍፍሉ መደልደሉን ቦርዱ አስታውቋል፡፡

ቦርዱ ይህንኑ አስመልክቶ ቅዳሜ መጋቢት 2/2015 ከፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ውይይት በአገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፓርቲዎች 65 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ መደበኛ በጀት የበጀት ሲሆን፣ ፓርቲዎች ለሚያከናውኑት የሲቪል ትምህርት 41 ሚሊዮን ብር መመደቡን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ ተናግረዋል፡፡

ፓርቲዎች የሚደርሳቸው ገንዘብ በዋና ዋና መስፈርቶች የሚመዘን ሲሆን፣ በሴት አባል ብዛት፣ በሴት አመራር ብዛት፣ በአካል ጉዳተኛ አባል ብዛትና በአካል ጉዳተኛ አመራር ብዛት ተሰልቶ የሚመደብ መሆኑ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም በእኩልነት የሚከፈልባቸው መስፈርቶች በቀድሞ ጠቅላላ ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ያላቸው ፓርቲዎች ናቸው ተብሏል፡፡

በበጀት ዓመቱ የገንዘብ ክፍፍል ውስጥ ያልገቡ ፓርቲዎች መኖራቸውን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡ በገንዘብ ክፍሉ ያልተካተቱ ፓርቲዎች ከዚህ በፊት የወሰዱትን ገንዘብ ምንም ጥቅም ላይ ያላዋሉ፣ ቦርዱ ላቀረበው የበጀት ድልድል ጥያቄ ፍላጎት ምላሽ ያልሰጡ እና የፓርቲ ገንዘብ ምዝበራ ተፈጽሞባቸዋል የተባሉ ፓርቲዎች ይገኙበታል፡፡

ፓርቲዎቹ ከዚህ በፊት የተሰጣቸውን ገንዘብ በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋላቸውን የሚያረጋግጥ እውቅና ባለው ኦዲተር አረጋግጠው ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ ገንዘቡን በአግባቡ ያልተጠቀሙ ፓርቲዎች መኖራቸውም ተጠቁሟል፡፡

ለቦርዱ የኦዲት ሪፖርት ካቀረቡ ፓርቲዎች መካከል፣ እስከ 25 በመቶ ለሚደርሰው ውጪ ማስረጃ ያላቀቡ መገኘታቸው ብርቱካን ጠቁመዋል፡፡ እንዲሁም አሳማኝ የውጪ ምክንያት ያላቀረቡ ፓርቲዎች መኖራቸውም የተጠቆመ ሲሆን፣ ከመንግሥት የተመደበን ገንዘብ በአግባቡ አለመጠቀም ቅጣት እንደሚያስከትልም ተጠቅሷል፡፡

የዘንድሮው ገንዘብ ድልድል የበጀት ዓመቱ ከሰባት ወራት በላይ ካለቀ በኋላ የሚከፋፈል ነው፡፡

በመድረኩም ፓርቲዎቹ በበጀት ድልድሉ ላይ ያላቸውን ጥያቄ ያነሱ ሲሆን፣ የገንዘብ ሥርጭቱ ዘግይቶ መምጣቱ ገንዘቡን በአግባቡ ሥራ ላይ ለማዋል እንቅፋት እንደሚሆን በማንሳት፣ ከዚህ በኋላ በበጀት ዓመት መጀመሪያ እንዲሰራጭ ጠይቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ፓርቲዎቹ ከመንግሥት የተመደበላቸውን ገንዘበ በአግባቡ ለመጠቅም የሚያስችል ነጻ የፓርቲ እንቅስቃሴ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታዎች አለመኖራቸውን እንደ ችግር አንስተዋል፡፡ በተለይም ገዥው ፓርቲ በተፎካካሪ ፓርቲዎች ላይ የሚፈጥረው የነጻነት ገደብ ፓርቲዎቹ ገንዘቡን ተጠቅመው ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ እንቅፋት መሆኑም ተነስቷል፡፡(አዲስ ማለዳ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: birtukan midekssa, Election Board

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule