• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ

March 15, 2023 12:52 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ መሰረት መንግሥት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ላገኙ ፖለቲካ ፓርቲዎች በየዓመቱ የበጀት ድጎማ ያደርጋል፡፡ በዚሁ መሠረት የ2015 በጀት ለፖለቲካ ፓርቲዎች ለማከፋፈል በምርጫ ቦርድ ቀመር መሰረት የገንዘብ ክፍፍሉ መደልደሉን ቦርዱ አስታውቋል፡፡

ቦርዱ ይህንኑ አስመልክቶ ቅዳሜ መጋቢት 2/2015 ከፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ውይይት በአገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፓርቲዎች 65 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ መደበኛ በጀት የበጀት ሲሆን፣ ፓርቲዎች ለሚያከናውኑት የሲቪል ትምህርት 41 ሚሊዮን ብር መመደቡን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ ተናግረዋል፡፡

ፓርቲዎች የሚደርሳቸው ገንዘብ በዋና ዋና መስፈርቶች የሚመዘን ሲሆን፣ በሴት አባል ብዛት፣ በሴት አመራር ብዛት፣ በአካል ጉዳተኛ አባል ብዛትና በአካል ጉዳተኛ አመራር ብዛት ተሰልቶ የሚመደብ መሆኑ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም በእኩልነት የሚከፈልባቸው መስፈርቶች በቀድሞ ጠቅላላ ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ያላቸው ፓርቲዎች ናቸው ተብሏል፡፡

በበጀት ዓመቱ የገንዘብ ክፍፍል ውስጥ ያልገቡ ፓርቲዎች መኖራቸውን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡ በገንዘብ ክፍሉ ያልተካተቱ ፓርቲዎች ከዚህ በፊት የወሰዱትን ገንዘብ ምንም ጥቅም ላይ ያላዋሉ፣ ቦርዱ ላቀረበው የበጀት ድልድል ጥያቄ ፍላጎት ምላሽ ያልሰጡ እና የፓርቲ ገንዘብ ምዝበራ ተፈጽሞባቸዋል የተባሉ ፓርቲዎች ይገኙበታል፡፡

ፓርቲዎቹ ከዚህ በፊት የተሰጣቸውን ገንዘብ በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋላቸውን የሚያረጋግጥ እውቅና ባለው ኦዲተር አረጋግጠው ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ ገንዘቡን በአግባቡ ያልተጠቀሙ ፓርቲዎች መኖራቸውም ተጠቁሟል፡፡

ለቦርዱ የኦዲት ሪፖርት ካቀረቡ ፓርቲዎች መካከል፣ እስከ 25 በመቶ ለሚደርሰው ውጪ ማስረጃ ያላቀቡ መገኘታቸው ብርቱካን ጠቁመዋል፡፡ እንዲሁም አሳማኝ የውጪ ምክንያት ያላቀረቡ ፓርቲዎች መኖራቸውም የተጠቆመ ሲሆን፣ ከመንግሥት የተመደበን ገንዘብ በአግባቡ አለመጠቀም ቅጣት እንደሚያስከትልም ተጠቅሷል፡፡

የዘንድሮው ገንዘብ ድልድል የበጀት ዓመቱ ከሰባት ወራት በላይ ካለቀ በኋላ የሚከፋፈል ነው፡፡

በመድረኩም ፓርቲዎቹ በበጀት ድልድሉ ላይ ያላቸውን ጥያቄ ያነሱ ሲሆን፣ የገንዘብ ሥርጭቱ ዘግይቶ መምጣቱ ገንዘቡን በአግባቡ ሥራ ላይ ለማዋል እንቅፋት እንደሚሆን በማንሳት፣ ከዚህ በኋላ በበጀት ዓመት መጀመሪያ እንዲሰራጭ ጠይቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ፓርቲዎቹ ከመንግሥት የተመደበላቸውን ገንዘበ በአግባቡ ለመጠቅም የሚያስችል ነጻ የፓርቲ እንቅስቃሴ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታዎች አለመኖራቸውን እንደ ችግር አንስተዋል፡፡ በተለይም ገዥው ፓርቲ በተፎካካሪ ፓርቲዎች ላይ የሚፈጥረው የነጻነት ገደብ ፓርቲዎቹ ገንዘቡን ተጠቅመው ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ እንቅፋት መሆኑም ተነስቷል፡፡(አዲስ ማለዳ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: birtukan midekssa, Election Board

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule