ከቤንሻንጉል አማርኛ ተናጋሪ ዜጎችን በግፍ የማፈናቀሉ ተጠናክሮ ቀጥሏል በአፋር የተከሰተው ርሃብ ተባብሷል -የሟቾች ቁጥር 22 ደርሷል ኢህአዴግ አድርባይነትን ከማጥፋት ራሱን ማጥፋት ይቀለዋል ርዕዮት ዓለሙ ሁለተኛ ዲግሪዋን እንዳትማር ተደረገች የመንግስትን ዘር ማፅዳት ዘመቻ ማስቆም የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት ነው ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ … [Read more...] about “የኢህአዴግ እብሪትና ትዕቢት አገርንና ህዝብን የሚያጠፋ ነው”
Politics
ሀገሬ ገመናሽ (ክፍል አንድ)
የጎጆዎቻንን ገመናስ እንሸፍንበት ገዶን አያውቅም፤ ድሮ በደህናው ጊዜ፣ ኑሮ ርካሽ በነበረበት ዘመን፣ ኑሮ ከሀገራችን እድገት ጋር እንዲህ አብሮ ሳያድግ፣ የጋገርነውን የዘንጋዳ ቅይጥ፣ ባሰጣነው ማኛ፣ እርቃናችንን በሰልባጅ እንሸፍነው ነበር፡፡ ዛሬም ቢሆን እንደየአቅማችን ገመናችንን እንሸፍንበት አልገደደንም፡፡ ሌላው ቀርቶ መሶባችን ባዶ ሆኖ የሚበላ ቢጠፋ፣ ጦም መዋላችንን እንሸፍንበት የከራረመ ስቴኪኒ ከጥርሳችን አይጠፋም፡፡ እንደርበው ጃኬት ባይኖረን፣ ቆዳ በሚያሻክር ብርድ ሙቀቱን እናማርራለን፡፡ አቦ የራስን ገመና ይሸፍኑበት መች ይገዳል! ሀገሬ የገደደው ያንቺ ገመና ይሸፈንበት መንገድ ነው፡፡ ሁሉም የጎጆውን ገመና ለመሸፈን ደፋ ቀና ሲል፣ የአንቺ ገመና እንደአዳል በግ ላት ተገልብጦ አረፈው፡፡ ለነገሩማ፤ አዎ ያስተማርሻቸው ልጆች አሉሽ፤ ህገ-መንግስትም አቁመሻል፤ ህግ … [Read more...] about ሀገሬ ገመናሽ (ክፍል አንድ)
ሀገሬ ገመናሽ (ክፍል ሁለት)
በቀደም ሳት ብሎኝ፣ ለ መጀመሪያ ልጄ ብቻ የፈረንጅ ሸራ ጫማ ገዝቼ ገባሁ። ያለወትሮዬ ማለቴ ለወትሮው ገበያ የምወጣው ሁለቱንም ልጆቼን ይዤ ስለነበረ ነው። ታዲያ ያን እለታ ማታ ትልቅዋ ልጄ ጫማውን ስትለካ፣ የታናሽ እህትዋ አይን ከሚለካው ጫማ ጋር ሲንከራተት ተመለከትኩ፤ ወይም የተመለከትኩ መሰለኝ። ከወደድሽው ላንቺም ይገዛልሻል አልኳት፤ የትንሽዋን ልጄን አይን እየሸሸሁ። በውስጤ አድሏዊነት ተላወሰ። በልጅትዋ ህሊና ውስጥ ይህ ስሜት እንደማያድር ባውቅም፣ የእኔን ሃሳብ ግን ቶሎ ላስወግደው አልቻልኩም። አየሽ ሀገሬ? እንኳን ህዝበ አዳምና ሔዋንን በእኩልነት ቤት ሆኜ አኖራለሁ የሚል ሀገር፣ አንድ ተራ ምስኪን ወላጅ እንኳን በጎጆው አድሏዊነት እንዳይሰፍን ይጥራል። አንቺ ግን ሀገሬ! … አንቺ ግን ዝሆንና ጥንቸል እያፋለምሽ ለአሸናፊው ታጨበጭቢያለሽ፤ ትሸልሚያለሽ። መቼም ማንም … [Read more...] about ሀገሬ ገመናሽ (ክፍል ሁለት)
ሀገሬ ገመናሽ (ክፍል ሶስት)
ሀገሬ አንዳንዴ ከሰሜን ወደ ደቡብ፣ ከምስራቅ ወደ ምእራብ የዘረጋሻቸውን ጎዳናዎች፣ ልታነጥፊያቸው ደፋ ቀና የምትይላቸውን ሀዲዶች ስመለከት ደስ ይለኛል። የአዲስ አበባን አስፋልትና በየአስፋልቱ ዳር ያቆምሻቸውን ህንፃዎች አዲስነት ስመለከት ደግሞ፣ ‹‹ቆይ ሀገሬ፣ መንገድም፣ ህንፃም አልነበራትም እንዴ?›› ብዬ እራሴን እጠይቃለሁ። እውነቴን ነው የምልሽ ሀገሬ ግንባታሽን ለተመለከተ ፈርሶ የሚሰራ ሀገር ነው እኮ የምትመስይው! ግን እኔ ልማትሽን፣ እድገትሽን፣ ትራንስፎርሜሽንሽን . . . አልነግርሽም! እንደነገርኩሽ ጉዳዬ ከገመናሽ ነው። ለልማት ለትራንስፎርሜሽንማ ራዲዮና ቲቪሽ መች አነሰሽ! ዋናው ራዲዮና ቲቪ አልበቃ ብሎ ኤፍ.ኤም፣ ኢቲቪ1፣ ኢቲቪ 2 . . . ልማትና እድገትሽ ራስምታትሽ እስኪሆን ይነግርሽ የለ! ነጋሪ ያጣው እኮ ገመናሽ ነው! እና እኔ ልጅሽ ልንገርሽ! በትልልቅ … [Read more...] about ሀገሬ ገመናሽ (ክፍል ሶስት)
“አሁን በሥልጣን ላይ ያሉት የባንዳ ልጆች ናቸው”
“አሁን በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች ባመዛኙ ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ የባንዳ ልጆች የነበሩ” አቶ ታዲዎስ ታንቱ በአፋር ክልል ሰዎች በርሃብ እየሞቱ ነው የተመስገን ደሳለኝ ብዕር እየዶለዶመ ይሆን? መንግስት ህገወጥ የእስር ዘመቻውን ቀጠለ የቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀመዛሙርት በፌደራል ፖሊስ ከግቢ እናስባርራችኋለን ተብለናል አሉ ዕውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው? (ሙሉው ዘገባ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about “አሁን በሥልጣን ላይ ያሉት የባንዳ ልጆች ናቸው”
ጥፋቱ የማን ነው?
ኤርትራዊ ሆነው በኢትዮጵያ ከፍተኛ የስልጣን ሃላፊነት የተሸከሙት አቶ በረከት ስምዖን በኢትዮጵያ ላይ የሚፈርድ፣ ዜጎችን የሚያሸማቅቅ፣ ለአገራቸው የተሰውትን የሚያናንቅና በተለይም በውድ አገራቸው የሚመኩ ወገኖችን የሚያኮስስ ንግግር ማድረጋቸው በህወሃት ነባር ታጋዮች ዘንድ ቅሬታ ማስነሳቱ ታወቀ። አቶ ስዬ አብርሃ፣ አቶ ገብሩ አስራት፣ እነ አቶ ተወልደን በስም በመጥራት በኤርትራ ጉዳይ ላይ ጥፋተኛ ያደረጉት አቶ በረከት “አንድነትና አንድ አገር” የሻዕቢያ መዝሙር መሆኑን በመናገር ኢትዮጵያ ውስጥ መገንጠል ለሚፈልጉ ጊዜው ሲደርስ እንደ ኤርትራ መገንጠል መብታቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሚኒስትር ማዕረግ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ በረከት ይህንን የተናገሩት Eritrean Oppositions Arabic Paltalk በሚሰኝ የኤርትራ ተቃዋሚዎች የፓልቶክ መወያያ ክፍል … [Read more...] about ጥፋቱ የማን ነው?
ሥራ አስፈጻሚ ወይስ ጉዳይ አስፈጻሚ?
“ከአያያዝ ይቀደዳል ከአነጋገር ይፈረዳል” እንዲሉ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ፓርላማ ተራ ቁጥር አንድ መቀመጫ ላይ ተሰይመው ንግግር ማድረጋቸውን ተከትሎ አዲስ ክስተት ተስተውሏል። የቅናት፣ የተንኮል፣ የንቀት፣ ያለመታዘዝ፣ ተቃውሞን የማሳየት… ይሁን የሌላ እስካሁን በውል አልታወቀም። በመጀመሪያ ንግግራቸው መዛለፋቸውን ግን ብዙዎች ከእርሳቸው የጠበቁት ባለመሆኑ ተገርመውባቸዋል። በሌላ በኩል ግን ገና ከጅምሩ አክርረው የመጡት “ተለሳላሽ” ናቸው የሚባለውን ለመስበር እንደሆነም አስተያየት ተሰጥቷል። የህወሃት፣ የብአዴን፣ የኦህዴድ፣ የደኢህዴን ሰዎችና ወ/ሮ አዜብ አቶ መለስ ንግግር ካላቸው ማታ እንኳን አያመሹም። ሲያንቀላፉ እንዳይታዩ በጊዜ ተኝተው ጠዋት ፓርላማ ናቸው። ሚኒስትሮችና ከፍተኛ ባለስልጣናት አንዳቸውም አይቀሩም። በሽተኛ እንኳን ቢሆኑ እንደ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ወሳኝ … [Read more...] about ሥራ አስፈጻሚ ወይስ ጉዳይ አስፈጻሚ?
የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!!
እ.አ.አ በ1997 በጨረታ ወደ ግል ንብረትነት ተዛወረ የተባለው የኢትዮጵያውያን ሀብት የተሸጠው 172 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ሽያጩ ተግባራዊ ከሆነ በኋላ ሽያጩን ተከትሎ በርካቶች አርረዋል፤ ተቃጥለዋል። “ዋይ ዋይ ወርቃችን” ብለው አንብተዋል። ህዝብ የፈለገውን ቢል ደንታ የሚሰጠው አካል ስለሌለ የለገደንቢ ወርቅ ማዕድን ከኢትዮጵያ ህዝብ እጅ በአዋጅ ተነጠቀ። ሽያጩን እውን ያደረገው የኢትዮጵያ የፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ቦርድ ሰብሳቢ የነበሩት የወቅቱ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሀሰን አሊ ሲሆኑ፣ የአቶ ስዬ አብርሃ ወንድም አቶ አሰፋ አብርሃ የኤጀንሲው ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ነበሩ። ሁለቱም ባለስልጣናት ዛሬ ሃላፊነት ላይ የሉም። ስለ እውነትና ስለ አገር ሲሉ የሚያውቁትን ለመተንፈስ እስከዛሬ ቢጠበቁም ያሉት ነገር የለም። ሃሰን አሊ ሲኮበልሉ፣ አቶ አሰፋ አብርሃ ከወንድማቸው ጋር … [Read more...] about የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!!






