"ዝምታ ነው መልሴ" ሲሉ ወይዘሮ ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ድምጻቸውን በቲውተር በኩል በዘፈን ምርጫ አጅበው ብቅ ያሉት ለስንብት ሁለት ቀናት ሲቀራቸው ነው። "የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደ ሰው ሲገፋው፣ መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው" ሲሉ የተቀኙት ፕሬዚዳንቷ "ለአንድ ዓመት ሞከርኩት" በሚል ሐረግ መልዕክታቸውን አስረውታል። ይህኔ ነው "የኔታ መስፍን ወልደማርያምን ነብሳቸውን ይማረው" ሲሉ ፋይል ያገላበጡ ፕሬዚዳንቷ በኤክስ ይፋዊ ገጻቸው ላይ ላሰፈሩት ቅኔ ምላሽ የሰጡት። አንዳንዶች "ክብርት ሆይ ሕዝብም መንግሥትም መሆን አይቻልም" ሲሉ ቀልደውባቸዋል። ግልጹ፣ ያመኑበትን ለመናገር ወደኋላ የማይሉት፣ የአደባባዩ ምሑር ፕሮፌሰር መስፍን "ለሦስት መንግሥት ያገለገለች" ሲሉ በሎሌነት የመሰሏቸው የሳህለወርቅ ዘውዴን ሹመት በፍጹም እንደማይቀበሉት ተናግረው … [Read more...] about የሦስት መንግሥታት “ሎሌ” ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ የ”ሳልቀደም ልቅደም” የስንብት ዘፈን
Politics
የትግራይ አበጋዞች ሽኩቻ
ከበረሃ ውንብድና አገረ መንግሥትን ወደመምራት ሳያስበው የተቀበለው ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር በማለት በነጻ አውጪ ስም አንዲት ሉዓላዊት አገር ጠርንፎ በአናሳዎች በግፍ ሲገዛ የነበረው የወንበዴዎች ቡድን ጎራ ለይቶ በአደባባይ መካሰስ ከጀመረና ውዝግቡም እየተካረረ መጥቶ ትግራይን እንደ አፍጋኒስታን ወይም ኢራቅ በጦር አበጋዞች ከፋፍሎ ወደለየለት ደረጃ እየወሰዳት መሆኑ በቅርቡ የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የቡድኑ መሪ የሆነው ደብረጽዮን እነ ጌታቸው የሚከሱኝ በፊትም ጦርነት ውስጥ ያስገባንና ሚሊዮኖችን ያስጨፈጨፈው ትህነግ ነው፤ አሁንም መልሶ ጦርነት ውስጥ ሊከተን ነው፤ ጦርነት ናፋቂ ነው እያሉ ነው፤ ነገር ግን ተጨፈጨፈ የተባለው ሕዝብ ማስረጃ የታለ? ባለተጨበጠና ባልተረጋገጠ፤ ማስረጃ በሌለው እኔን መክሰስ ብቻ ስለፈለጉ ባልሞተ ሕዝብ ይከስሱኛል በማለት … [Read more...] about የትግራይ አበጋዞች ሽኩቻ
አሜሪካ ኢሳያስንና ሻዕቢያን የማስወገድ ዓላማዋን ይፋ አድርጋለች
የሻዕቢያና የኢሳያስ አፈወርቂ ማብቂያቸው እየተቃረበ ይመስላል። ይህንኑ የሚያረጋግጡ ምልክቶች እዚያም እዚህም እየተሰሙ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር የመመለሷን ጉዳይ አጥብቀው በሚፈልጉ ጡነቸኞቹ አገራት ዘንድ አቋም የተያዘ ይመስላል። በኢትዮጵያ ሕዝብ ፍጹም የማይፍለገውን ትህነግን እንደ ሕጻን አዝላ የኖረችው አሜሪካ አሁን ላይ ሁለቱም እንደ አመጣጣቸው እንዲሰናበቱ አቋም ስለመያዟ ከምልክት በላይ መረጃዎች እየወጡ ነው። ፕሬዚዳንት ቢል ክሊንተን ኢሳያስን፣ መለስን፣ ሙሴቪኒንና ካጋሜን አንድ ላይ "የአዲሱ ትውልድ መሪዎች" ብለው ለምስራቅ አፍሪቃ ሲያጩ በድጋፍ ስልጣን ላይ የመጡት ሻዕቢያና ወያኔ ካርዳቸው አልቋል። አሁን ላይ ኢትዮጵያ የገነባችው ኃይልና ዘመናዊ የውትድርና ቴክኖሎጂ ሻዕቢያን ለማስወገድ ከትህነግ በላይ አስተማማኝ በመሆኑ አሜሪካ ትህነግን መሽከም … [Read more...] about አሜሪካ ኢሳያስንና ሻዕቢያን የማስወገድ ዓላማዋን ይፋ አድርጋለች
ኢትዮጵያ የሚያልቧት እንደዚህ ነው፤ “ገንዘብ ባለበት ጩኸት አለ”
የአገራችን “ሃብታሞች” ወግ ከፍቶ ውስጡን ላየው ያስደነግጣል። “ገንዘብ ባለበት ሁሉ ጩኸት አለ” የሚለው አባባል በተለይ በኢትዮጵያ እውነት እንደሆነ ማረጋገጫም ነው። ጎልጉል ባገኘው መረጃ መሠረት የኢትዮጵያን የንግድ ሥርዓት ሲጋልቡ የነበሩ አካላት፣ አሁን ላይ “ይህ ለምን ቀረብን?” ወይም “ገና ለገና ሊቀርብን ነው” በሚል ሥጋት አንድ ላይ አገር እየናጡ ነው። ከዚህ ቀደም “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው” በሚል ርዕስ ስለ አዲሱ ማክሮ ኢኮኖሚክ ፖሊሲ ስንዘግብ ውሳኔው “በኢትዮጵያ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ሳይሆን አዲስ መጽሐፍ ነው፤ ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው፤ ከዚህ አኳያ ፖሊሲው እንከን የማይወጣለት ነው” በሚል አቶ ኤርሚያስ አመልጋን ጠቅሰን እንደነበር ይታወሳል። ይህን ዘገባ ተከትሎ የአዲስ አበባ … [Read more...] about ኢትዮጵያ የሚያልቧት እንደዚህ ነው፤ “ገንዘብ ባለበት ጩኸት አለ”
የትግራይ አበጋዞች ፍልሚያ
የሕወሓትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጀመሩትን ንትርካቸውን በመቀጠል፣ አሁን ደግሞ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ መወዛገብ ጀመሩ። የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ፕሪቶሪያ የተላከው ልዑክ ያልተወያዩበትን መስማማቱን ሲገልጹ፣ ልዑኩን የመሩት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ልዑኩ ወደ ፕሪቶሪያ የሄደው ስለመንግሥትነት ጉዳዮች ለመወያየት ሳይሆን ተኩስ ለማስቆም መሆኑንና በዚያው መሠረት ኃላፊነታቸውን መወጣታቸውን አስታውቀዋል። ሕወሓት ስምምነቱን እንዲፈርሙ የመረጣቸው ልዑካን ስህተት መፈጸማቸው የተናገሩት ደብረ ጽዮን (ዶ/ር)፣ በዚህም ምክንያት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት መጀመር የነበረበት ፖለቲካዊ ውይይት እስካሁን አለመጀመሩንና የክልሉም ሉዓላዊነት አለመረጋገጡን አስታውቀዋል። አቶ … [Read more...] about የትግራይ አበጋዞች ፍልሚያ
ገዱ: “የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው እንክሰስው”፤ “ባለውለታ ነው እንጠቀምበት”
ሰሞኑን ለጥገኝነት ማመልከቻቸው ደጋፊ ነው የተባለለትን ዘለግ ያለ ጽሑፍ ያቀረቡት ገዱ አንዳርጋቸው በትግራይ ማኅበረሰብ ዘንድ የተከፋፈለ ዕይታ የፈጠሩ መሆናቸው ተነገረ። ““የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው፤ እጃችን ገብቷል እንክሰሰው” ባዮች በርተተው የታዩ ቢሆንም “ባለውለታችን ነውና አሁንም እንጠቀምበት” የሚሉ በሌላ ወገን ድምጻቸውን እያሰሙ ነው። በዘመነ ትህነግ የሥርዓቱ ተላላኪና ጉዳይ ፈጻሚ የነበሩት ገዱ አንዳርጋቸው የዚያን ጊዜው አለቆቻቸውን ለማስደሰት ያልታዘዙትን፣ ያልተጠየቁትን እላፊ በመሄድ በመፈጸም አለቆቻቸውን እጅ በመንሳት ይታወቃሉ። ለዚህ ታማኝነታቸው በአማራ ሕዝብ ላይ የመጨረሻውን ሥልጣን እንዲያገኙና ሎሌነታቸውን የበለጠ በደስታ እንዲፈጽሙ አድርጓቸዋል የሚሉ ጥቂት አይደሉም። እንደማሳያም የወልቃይትን ጉዳይ ይጠቅሳሉ። ገዱ አንዳርጋቸው ከዚህ በታች ያለው … [Read more...] about ገዱ: “የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው እንክሰስው”፤ “ባለውለታ ነው እንጠቀምበት”
“የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው”
ሁሉም ባይባልም አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዋና የፖለቲካ ፕሮግራም ሶሻል ዴሞክራሲ ወይም ሊበራል ዴሞክራሲ ወይም ምርጫን ማዕከሉ ያደረገ ዴሞክራሲያዊ ፖሊሲ ነው። የኢኮኖሚ ፕሮግራማቸው ደግሞ ገበያ መር ኢኮኖሚ ነው። እነዚሁ ፓርቲዎች በምርጫ ክርክር ሲደረግ በዋናነት እያነሱ የሚከራከሩት መንግሥት ኢኮኖሚውን ተቆጣጥሮታል፤ የዕዝ ኢኮኖሚ ነው አገሪቱን ለችግር የዳረጋት፣ የኢኮኖሚው አካሄድ በገበያ እንጂ በመንግሥት መመራት የለበትም በሚል የከረረ ተቃውሞ በማቅረብ ሲቃወሙ ላለፉት በርካታ ዓመታት ሰምተናል። ባለፈው ሰኞ መንግሥት የአገሪቱን ዐቢይ (ማክሮ) ኢኮኖሚ ወደ ገበያ መር የሚወስድ ውሳኔ ይፋ ሲያደርግ እነዚሁ ተቃዋሚዎች “እሰይ ስለቴ ሰመረ” ባይሉም ቢያንስ ለዓመታት ሲሟገቱለት የነበረው ሃሳብ ድል አድርጎ በማየታቸው ጥንቃቄ የተሞላበት ድጋፍ ሊያሰሙ የሚጠበቅ … [Read more...] about “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው”
“እንደ ጌታቸው ዐቢይን አልተሳደብኩም፤ ለምን ሥልጣን ከለከሉኝ?” ደብረጽዮን
ጌታቸው ረዳ በድምጸ ወያኔ በርካታ ምሥጢር ይፋ አድርገዋል፤ ወደ ሚዲያ የወጣበት አንዱ ምክንያት “በስብሰባ ላይ መናገር ስላልቻልሁ” ነው በማለት ተናግሯል። ደብረጽዮንን ጨምሮ የተለያዩ የትህነግ አመራሮችም ሆኑ የወታደር አዛዦች የፕሪቶሪያውን ስምምነት “ባክህን አድነን ፈርም፤ አለበለዚያ ወደ ቆላ ተምቤን ልንሄድ ነው” እያሉ ይገፉት እንደነበር ገልጾዋል። እነ ደብረጽዮን ይህን ባደረጉ ማግስት “ከጀግና ወደ ባንዳ ወደ ይሁዳ” እንዳወረዱትም ጌታቸው በግልጽ አመልክቷል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ደብረጽዮን በየቦታው እየዞረ “በቅልጥማችን ወይም በጉልበታችን ፌዴራል መንግሥትን ወደ ጠረጴዛ አመጣነው” ሲል ተደምጧል። በነጻ ሚዲያ ላይ ከስዩም ተሾመ ጋር ውይይት ያደረገው አርአያ ተስፋማርያም ሌላ የሰጠው መረጃ አለ፤ “በ3ኛው ዙር መከላከያ መቀሌ ሊገባ ሲል እየገሰገሰ ሳለ … [Read more...] about “እንደ ጌታቸው ዐቢይን አልተሳደብኩም፤ ለምን ሥልጣን ከለከሉኝ?” ደብረጽዮን
ኢትዮጵያ 16.6 ቢሊዮን ዶላር ከዓለም ባንክ አገኘች
ለሁለት ዓመታት የተደረገው ድርድር ያስገኘው ውጤት ነው የዓለም ባንክ በዛሬው ዕለት (ማክሰኞ) “የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዘላቂና ሁሉን ዓቀፍ የልማት ፖሊሲ ዘመቻ” (Ethiopia First Sustainable and Inclusive Growth Development Policy Operation) በሚል ለሚጠራው የልማት ፖሊሲ ማስፈጸሚያ የሚሆን ድጋፍና ብድር መፍቀዱን ይፋ አድርጓል።በወጣው መግለጫ መሠረት ባንኩ የሚያደርገው ድጋፍ ሦስት ዓላማዎችን ያካተተ ነው፤ (ሀ) ለመዋቅር መልሶ ማዋቀርና ንግድን ለማሳለጥ (ለ) በጀትን በተመለከተ ዘላቂነትንና ግልጽነትን ለማስፋፋት እና (ሐ) የአካባቢ ጥበቃን እና ማኅበራዊ አይበገሬነትን ለማበረታታት እንደሆነ ተገልጾዋል። በተለምዶ የዓለም ባንክ የሚባለው ቡድን ሲሆን በሥሩም የተለያዩ ድርጅቶች አሉት፤ ብድርም ሆነ ሥጦታ ሲፈቀድ … [Read more...] about ኢትዮጵያ 16.6 ቢሊዮን ዶላር ከዓለም ባንክ አገኘች
በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን እጁን ሰጠ በአማራ ክልል በርካታ የታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በመንግሥት የቀረበላቸውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ሰላማዊ ሕይወት እየመሩ መሆኑን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታውቋል፡፡ የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩትን የፀጥታ ችግሮች በንግግርና በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በመንግሥት ለታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በተደጋጋሚ የሰላም አማራጮች ሲቀርቡ ቆይተዋል፡፡ ይሁንና በክልሎችም ሆነ በፌዴራል መንግሥት እየቀረበ ያለው የሰላም አማራጭ እንዳይሳካ እና ወደ መሬት እንዳይወርድ በተለይም ደግሞ ውጭ ሆነው በትግሉ ስም ጥቅም የሚያግበሰብሱ አንዳንድ ጽንፈኛ … [Read more...] about በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ