በአዲስ አበበ ከተማ የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ፣ ባለሙያዎች እና ደላሎች በሙስና ወንጀል እጅ ከፍንጅ ተይዘው በቁጥጥር ሥር ዋሉ። የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳዳር ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ የሆኑት፦ 1ኛ. ሃብታሙ ግዲሳ ጆቴ 2ኛ. ስምረት ገ/እግዚአብሔር አሰፋ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር 3ኛ. ዮሴፍ ባቡ ሆራ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር 4ኛ. አቤኔዘር ቶሎሳ ሙሉ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር 5ኛ. ለሚ ሲሌ ከፍተኛ ግብር ከፋይ የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር እና 6ኛ. መቅደስ አረጋዊ ገንዘብ ተቀባይ የሆኑት በቀን 06/01/2017 ዓ.ም በሙስና ወንጀል … [Read more...] about በአዲስ አበባ ገቢዎች የታክስ ኦዲት ባለሙያ ሌቦች ተያዙ
operation dismantle tplf
ኢትዮጵያ የሚያልቧት እንደዚህ ነው፤ “ገንዘብ ባለበት ጩኸት አለ”
የአገራችን “ሃብታሞች” ወግ ከፍቶ ውስጡን ላየው ያስደነግጣል። “ገንዘብ ባለበት ሁሉ ጩኸት አለ” የሚለው አባባል በተለይ በኢትዮጵያ እውነት እንደሆነ ማረጋገጫም ነው። ጎልጉል ባገኘው መረጃ መሠረት የኢትዮጵያን የንግድ ሥርዓት ሲጋልቡ የነበሩ አካላት፣ አሁን ላይ “ይህ ለምን ቀረብን?” ወይም “ገና ለገና ሊቀርብን ነው” በሚል ሥጋት አንድ ላይ አገር እየናጡ ነው። ከዚህ ቀደም “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው” በሚል ርዕስ ስለ አዲሱ ማክሮ ኢኮኖሚክ ፖሊሲ ስንዘግብ ውሳኔው “በኢትዮጵያ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ሳይሆን አዲስ መጽሐፍ ነው፤ ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው፤ ከዚህ አኳያ ፖሊሲው እንከን የማይወጣለት ነው” በሚል አቶ ኤርሚያስ አመልጋን ጠቅሰን እንደነበር ይታወሳል። ይህን ዘገባ ተከትሎ የአዲስ አበባ … [Read more...] about ኢትዮጵያ የሚያልቧት እንደዚህ ነው፤ “ገንዘብ ባለበት ጩኸት አለ”
የትግራይ አበጋዞች ፍልሚያ
የሕወሓትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጀመሩትን ንትርካቸውን በመቀጠል፣ አሁን ደግሞ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ መወዛገብ ጀመሩ። የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ፕሪቶሪያ የተላከው ልዑክ ያልተወያዩበትን መስማማቱን ሲገልጹ፣ ልዑኩን የመሩት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ልዑኩ ወደ ፕሪቶሪያ የሄደው ስለመንግሥትነት ጉዳዮች ለመወያየት ሳይሆን ተኩስ ለማስቆም መሆኑንና በዚያው መሠረት ኃላፊነታቸውን መወጣታቸውን አስታውቀዋል። ሕወሓት ስምምነቱን እንዲፈርሙ የመረጣቸው ልዑካን ስህተት መፈጸማቸው የተናገሩት ደብረ ጽዮን (ዶ/ር)፣ በዚህም ምክንያት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት መጀመር የነበረበት ፖለቲካዊ ውይይት እስካሁን አለመጀመሩንና የክልሉም ሉዓላዊነት አለመረጋገጡን አስታውቀዋል። አቶ … [Read more...] about የትግራይ አበጋዞች ፍልሚያ
የ፲፪ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት የዘንድሮና የአምናው መጠነኛ ንጽጽር
በ2016 ዓም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 684 ሺህ 205 ተማሪዎች ያለፉት 36 ሺህ 409 ወይም 5.4 በመቶ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከትላንት በስቲያ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ከዚህ በታች ያለውን መረጃ ያሰባሰብነው ከመንግሥታዊ ሚዲያና ከቲክቫህ ነው። በአጠቃላይ 1 ሺህ 363 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ሲሆን በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ 4 ትምህርት ቤቶች ከሐረሪ ክልል ውጭ ሁሉም ክልሎች ላይ አንድም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን አመላክተዋል።በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ከ500 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ባለፈው ዓመት 273 የነበሩ ሲሆን በአሁኑ 1ሺ 220 ተማሪዎች ከ500 በላይ ያመጡ ናቸው ተብሏል።እንዲሁም በዘንድሮ 12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 5.4 በመቶ ፈተናውን አልፈዋል ይህም ማለት … [Read more...] about የ፲፪ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት የዘንድሮና የአምናው መጠነኛ ንጽጽር
“እንደ ጌታቸው ዐቢይን አልተሳደብኩም፤ ለምን ሥልጣን ከለከሉኝ?” ደብረጽዮን
ጌታቸው ረዳ በድምጸ ወያኔ በርካታ ምሥጢር ይፋ አድርገዋል፤ ወደ ሚዲያ የወጣበት አንዱ ምክንያት “በስብሰባ ላይ መናገር ስላልቻልሁ” ነው በማለት ተናግሯል። ደብረጽዮንን ጨምሮ የተለያዩ የትህነግ አመራሮችም ሆኑ የወታደር አዛዦች የፕሪቶሪያውን ስምምነት “ባክህን አድነን ፈርም፤ አለበለዚያ ወደ ቆላ ተምቤን ልንሄድ ነው” እያሉ ይገፉት እንደነበር ገልጾዋል። እነ ደብረጽዮን ይህን ባደረጉ ማግስት “ከጀግና ወደ ባንዳ ወደ ይሁዳ” እንዳወረዱትም ጌታቸው በግልጽ አመልክቷል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ደብረጽዮን በየቦታው እየዞረ “በቅልጥማችን ወይም በጉልበታችን ፌዴራል መንግሥትን ወደ ጠረጴዛ አመጣነው” ሲል ተደምጧል። በነጻ ሚዲያ ላይ ከስዩም ተሾመ ጋር ውይይት ያደረገው አርአያ ተስፋማርያም ሌላ የሰጠው መረጃ አለ፤ “በ3ኛው ዙር መከላከያ መቀሌ ሊገባ ሲል እየገሰገሰ ሳለ … [Read more...] about “እንደ ጌታቸው ዐቢይን አልተሳደብኩም፤ ለምን ሥልጣን ከለከሉኝ?” ደብረጽዮን
በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን እጁን ሰጠ በአማራ ክልል በርካታ የታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በመንግሥት የቀረበላቸውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ሰላማዊ ሕይወት እየመሩ መሆኑን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታውቋል፡፡ የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩትን የፀጥታ ችግሮች በንግግርና በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በመንግሥት ለታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በተደጋጋሚ የሰላም አማራጮች ሲቀርቡ ቆይተዋል፡፡ ይሁንና በክልሎችም ሆነ በፌዴራል መንግሥት እየቀረበ ያለው የሰላም አማራጭ እንዳይሳካ እና ወደ መሬት እንዳይወርድ በተለይም ደግሞ ውጭ ሆነው በትግሉ ስም ጥቅም የሚያግበሰብሱ አንዳንድ ጽንፈኛ … [Read more...] about በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ
ዘመነ ካሤ ቀድሞ ወደ ድርድር እየሮጠ ነው
ገና ከጅምሩ “አንደ ወጥ አመራር፣ ድርጅታዊ ግብ፣ ዓላማ የለውም፤ በዚህ አካሄድ ጦርነት ማካሄድ ይከብዳል፤ ጊዜያዊ ድሎች ቢመዘገቡም ዘላቂ ድል ማግኘት ያስቸግራል” የሚለው በአማራ ክልል የተነሳውን ግጭት አስመልክቶ በስፋትና በተደጋጋሚ ሲስጥ የቆየ አስተያየት ነው። ይህ መሠረታዊ ሐቅ የገባቸው አንድ ለመሆን ብዙ የጣሩ ሲሆን፤ በርካታዎች ግን በተለይ በውጭ አገር በሚላክላቸው ዳረጎት “ፋኖ” የሚል ስም ይዘው በሕዝባቸው ላይ ብረት ያነሱ በመሆናቸው የአንድነት ጉዳይ ብዙም የሚመቻቸው ሳይሆን ቆይቷል። የስምምነት ውይይቶችም ሊደረጉ ሲሉ ከአረብ አገር እስከ አውሮጳና አሜሪካ እንደ ግል ካምፓኒ (ፒኤልሲ) የተዋጊ “የፋኖ” ሱቅ የከፈቱት ዳያስፖራዎች “ቧንቧውን እዘጋዋለሁ” እያሉ በማስፈራራት ተፈላጊው አንድነት እውን ሳይሆን ቀርቷል። በመንግሥት በኩል “አንድ ሁኑ እና እንደራደር” … [Read more...] about ዘመነ ካሤ ቀድሞ ወደ ድርድር እየሮጠ ነው
የኅቡዕ ቡድን ሪፖርት በኅቡዕ በሚሠሩ “ኢትዮጵያውያን” – ኢትዮጵያ ላይ የተመዘዘ ሰይፍ!
የስሙ መነሻ ግንድ የሚመዘዘው ከላቲን ነው። “vates” ይባላል። ትርጉሙም “prophet” ነቢይ፣ ወይም Fortune teller ትንቢት አብሳሪ፣ የወደፊቱን ገላጭ እንደ ማለት ነው። ስሙንም ስያሜውንም ጠቅሶ ማብራሪያ ያኖረው ራሱ ቡድኑ ሲሆን ከስሙ ለመረዳት እንደሚቻለው “ሰማያዊ ቅባትን” ራሱ ላይ ደፍቷል። የአደባባይ የድረገጹ ስምና መገኛው vatescorp.com ነው። ምርመራና የሥጋት ቅድመ ትንተና ማድረግ ዋናው የሥራው የጀርባ አጥንት እንደሆነ የሚጠቁመው ይኸው ቡድን ከስያሜውና ለራሱ ከሰጠው የነቢይነት አክሊል ውጪ ሌላ ዝርዝር የማንነት መገለጫ ስለሌለው ጥሞናን ለሚያስቀድሙ ዜጎች ሁሉ “ማነህ ነቢዩ? እነማን ናችሁ ትንቢት አብሳሪዎቹ?” ወዘተ የሚል ጥያቄ እንዲያነሱ አስገድዷቸዋል። ይህ ግራ አጋቢነቱ ቀድሞ መነጋገሪያ የሆነበት ማኅበር፣ ቡድን፣ የመናፍስት … [Read more...] about የኅቡዕ ቡድን ሪፖርት በኅቡዕ በሚሠሩ “ኢትዮጵያውያን” – ኢትዮጵያ ላይ የተመዘዘ ሰይፍ!
ቱሪዝም በአማራ ክልል ሊቆም ነው
"... አሁን ቱሪስት የለም" የላሊበላ ነዋሪ እስከ 2 ቢሊዮን የሚጠጋ ብርም ከዘርፉ ይገኝ ነበር የአማራ ክልል ቱሪዝም በግጭቱ ምክንያት ሥራ ለማቆም መቃረቡን የክልሉ የባህልና የቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ‼️ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የዐማራ ክልልን ይጎበኛሉ ተብለው ከታቀዱት የውጭ ሀገር ጎብኝዎች ቁጥር የመጡት 20 በመቶ ብቻ መኾናቸውን የገለጸው የባህል እና ቱሪዝም ቢሮ፣ የክልሉ ቱሪዝም በእጅጉ በመዳከሙ ሥራ ለማቆም መቃረቡን አስታውቋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር አየለ አናውጤ ትናንት ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በክልሉ ተለዋዋጭ ገጽታ እያሳየ የቀጠለው የትጥቅ ግጭት፣ “ዘርፉን ጨርሶ ለማስቆም እየተቃረበ ነው፤” ብለዋል፡፡ በቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶችም፣ በግጭቱ ሳቢያ ከሥራ ገበታ ውጭ መኾናቸውን አመልክተዋል፡፡ (VOA) ጥር 7 2016 የታተመው … [Read more...] about ቱሪዝም በአማራ ክልል ሊቆም ነው
ትግራይ እየፈረሰች ነው – ሐይቲ በኢትዮጵያ
"አሁን ማንም ሰው ነው አግቶ የሚወስድህ፤ የሚጠብቅ የፀጥታ አካል የለም" ትህነግ በእብሪት ተሞልቶ መቀሌ መሽጎ በነበረበት ወቅት አገሪቱ በግጭት ስትታመስ፤ ዜጎች ሲፈናቀሉ፣ ለውጡ ነውጥ ሆኖ ኢትዮጵያ በመፍረስ አደጋ ውስጥ ሆና ሳለ የሰላም ጉዳይ ያሳሰባቸው እናቶች ወደተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ተጉዘው ነበር። በሁሉም ቦታዎች የክብር አቀባበል ከተደረገላቸው በኋላ የተጓዙት ወደ መቀሌ ነበር። የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው፣ የሰላም ሠንደቅ በማውለብለብ እያለቀሱ መሬት ላይ ተደፍተው “ሰላም ላገራችን” ብለው ልመናቸውን ሲያቀርቡ የወንበዴው ቡድን መሪና በወቅቱ የክልሉ አስተዳዳሪ የነበረው ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እያላገጠ “እኛ ክልል ሰላም ነው፤ ይልቅ ሌላ ክልል ነው ሰላም የጠፋው፤ ስለዚህ እዚያ ብትሔዱ ይሻላል፤ እኛ ጋር ለምን እንደመጣችሁ አናውቀም?” በማለት ነበር … [Read more...] about ትግራይ እየፈረሰች ነው – ሐይቲ በኢትዮጵያ










