አምስተርዳም ይካሄዳል ተብሎ በውጭ አገር በሚኖሩ በተለያዩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የተሰራጨው የሽግግር መንግሥት ምስረታ ጉባኤ ከአሜሪካ ወደ አምስተርዳም ያመራው አሜሪካ ጥያቄውን ባለመቀበሏ መሆኑ ተሰማ። ስብሰባው ከጀርባው ሆነው የሚመሩትና ሻዕቢያና ሌሎች ፍላጎት ያላቸው የሚታወቁ አካላት እንደሆኑም እየተነገረ ነው። የቀድሞ የትህነግ አመራርና አሁን ላይ “ቪዥን ኢትዮጵያ” ከሚባለው አደረጃጀት ጋር እየሠሩ ያሉት አቶ ግደይ ዘርዓጽዮን በግል የኢሜል አድራሻቸው “ለስብሰባው ተዘጋጁበት” ሲሉ ያሰራጩት ሰነድ ጉባዔው ለምን ወደ አምስተርዳም እንደተዛወረ፣ ወይም አምስተርዳም ለምን እንደተመረጠች አያስረዳም። ይህንኑ አስመልክተን ተጋባዥ ከሆኑት መካከል የአዲስ ሪፖርተር የዋሽንግቶን ተባባሪ ያነጋገራቸው “ቅድሚያ ዕቅዱ ስብሰባውን በአሜሪካ ለማድረግ ነበር፤ ምላሹ ጥሩ ባለመሆኑ ወደ … [Read more...] about አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው
