በእኛ ሀገር የሚከበሩ የህዝብ በዓላት በህግ የታወቁ ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሠሩ መንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለምአቀፍ ተቋማት እንዲሁም ኢምባሲዎች እና የቆንፅላ ጽ/ቤቶችም የእኛን ሕዝብ በዓላቶች እንዲያከብሯቸው ይጠበቃል። ምክንያቱም በዓላቱን ማክበር ህዝብን ማክበር ከዚያም ሲያልፍ ሀገሪቱ ሉዓላዊ መሆኗን ማረጋገጥ ነውና። እነዚህ በዓላት የዘመን መለወጫ በዓል (መስከረም 1)፣ የዓደዋ ድል መታሰቢያ ቀን (የካቲት 23)፣ የድል ቀን (ሚያዝያ 27)፣ የዓለም የሠራተኞች ቀን፣ መስቀል (መስከረም 17)፣ ጥምቀት (ጥር 11)፣ የክርስቶስ ልደት(ታህሳስ 29/28) እንዲሁም ቀናቸው በየዓመቱ የሚቀያር ስቅለት፣ ትንሳዔ፣ ፣ኢድ አልአድሃ፣ መውሊድና ኢድ አል ፈጥር ናቸው። በእነዚህ ቀናት እንደሁኔታው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣ የግል ድርጅቶችና የንግድ ሱቆች ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ … [Read more...] about ግንቦት 20 በህግ የታወቀ የህዝብ በዓል ነው?