• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ

May 28, 2025 02:01 am by Editor 2 Comments

መለስ ዜናዊ ከስሙ ጀምሮ ሁሉ ነገሩ የውሸት ወይም ፌክ ነው። ላደረሰብን ግፍ እንክሰሰው እንኳን ብንል በየትኛው ስሙ ነው ፍርድ ቤት የምናቆመው የነበረው? ደግነቱ ከዚህ ሁሉ በፊት ወደ ዕረፍቱ ሄዶ እኛንም አሳረፈን።

መለስ የዕውቀት ችግር አልነበረውም፤ ዕድሜ ለኢትዮጵያ ከሥር መሠረቱ በነጻ አስተምራዋለች። ንጉሡም ሰው ነው፤ ነገ ሀገር ይጠቅማል ብለው ሸልመውታል ይባላል። ግን ያልታከመና ሥር የሰደደ የበታችነት ስሜት የነበረው፣ አስተሳሰቡ ደሃ የሆነ ሰው ነበር። በዚህ ደሃ አስተሳሰቡ ነበር ኢትዮጵያን ለመምራት ሥልጣን ኮርቻ ላይ የተፈናጠጠው። ሥልጣን፣ ሃብት፣ ድሎት፣ ወዘተ ቢመጣም አስተሳሰብ ደሃ ከሆነ ችግሩ ውስብስብና መፍትሔ ዓልባ ነው የሚሆነው።

መለስ ኢትዮጵያን በጣም ነበር የሚጠላት፤ ለማፍረስ ይፈልግ ነበር ለማለት ብዙም አያስደፍርም። ነገርግን ልክ እንደ ፖለቲካ ወላጅ አባቱ የሻዕቢያው ኢሳያስ ኢትዮጵያ ተዳክማና ደህይታ ማየት የዘወትሩ ምኞቱና ሕልሙ ነበር። ይህንንም ገና ሥልጣን ከመያዙ ጀምሮ በዕቅድ የሠራበት፤ ሕልሙንም ዕውን ያደረገበት ጉዞ ነበር።

ወደ ሥልጣን ሲመጣ ትህነግ የሚለውን የድርጅቱን ስም መለወጥ አልፈለገም። የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር የተባለውን የአሸባሪና የወንበዴዎች ስብስብ እየመራ አዲስ አበባ ገባ። በነጻ አውጪ ድርጅት ስምም የሚጠላትን አገር “አገሪቱ” እያለ መራ፤ “አገራችን ኢትዮጵያ” ለማለት እንደተጸየፈ ሞት ወሰደው። ደሃ አስተሳሰብ ቶሎ ካልተፋቱት እስከ መቃብር ነው ፍቅሩ።

መለስ ኤርትራ በግድ እንድትገነጠል አደረገ፤ በኤርትራ መገንጠል ዋና ትኩረት ያደረገው አሰብን ለኤርትራ ለመስጠትና ኢትዮጵያን ወደብ ዓልባ አድርጎ ማደኽየት ነው። እንዳሰበውም አደረገውና በቀን ሦስት ሚሊዮን ዶላር ኢትዮጵያ ለጅቡቲ ወደብ ኪራይ እንድትከፍል አደረጋት፤ በዓመት አይደለም በቀን፤ 3,000,000 ብር አይደለም፤ ሦስት ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በቀን!! ከዚህ ተነስተን ላለፉት 30+ ዓመታት ስንት እንደከፈልን መገመት አያዳግትም።

መለስ ድሃ አስተሳሰቡን ሲናገሩበት አይወድም፤ ያልተፈወሰ የበታችነት ስሜት የተጠናወተው ስለነበር የማይወደውን መከራከሪያ ለሚያመጡ ሰዎች የሚሰጠው ምላሽ በየጊዜው ልኩን ያሳበቀበት ሆኖ አልፏል። ለምሳሌ አሰብን በማጣታችን የኢኮኖሚ ጉዳት ይደርስብናል ወይ ተብሎ ሲጠየቅ፤ አሰብን ማጣት በኢኮኖሚው ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አያደርስም፤ ምንም ለውጥ አያመጣም፤ ኤርትራውያን ከፈለጉ ግመሎቻቸውን ያጠጡበት ነበር ያለው። ምስጋና ለፈጣሪ ይግባውና አሁን ትክክለኛ ባለቤቶቹ የአፋር ግመሎች ከቀይ ባሕር የሚጠጡበት ዘመን ላይ እንገኛለን።

የመለስ ውዳቂ፣ ተራ ምቀኝነት የተሞላበት፣ አይደለም የአገር መሪ ከማንም ሰው የማይጠበቅ አስተሳሰቡ የታየው በባድመ ጦርነት ወቅት ነበር። የግል ጠባቂው/አጃቢው የነበረው ሚኪ ራያ በጦርነቱ ወቅት አስመራ እየሄደ ኢሳያስን እጅ ሲነሳና በሰላም እንጨርሰው እያለ ሲለምን ነበር ብሎ ሰሞኑን ነግሮናል። እንዲያውም ኢሳያስ መለስ ዜናዊን “ጨምላቃ” ብሎ ሲሰድበው፤ መለስም ጭንቅላቱን እንዳዘቀዘቀ ድምፅ ሳያሰማ ስድቧን ጠጥቶ እንደወጣ ሚኪ ራያ ነግሮናል። ለነገሩ ለመለስ ዓይነት ነውር ቀለቡ ይህ ሽልማት ነው፤ ምክንያቱም የኢሳያስ ስድብ ለመለስ እንደ ቡራኬ ስለሆነ።

ይኸው የባድመ ጦርነት ካበቃ በኋላ ወደ አልጀርስ ስምምነት ለማድረግ ዝግጅት በሚደረግበት ወቅት ኢትዮጵያውያን ምሑራን እና ጠበቆች አሰብን ለማስመለስ አሁን ነው ጊዜውና ሙግቱን በጠንካራ ማስረጃ እናቅርብ፤ ክፍያም አንፈልግም፤ ለአገራችን በነጻ እናገልግል ብለው ቢጠይቁም መለስ “እናንተን አልፈልግም” ብሎ የውጭ አገር ዜጎችን በዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ቀጥሮ አሰብ ለኢትዮጵያ እንዳትሰጥ እንዲያደርጉ በርትቶ ነበር የሠራው። ይህንን መለስ ነው እንግዲህ ደጋፊና አምላኪዎቹ “world class mind” እያሉ ከሙታን መንደር እንደ ዓልአዛር እንዲነሳላቸው የሚያንቆለጳጵሱት።

የአስተሳሰብ ደሃ የሆነው መለስ ኢትዮጵያን ደሃ ማድረግ የተለማደው ትግራይ ላይ ነው። በ17ቱ ዓመት የበረሃ ውንብድና ዘመኑ እሱና ወንበዴ ጓደኞቹ ለትግራይ ተብሎ በዕርዳታ የተላከ ዘይት፣ እህል እና ዱቄት የትግራይ ሕዝብ እንዳያገኝ በማድረግ እንዲሰቃይና እንዲሞት ያደረጉ፤ እንታገልለታለን ለሚሉት ሕዝብ 50 ዓመት ሙሉ ሰቆቃን የጋቱ ጨካኞች ናቸው። ከዚህ አንጻር አሰብን በማጣት የሚደርስብ የኢኮኖሚ ጉዳት ለመለስ ደስታው ነው። ምክንያቱም ኢትዮጵያን አዳክሞና የትግራይ ተመጽዋች አድርጎ ታላቋን ትግራይ ሲመሠርት አሰብን ከኢትዮጵያ ከመቀበል ይልቅ ከኤርትራ ለመውሰድ ይቀላል ብሎ የራሱን ወንበዴ ጓደኞቹን ያሳመነው መለስ ነው። አሁን ግን ዘመን መጣ፣ ምርኮ የሚመለስበት ዘመን፣ የፈረሰው ባሕር ኃይላችን በደማችን የቀላውን ቀይ ባሕርን የሚቆጣጠርበት ዕድሜ ላይ ደረስን፤ አለመሞት ደጉ ይህን አሳየን።

መለስ የድሃ አስተሳሰቡን ውጪ አገር ሲሄድና ፈረንጆችን ሲያገኝ በጣም ጎልቶ ይታይበታል። አሽከራቸው፣ ተላላኪያቸውና ጉዳይ ፈጻሚያቸው ስለነበር፤ ለራሱ ክብር ነስቶ አገራችንን ክብር ያሳጣ ወራዳ ሰው ስለነበር ውጪ አገር ሲሄድ ሎሌነቱን በገሃድ ይታይበታል። አፍቃሪ ትህነጉ ቴዎድሮስ ጸጋዬ “ህወሃት ለመገርደድ ወይም ለግርድና የተፈጠረ ነው፤ ለሻዕቢያ ሲገረደድ ነው የኖረው፤ አሁንም በዚያው ነው የሚቀጥለው” በማለት የተናገረውን እዚህ ላይ መጥቀስ የመለስን እና የፈረንጅ አለቆቹን ግንኙነት በጥሩ የሚገልጥ ነው። ትህነግ ይኸው ቴዎድሮስ የተናገረው አባባል አልለቅ ብሎት የመለስ ሌጋሲ አስቀጣዮቹ እነ ደብረጽዮን ገደለን፣ ጨፈጨፈን፣ አረደን፣ ሴቶቻችንን ደፈረ፣ ዘረፈን፣ … ሲሉት ለነበረው ሻዕቢያ ወደውና ፈቅደው “እየተገረደዱ” ነው። መለስም ለፈረንጅ ጌቶቹ እንዲሁ ነበር፤ የአስተሳሰብ ድህነት ማለት ይህ ነው።

መለስ ውጪ አገራት ሄዶና “ተገርድዶ” ሲመለስ በጣም ሼም የሚሰማው ሰው ነበር። ይህንን ኻፍረቱን ለመሸፈንም ወደ አገር ሲመለስ መወራጨት ይጀምራል። ቶሎ ብሎ ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ወይም የፓርላማ ስብሰባ ላይ በመከሰት ሕዝቡን፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰዎችን፣ በአቅራቢያው ያሉትን ወንበዴ ጓደኞቹን፣ … ምንም የሚቀረው የለም አፉ እንዳመጣለት ይሳደባል። ሁኔታው “እኔ ለጌቶቼ እንደተገረደድሁ እናንተም ለኔ ትገረደዳላችሁ” ይመስላል። ይህ ነው እንግዲህ በደጋፊዎቹ “world class mind” የተባለለት መለስ።

መለስ በዚህ የወረደ የበታችነት አስተሳሰቡ ከዘረኝነት ጀምሮ ጥሎልን የሄደው የድንቁርና ኮተትና ዝባዝንኬ ለኢትዮጵያ ቆፍሮ የሄደው ጉድጓድ ነው። በዚህ ትውልድ ሙሉ በሙሉ መደፈን ባይችልም ሥራው ግን ተጀምሯል። መለስንና ትህነግን የሚያስታውሱን እዚህ ጉድጓድ ውስጥ እየተቀበሩ በምትኩ ኢትዮጵያዊነት እየጎላና እያበበ መሄዱ አይቀሬ ነው።   

መለስ ዜናዊ ደሃ አስተሳሰብ የተጠናወተው፤ በበታችነት ስሜት የተሰቃየ ተራ ሆኖ ኢትዮጵያን ተራ ያደረገ ነበር። ስለ እርሱ ይህንን ያህል ከተባለ ይበቃዋል። የሌላኛው መሪ ወግ ግን በአንድ ዐርፍተ ነገር ይጠቃለላል፤ ግንቦት 20ን ተራ የሥራ ቀን አደረገልን። (ነሐሴ ፲፬ ነኝ ከ፬ ኪሎ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions, Politics Tagged With: abiy ahmed, ginbot 20, may 28, meles zenawi, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    May 28, 2025 10:04 pm at 10:04 pm

    የጅል መንጋ ሲንጋጋ ጊዜው መሽቶ ነጋ
    ትላንትን በዛሬ መዝኖ ግጠሙኝ አለ ፎክሮ
    ጊዜው ተለውጦ ተቀይጦ የሰው መልኩ ሁሉ ተረስቶ
    አውሬ መሰለ ባህሪው ተለውጦ
    የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው ብሎ ታቅፎ
    ተመልሶ ይቧቀሳል ደም ተጠምቶ
    በልቶ አዳሪ የታደለ ጦም አዳሪ ያልታደለ
    ተገናኙ በሜዳ ላይ በወረፋ ሊሯሯጡ
    በእሳት ቋንቋ ሊናገሩ፤ ጊዜ ዘሞ ሲራኮቱ
    ሃገር ቤትም ተቃጠሉ
    ዜሮ ጅምር ዜሮ ድምር
    ሁሉም ባዶ ሆነ ድሉ።

    Reply
  2. Tefera says

    May 29, 2025 01:14 pm at 1:14 pm

    Just non-sens… and then who are you

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule