• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ

May 28, 2025 02:01 am by Editor 2 Comments

መለስ ዜናዊ ከስሙ ጀምሮ ሁሉ ነገሩ የውሸት ወይም ፌክ ነው። ላደረሰብን ግፍ እንክሰሰው እንኳን ብንል በየትኛው ስሙ ነው ፍርድ ቤት የምናቆመው የነበረው? ደግነቱ ከዚህ ሁሉ በፊት ወደ ዕረፍቱ ሄዶ እኛንም አሳረፈን።

መለስ የዕውቀት ችግር አልነበረውም፤ ዕድሜ ለኢትዮጵያ ከሥር መሠረቱ በነጻ አስተምራዋለች። ንጉሡም ሰው ነው፤ ነገ ሀገር ይጠቅማል ብለው ሸልመውታል ይባላል። ግን ያልታከመና ሥር የሰደደ የበታችነት ስሜት የነበረው፣ አስተሳሰቡ ደሃ የሆነ ሰው ነበር። በዚህ ደሃ አስተሳሰቡ ነበር ኢትዮጵያን ለመምራት ሥልጣን ኮርቻ ላይ የተፈናጠጠው። ሥልጣን፣ ሃብት፣ ድሎት፣ ወዘተ ቢመጣም አስተሳሰብ ደሃ ከሆነ ችግሩ ውስብስብና መፍትሔ ዓልባ ነው የሚሆነው።

መለስ ኢትዮጵያን በጣም ነበር የሚጠላት፤ ለማፍረስ ይፈልግ ነበር ለማለት ብዙም አያስደፍርም። ነገርግን ልክ እንደ ፖለቲካ ወላጅ አባቱ የሻዕቢያው ኢሳያስ ኢትዮጵያ ተዳክማና ደህይታ ማየት የዘወትሩ ምኞቱና ሕልሙ ነበር። ይህንንም ገና ሥልጣን ከመያዙ ጀምሮ በዕቅድ የሠራበት፤ ሕልሙንም ዕውን ያደረገበት ጉዞ ነበር።

ወደ ሥልጣን ሲመጣ ትህነግ የሚለውን የድርጅቱን ስም መለወጥ አልፈለገም። የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር የተባለውን የአሸባሪና የወንበዴዎች ስብስብ እየመራ አዲስ አበባ ገባ። በነጻ አውጪ ድርጅት ስምም የሚጠላትን አገር “አገሪቱ” እያለ መራ፤ “አገራችን ኢትዮጵያ” ለማለት እንደተጸየፈ ሞት ወሰደው። ደሃ አስተሳሰብ ቶሎ ካልተፋቱት እስከ መቃብር ነው ፍቅሩ።

መለስ ኤርትራ በግድ እንድትገነጠል አደረገ፤ በኤርትራ መገንጠል ዋና ትኩረት ያደረገው አሰብን ለኤርትራ ለመስጠትና ኢትዮጵያን ወደብ ዓልባ አድርጎ ማደኽየት ነው። እንዳሰበውም አደረገውና በቀን ሦስት ሚሊዮን ዶላር ኢትዮጵያ ለጅቡቲ ወደብ ኪራይ እንድትከፍል አደረጋት፤ በዓመት አይደለም በቀን፤ 3,000,000 ብር አይደለም፤ ሦስት ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በቀን!! ከዚህ ተነስተን ላለፉት 30+ ዓመታት ስንት እንደከፈልን መገመት አያዳግትም።

መለስ ድሃ አስተሳሰቡን ሲናገሩበት አይወድም፤ ያልተፈወሰ የበታችነት ስሜት የተጠናወተው ስለነበር የማይወደውን መከራከሪያ ለሚያመጡ ሰዎች የሚሰጠው ምላሽ በየጊዜው ልኩን ያሳበቀበት ሆኖ አልፏል። ለምሳሌ አሰብን በማጣታችን የኢኮኖሚ ጉዳት ይደርስብናል ወይ ተብሎ ሲጠየቅ፤ አሰብን ማጣት በኢኮኖሚው ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አያደርስም፤ ምንም ለውጥ አያመጣም፤ ኤርትራውያን ከፈለጉ ግመሎቻቸውን ያጠጡበት ነበር ያለው። ምስጋና ለፈጣሪ ይግባውና አሁን ትክክለኛ ባለቤቶቹ የአፋር ግመሎች ከቀይ ባሕር የሚጠጡበት ዘመን ላይ እንገኛለን።

የመለስ ውዳቂ፣ ተራ ምቀኝነት የተሞላበት፣ አይደለም የአገር መሪ ከማንም ሰው የማይጠበቅ አስተሳሰቡ የታየው በባድመ ጦርነት ወቅት ነበር። የግል ጠባቂው/አጃቢው የነበረው ሚኪ ራያ በጦርነቱ ወቅት አስመራ እየሄደ ኢሳያስን እጅ ሲነሳና በሰላም እንጨርሰው እያለ ሲለምን ነበር ብሎ ሰሞኑን ነግሮናል። እንዲያውም ኢሳያስ መለስ ዜናዊን “ጨምላቃ” ብሎ ሲሰድበው፤ መለስም ጭንቅላቱን እንዳዘቀዘቀ ድምፅ ሳያሰማ ስድቧን ጠጥቶ እንደወጣ ሚኪ ራያ ነግሮናል። ለነገሩ ለመለስ ዓይነት ነውር ቀለቡ ይህ ሽልማት ነው፤ ምክንያቱም የኢሳያስ ስድብ ለመለስ እንደ ቡራኬ ስለሆነ።

ይኸው የባድመ ጦርነት ካበቃ በኋላ ወደ አልጀርስ ስምምነት ለማድረግ ዝግጅት በሚደረግበት ወቅት ኢትዮጵያውያን ምሑራን እና ጠበቆች አሰብን ለማስመለስ አሁን ነው ጊዜውና ሙግቱን በጠንካራ ማስረጃ እናቅርብ፤ ክፍያም አንፈልግም፤ ለአገራችን በነጻ እናገልግል ብለው ቢጠይቁም መለስ “እናንተን አልፈልግም” ብሎ የውጭ አገር ዜጎችን በዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ቀጥሮ አሰብ ለኢትዮጵያ እንዳትሰጥ እንዲያደርጉ በርትቶ ነበር የሠራው። ይህንን መለስ ነው እንግዲህ ደጋፊና አምላኪዎቹ “world class mind” እያሉ ከሙታን መንደር እንደ ዓልአዛር እንዲነሳላቸው የሚያንቆለጳጵሱት።

የአስተሳሰብ ደሃ የሆነው መለስ ኢትዮጵያን ደሃ ማድረግ የተለማደው ትግራይ ላይ ነው። በ17ቱ ዓመት የበረሃ ውንብድና ዘመኑ እሱና ወንበዴ ጓደኞቹ ለትግራይ ተብሎ በዕርዳታ የተላከ ዘይት፣ እህል እና ዱቄት የትግራይ ሕዝብ እንዳያገኝ በማድረግ እንዲሰቃይና እንዲሞት ያደረጉ፤ እንታገልለታለን ለሚሉት ሕዝብ 50 ዓመት ሙሉ ሰቆቃን የጋቱ ጨካኞች ናቸው። ከዚህ አንጻር አሰብን በማጣት የሚደርስብ የኢኮኖሚ ጉዳት ለመለስ ደስታው ነው። ምክንያቱም ኢትዮጵያን አዳክሞና የትግራይ ተመጽዋች አድርጎ ታላቋን ትግራይ ሲመሠርት አሰብን ከኢትዮጵያ ከመቀበል ይልቅ ከኤርትራ ለመውሰድ ይቀላል ብሎ የራሱን ወንበዴ ጓደኞቹን ያሳመነው መለስ ነው። አሁን ግን ዘመን መጣ፣ ምርኮ የሚመለስበት ዘመን፣ የፈረሰው ባሕር ኃይላችን በደማችን የቀላውን ቀይ ባሕርን የሚቆጣጠርበት ዕድሜ ላይ ደረስን፤ አለመሞት ደጉ ይህን አሳየን።

መለስ የድሃ አስተሳሰቡን ውጪ አገር ሲሄድና ፈረንጆችን ሲያገኝ በጣም ጎልቶ ይታይበታል። አሽከራቸው፣ ተላላኪያቸውና ጉዳይ ፈጻሚያቸው ስለነበር፤ ለራሱ ክብር ነስቶ አገራችንን ክብር ያሳጣ ወራዳ ሰው ስለነበር ውጪ አገር ሲሄድ ሎሌነቱን በገሃድ ይታይበታል። አፍቃሪ ትህነጉ ቴዎድሮስ ጸጋዬ “ህወሃት ለመገርደድ ወይም ለግርድና የተፈጠረ ነው፤ ለሻዕቢያ ሲገረደድ ነው የኖረው፤ አሁንም በዚያው ነው የሚቀጥለው” በማለት የተናገረውን እዚህ ላይ መጥቀስ የመለስን እና የፈረንጅ አለቆቹን ግንኙነት በጥሩ የሚገልጥ ነው። ትህነግ ይኸው ቴዎድሮስ የተናገረው አባባል አልለቅ ብሎት የመለስ ሌጋሲ አስቀጣዮቹ እነ ደብረጽዮን ገደለን፣ ጨፈጨፈን፣ አረደን፣ ሴቶቻችንን ደፈረ፣ ዘረፈን፣ … ሲሉት ለነበረው ሻዕቢያ ወደውና ፈቅደው “እየተገረደዱ” ነው። መለስም ለፈረንጅ ጌቶቹ እንዲሁ ነበር፤ የአስተሳሰብ ድህነት ማለት ይህ ነው።

መለስ ውጪ አገራት ሄዶና “ተገርድዶ” ሲመለስ በጣም ሼም የሚሰማው ሰው ነበር። ይህንን ኻፍረቱን ለመሸፈንም ወደ አገር ሲመለስ መወራጨት ይጀምራል። ቶሎ ብሎ ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ወይም የፓርላማ ስብሰባ ላይ በመከሰት ሕዝቡን፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰዎችን፣ በአቅራቢያው ያሉትን ወንበዴ ጓደኞቹን፣ … ምንም የሚቀረው የለም አፉ እንዳመጣለት ይሳደባል። ሁኔታው “እኔ ለጌቶቼ እንደተገረደድሁ እናንተም ለኔ ትገረደዳላችሁ” ይመስላል። ይህ ነው እንግዲህ በደጋፊዎቹ “world class mind” የተባለለት መለስ።

መለስ በዚህ የወረደ የበታችነት አስተሳሰቡ ከዘረኝነት ጀምሮ ጥሎልን የሄደው የድንቁርና ኮተትና ዝባዝንኬ ለኢትዮጵያ ቆፍሮ የሄደው ጉድጓድ ነው። በዚህ ትውልድ ሙሉ በሙሉ መደፈን ባይችልም ሥራው ግን ተጀምሯል። መለስንና ትህነግን የሚያስታውሱን እዚህ ጉድጓድ ውስጥ እየተቀበሩ በምትኩ ኢትዮጵያዊነት እየጎላና እያበበ መሄዱ አይቀሬ ነው።   

መለስ ዜናዊ ደሃ አስተሳሰብ የተጠናወተው፤ በበታችነት ስሜት የተሰቃየ ተራ ሆኖ ኢትዮጵያን ተራ ያደረገ ነበር። ስለ እርሱ ይህንን ያህል ከተባለ ይበቃዋል። የሌላኛው መሪ ወግ ግን በአንድ ዐርፍተ ነገር ይጠቃለላል፤ ግንቦት 20ን ተራ የሥራ ቀን አደረገልን። (ነሐሴ ፲፬ ነኝ ከ፬ ኪሎ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions, Politics Tagged With: abiy ahmed, ginbot 20, may 28, meles zenawi, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    May 28, 2025 10:04 pm at 10:04 pm

    የጅል መንጋ ሲንጋጋ ጊዜው መሽቶ ነጋ
    ትላንትን በዛሬ መዝኖ ግጠሙኝ አለ ፎክሮ
    ጊዜው ተለውጦ ተቀይጦ የሰው መልኩ ሁሉ ተረስቶ
    አውሬ መሰለ ባህሪው ተለውጦ
    የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው ብሎ ታቅፎ
    ተመልሶ ይቧቀሳል ደም ተጠምቶ
    በልቶ አዳሪ የታደለ ጦም አዳሪ ያልታደለ
    ተገናኙ በሜዳ ላይ በወረፋ ሊሯሯጡ
    በእሳት ቋንቋ ሊናገሩ፤ ጊዜ ዘሞ ሲራኮቱ
    ሃገር ቤትም ተቃጠሉ
    ዜሮ ጅምር ዜሮ ድምር
    ሁሉም ባዶ ሆነ ድሉ።

    Reply
  2. Tefera says

    May 29, 2025 01:14 pm at 1:14 pm

    Just non-sens… and then who are you

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule