• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን!

April 9, 2025 10:28 pm by Editor 1 Comment

የመለስ ዜናዊ የግል ጠባቂ/አጃቢ የነበረው ሚኪ ራያ ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያ በተሰራጨ ቪዲዮ ላይ የቀድሞ ጌታውን ማንነት ባልታወቀ ምክንያት እያዝረከረከው ነው። በትግሪኛ የተናገረውን አስፋው አብርሃ በቴሌግራም ገጹ ተርጉሞ አቅርቦታል፤

መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ከኢትዮጵያ በበለጠ ለኤርትራ ያስቡና ይጨነቁ ነበር። ይህ የሁለቱ ሰዎች ስሜትና ባህሪ  በተለያዩ  አጋጣሚዎች ተገልጧል – ከ1992ቱ ጦርነት በፊት፣ በጦርነቱ ወቅት እና ከጦርነቱ በኋላ ምንም ያልተቀየረ ስሜት!

ከጦርነቱ በፊት ….

ሚኪ ራያ “መለስ ዜናዊ  መዝናናት ሲፈልግ ወደ አስመራ ይመላለስ ነበር፤ በረራውም Unofficial በረራ ነበር ይለናል – ያው በድብቅ ማለት መሆኑ ነው።

“መለስ ዜናዊ ከስራ ውጪ መዝናናት ሲፈልግ አስመራ ነበር የሚሄደው። የራሱን ሰዎች ብዙም አይቀርባቸውም ነበር። እኔ ቢያንስ ለሦስት ጊዜ ያህል ከሱ ጋር ወደ አስመራ unofficial በረራዎችን አድርገናል። ኢሳያስና መለስ በሁለት አገሮች ውስጥ ያሉ ወንድማማቾች ይመስሉ ነበር። በቃ በሁለት አገር ያሉ ሁለት ዳይናስቲዎች ነበሩ ማለት ትችላለህ። Scary ነው ግን እውነታው እሱ ነበር”።

ሚኪ ራያ መለስ ዜናዊን በ1992ቱ የባድመው ጦርነት ወቅት በዚህ መልኩ ይገልጸዋል፤

ጦርነቱ ተጀምሮ ሠራዊቱ ውጊያ ላይ እያለ መለስ ዜናዊ ለአስመራ እጅግ ከመጨነቁ የተነሳ ፕሮቶኮልንና አግባብነትን የተቃረነ አስነዋሪ ሥራ ሠርቷል።

ጦርነቱ ተጀምሮ የኢትዮጵያ ወታደሮች እየተዋደቁ ባለበት ቅፅበት አገሪቱ (ኢትዮጵያ) ሳታውቅ መለስ ወደ አስመራ ሄዶ ነበር። አንድ መሪ አገሪቱ በመሰል ወሳኝ ሁነት ውስጥ እያለች ከወታደራዊ ካውንስልም ሆነ ከካቢኔው ዕውቅና ውጪ በግሉ ወስኖ በግሉ የሚፈፅመው ምንም አይነት ተነሳሽነት ሊኖረው ተገቢ አልነበረም። መለስ ግን አድርጎታል። ጦርነቱ ኤርትራን እንደሚጎዳ ስላወቀ የተጀመረው ጦርነት እንዲቆም ኢሳያስን ለማሳመን ነበር ወደ አስመራ የሄደው። በነገራችን ላይ መለስ ዜናዊ ኤርትራን የሚመለከትበትና የሚያስተናግድበት መንገድ በፃድቃንና በስዬ ተደጋጋሚ ወቀሳና ትችትን አስተናግዷል።

ወደ ታሪኩ ስንመለስ ጦርነቱ ተጀምሮ በሁለቱም ወገን ያለው ወታደር በተጋጋለ ተኩስ ውስጥ ተጥዶ እያለ እሱ ወደ አስመራ መሄዱ ምን ያህል በሕይወቱ ላይ እንደፈረደ ለመገመት አይከብድም። የሚያሳዝነው ግን ከኢሳያስ ጋር የነበረው ግንኙነት በቅሌት ነበር የተጠናቀቀው።

እንደ ሚኪ ራያ ገለፃ ከሆነ በወቅቱ ከመለስ ጋር የሄደውና ከውጪ ሆኖ ሲጠብቅ የነበረ ታጋይ (አሌ ይባላል) ጭቅጭቅ ሰምቶ ወደ ውስጥ ሲገባ ኢሳያስ መለስ ዜናዊን “ጨምላቃ” ብሎ ሲሰድበው ሰምቷል። መለስም ጭንቅላቱን እንዳዘቀዘቀ ድምፅ ሳያሰማ ስድቧን ጠጥቷታል!

መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን!

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: Isayas Afewerki, meles zenawi, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Haymanot Amare says

    June 13, 2025 01:55 pm at 1:55 pm

    ስላም ፍላጊ አኝብ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule