• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን!

April 9, 2025 10:28 pm by Editor 1 Comment

የመለስ ዜናዊ የግል ጠባቂ/አጃቢ የነበረው ሚኪ ራያ ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያ በተሰራጨ ቪዲዮ ላይ የቀድሞ ጌታውን ማንነት ባልታወቀ ምክንያት እያዝረከረከው ነው። በትግሪኛ የተናገረውን አስፋው አብርሃ በቴሌግራም ገጹ ተርጉሞ አቅርቦታል፤

መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ከኢትዮጵያ በበለጠ ለኤርትራ ያስቡና ይጨነቁ ነበር። ይህ የሁለቱ ሰዎች ስሜትና ባህሪ  በተለያዩ  አጋጣሚዎች ተገልጧል – ከ1992ቱ ጦርነት በፊት፣ በጦርነቱ ወቅት እና ከጦርነቱ በኋላ ምንም ያልተቀየረ ስሜት!

ከጦርነቱ በፊት ….

ሚኪ ራያ “መለስ ዜናዊ  መዝናናት ሲፈልግ ወደ አስመራ ይመላለስ ነበር፤ በረራውም Unofficial በረራ ነበር ይለናል – ያው በድብቅ ማለት መሆኑ ነው።

“መለስ ዜናዊ ከስራ ውጪ መዝናናት ሲፈልግ አስመራ ነበር የሚሄደው። የራሱን ሰዎች ብዙም አይቀርባቸውም ነበር። እኔ ቢያንስ ለሦስት ጊዜ ያህል ከሱ ጋር ወደ አስመራ unofficial በረራዎችን አድርገናል። ኢሳያስና መለስ በሁለት አገሮች ውስጥ ያሉ ወንድማማቾች ይመስሉ ነበር። በቃ በሁለት አገር ያሉ ሁለት ዳይናስቲዎች ነበሩ ማለት ትችላለህ። Scary ነው ግን እውነታው እሱ ነበር”።

ሚኪ ራያ መለስ ዜናዊን በ1992ቱ የባድመው ጦርነት ወቅት በዚህ መልኩ ይገልጸዋል፤

ጦርነቱ ተጀምሮ ሠራዊቱ ውጊያ ላይ እያለ መለስ ዜናዊ ለአስመራ እጅግ ከመጨነቁ የተነሳ ፕሮቶኮልንና አግባብነትን የተቃረነ አስነዋሪ ሥራ ሠርቷል።

ጦርነቱ ተጀምሮ የኢትዮጵያ ወታደሮች እየተዋደቁ ባለበት ቅፅበት አገሪቱ (ኢትዮጵያ) ሳታውቅ መለስ ወደ አስመራ ሄዶ ነበር። አንድ መሪ አገሪቱ በመሰል ወሳኝ ሁነት ውስጥ እያለች ከወታደራዊ ካውንስልም ሆነ ከካቢኔው ዕውቅና ውጪ በግሉ ወስኖ በግሉ የሚፈፅመው ምንም አይነት ተነሳሽነት ሊኖረው ተገቢ አልነበረም። መለስ ግን አድርጎታል። ጦርነቱ ኤርትራን እንደሚጎዳ ስላወቀ የተጀመረው ጦርነት እንዲቆም ኢሳያስን ለማሳመን ነበር ወደ አስመራ የሄደው። በነገራችን ላይ መለስ ዜናዊ ኤርትራን የሚመለከትበትና የሚያስተናግድበት መንገድ በፃድቃንና በስዬ ተደጋጋሚ ወቀሳና ትችትን አስተናግዷል።

ወደ ታሪኩ ስንመለስ ጦርነቱ ተጀምሮ በሁለቱም ወገን ያለው ወታደር በተጋጋለ ተኩስ ውስጥ ተጥዶ እያለ እሱ ወደ አስመራ መሄዱ ምን ያህል በሕይወቱ ላይ እንደፈረደ ለመገመት አይከብድም። የሚያሳዝነው ግን ከኢሳያስ ጋር የነበረው ግንኙነት በቅሌት ነበር የተጠናቀቀው።

እንደ ሚኪ ራያ ገለፃ ከሆነ በወቅቱ ከመለስ ጋር የሄደውና ከውጪ ሆኖ ሲጠብቅ የነበረ ታጋይ (አሌ ይባላል) ጭቅጭቅ ሰምቶ ወደ ውስጥ ሲገባ ኢሳያስ መለስ ዜናዊን “ጨምላቃ” ብሎ ሲሰድበው ሰምቷል። መለስም ጭንቅላቱን እንዳዘቀዘቀ ድምፅ ሳያሰማ ስድቧን ጠጥቷታል!

መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን!

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: Isayas Afewerki, meles zenawi, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Haymanot Amare says

    June 13, 2025 01:55 pm at 1:55 pm

    ስላም ፍላጊ አኝብ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule