• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ

November 5, 2025 12:06 pm by Editor Leave a Comment

* “እኛ የገባነው ልናፈርሰው ነው” ሕዝቅኤል ገቢሣ

በሰላማዊ ትግል መንግሥት ለመጣል ማቀዱን አስታውቆ ሃያ አንድ ቦርድ አባላትን ሰይሞ የሰነበተው የ-አብሮነት ማኅበር ሰባት ሥራ አስፈጻሚዎችን መምረጡ ታወቀ። ማኅበሩ “ለቦርድ አባላት” በሚል ባሰራጨው የ“እንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አቶ ልደቱ፣ ከአማራ የማኅበሩ ፕሬዚዳንትና ሊቀመንበር ሆነዋል። መቅደስ አዳነ ከወላይታ (ምክትል)፣ አሸናፊ አብርሃም ከደቡብ (ጸሐፊ)፣ ሙሉጌታ ዘለቀ ከአማራ (ገንዘብ ያዥ)፣ የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ሕዝቅኤል ገቢሣ /በተለይ እንግሊዘኛና ትግርኛ ጠንቀቀው ስለሚያውቁ/ ከኦሮሞ፣ የድርጅት አስተባባሪ እስማኤል ጎርሴ ከሶማሌ፣ የውጭ ግንኙነት ኦፊሰር መስፍን አየነው ከትግራይ መመረጣቸው ይፋ አድርጓል።

ቀደም ሲል ምርጫው ከመደረጉ በፊት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አባላቶች ሕቡዕ እንደሚሆኑ ተመልክቶ እንደነበር የስብሰባው ተሳታፊዎችን ጠቅሰን መዘገባችን አይዘነጋም። ያለፈው ሳምንት ባለመግባባት ምርጫው ሳይካሄድ ከቀር በኋላ ሃሳብ ተቀይሮ ሕቡዕ እንዲሆኑ ተወስኖ የነበረው የሥራ አስፈጻሚዎች ዝርዝር ታውቋል።

በተከታታይ ለዲሲ የአዲስ ሪፖርተር ተባባሪ መረጃ የሚሰጡት ወገኖች እንዳሉት ከሆነ ሰኞ ዕለት በተካሄደው ምርጫ ቀደም ሲል አቶ ልደቱ በግል እንዳይመረጥ ቅስቀሳ ያደረጉበት የርዕዮት ሚዲያ ባለቤት ቴዎድሮስ ጸጋዬ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሳይሆን ቀርቷል።

ቴዎድሮስ ባለፈው ሳምንት ባለመግባባት ምርጫ ማድረግ ሳይቻል በተበተነው ስብሰባ ላይ እጁን ሳያወጣ በተደጋጋሚ በመናገር ስብሰባውን በመበጥበጡ፣ ከሁሉም በላይ ግን ከሻዕቢያ ጋር ግንኙነት ያላቸውን አጥብቆ ስለሚቃወም፣ በተቃራኒው ሻዕቢያን የሚቃወሙትን ስለሚደግፍ ነበር አቶ ልደቱ በግል ስልክ እየደወሉ ምርጫ ውስጥ እንዳይገባ የቀሰቀሱበት።

ያለፈው ስብሰባ ከተበተነ በኋላ ቴዎድሮስ ሥራ አስፈጻሚ ውስጥ እንዳይመረጥ አቶ ልደቱ ካነጋገሯቸው መካከል ሁለቱ ለአዲስ ሪፖርተር እንዳሉት “ቴዎድሮስ ከሰማ የሚዲያ ዘመቻ ስለሚከፍትብን ምሥጢር ይሁን” ሲሉ አቶ ልደቱ መናገራቸውን አመልክተዋል። አቶ ልደቱን በግል ስልካቸው በማግኘት ለማነጋገር ተባባሪያችን ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።

ፕሮፌሰር ሕዝቅኤል ገቢሣ ምርጫው እየተደረገ ሳለ “diversity (ብዘሃነትን) አትከተሉም” በማለት አስቀድመው ተቃውሞ አሰምተው እንደነበር የተናገሩት የመረጃው ባለቤቶች፣ ስብሰባው ካለቀ በኋላ እንደሰሙት ከሆነ መመረጣቸው ከተነገራቸው መካከል መልቀቂያ ያስገቡም አሉ። (የሕዝቅኤል ተቃውሞ ሰባት አባላት ባሉበት ቡድን ሁለት አማራ እንዴት ይሆናል ከሚል የመነጨ ነው በሚልም ተወስዷል)

ከአቶ ስብሃት ነጋና ከሻዕቢያ ሰዎች ጋር አብረው እንደሚሠሩ፣ በምስራቅ ኢትዮጵያ አቅጣጫ የተጀመሩ ሰፋፊ ፕሮጀክቶችን ለማስተጓጎልና ጦርነቱን ለማስፋት በግብጽ መሾማቸው የተሰማባቸው ሕዝቅኤል፣ ከሚቀርቧቸው ሰዎች ጋር ሆነው የ-አብሮነት እንደሚፈርስ ስብሰባ በተደረገ በአንድ ቀን ውስጥ መናገራቸው ተሰምቷል።

“እኔና መስፍን አየነው የገባነው ስብስቡን ለማፍረስ ነው” በማለት ፕሮፌሰሩ መናገራቸውን የሰሙት እነ አቶ ስብሃት ነጋ የሚመሩትን ቡድን የሚቃወሙ ሌላኛው የትግራይ ቡድን ደጋፊዎች ሲሆኑ፣ ሕዝቅኤል “አዲስ የተቋቋመ አደረጃጀት አለ። ከአብሮነት ውስጥ የሚፈለጉትን ወደዚያ እንወስዳለን። የ-አብሮነት ነገር አይታመንም። የሌሎችን መብትና ስብጥር አያከብርም” ማለታቸው ታውቋል። እሳቸውንም በግል ስልካቸው ለማግኘት በተደጋጋሚ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም።

እነዚሁ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የመረጃ ምንጮች ለተባባሪያችን እንዳሉት ሕዝቅኤል አዲስ እየተመሠረተ ነው ያሉት አደረጃጀት እሳቸው ያሉበት ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ ያደራጁትና እነ አቶ ስብሃት ነጋ፣ አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ከኋላ የሚመሩት ነው።

ከሃያ አንዱ የቦርድ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ታምራት ላይኔ፣ አስቀድመው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ለመሆን ፈቃደኛ ሆነው የነበሩ ቢሆንም፣ በሰላማዊና የትጥቅ ትግል ስልት ላይ ክርከር ከተካሄደ በኋላ በሰኞው ዕለት ምርጫ ርሳቸውን ከሥራ አስፈጻሚነት ተወዳዳሪነት ማግለላቸውን በስብሰባው የተካፈሉ አስታወቀዋል።

የ-አብሮነትን አብረው አጅበው የነበሩት እነ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ ኢተና ወዘተ የመሳሰሉት ሙሉ በሙሉ ራሳቸውን ማግለላቸውን ጠቅሰን መዘገባችን አይዘነጋም። ይህም የሆነው በአገር ውስጥ የኦሮሞ ተወላጆች በሰነዘሩባቸው ተቃውሞ መሆኑ አይዘነጋም።

ቡድኑ ሥራ ሲጀምር በአገር ውስጥ የሕቡዕ አደረጃጀት በማስፋፋት የተቃውሞና ዓድማ እንደሚያደራጅ አቶ ልደቱ በተደጋጋሚ መናገራቸው አይዘነጋም። የ-አብሮነት ከአገር ውስጥ አብሮ ካሉ የተወሰኑ ድርጅቶች ጋር እንደሚሠራ፣ አንዳንዶቹም በጅምሩ ወቅት በይፋ በዙም (Zoom) ስብሰባ ይካፈሉ እንደነበር የሚታወስ ነው። (አዲስ ሪፖርተር)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics, Slider Tagged With: ezikiel gebissa, issac ephraim, lidetu ayalew, operation dismantle tplf, sebhat nega, ye-abronet

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule