ከሰሞኑን ከትግራይ ክልል አንድ ምሥጢራዊ ሰነድ ሾልኮ ወጥቶ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። በማኅበራዊ ሚዲያዎችም በርካቶች እየተቀባበሉት ይገኛሉ። ምሥጢራዊ ሰነዱ ፥ የሕገወጥ የሰዎች ዝውውር (በብዛት ኤርትራውያን በሕገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወር የሚመለከት) እና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ የተጠና ሰነድ ሲሆን በ4 ክፍሎች የተከፋፈሉ 69 ገፆች አሉት። በሰነዱ በጥናት የተለዩ የወንጀል ተግባራት ፦* ሥልጣን ያለአግባብ በመጠቀም* በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በመያዝና በማዘዋወር (መኒ ላውንደሪንግ money laundering)* ሰው ማፈንና መሰወር* በሕገወጥ መንገድ ሰዎችን ከአገር ወደ አገር ማዘዋወር* የመንግሥት ስራ ምቹ ባልሆነ መንገድ መምራት* ኃላፊነት ባልተገባ መንገድ በመጠቀም* ሙስናመፈፀማቸውን ያረጋግጣል። በሰነዱ በተጠቀሱ የወንጀል ተግባራት በሠራዊት አመራር ያሉ … [Read more...] about ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው?
Disengage TPLF
በፊርማው ስምምነት መሠረት የትህነግ ታጣቂዎች ከ፱ ግምባሮች ለቀቁ
በሰላም ስምምነቱ መሰረት የትግራይ ታጣቂዎች በስራቸው ከነበሩ የውግያ ግምባሮች ለቀው መውጣት እንደጀመሩ ተገልጿል። ታጣቂዎቹ ከደቡብ፣ ማይ ቅነጣል፣ ዛላምበሳ፣ ነበለት፣ ጨርጨር፣ ኩኩፍቶ፣ ሕጉምብርዳ፣ በሪተኽላይ እና አበርገለ ለቆ ግንባሮች ነው መውጣት እንደጀመሩ ከክልሉ መገናኛ ብዙሃን የተሰማው። ከጥቂት ቀናት በፊት (የትግራይ ኃይሎች አዛዥ) ታደሰ ወረደ በሰጡት መግለጫ በናይሮቢው ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለኃይሎቻቸው ኦረንቴሽን (orientation) ሲሰጥ እንደነበር እና ይኸው ኦረንቴሽን እንዳለቀ ኃይላቸው ካለበት ቦታ Disengage አድርጎ / ተላቆ የውጊያ ግንባሮች የማፍረስ እና ሰራዊቱ ወደ ተቀመጠለት ቦታ እንደሚጓጓዝ መግለፃቸው አይዘነጋም። አዛዥ ኃላፊው ታደሰ ፤ "የሎጅስቲክስ አቅማችን ወይም የማጓጓዝ አቅማችን እስከፈቀደ ድረስ በአንድ ጊዜም … [Read more...] about በፊርማው ስምምነት መሠረት የትህነግ ታጣቂዎች ከ፱ ግምባሮች ለቀቁ


