• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቀሲስ በላይን ፊት አድርጎ የተሞከረው የማጭበርበር ሤራ ከሸፈ

April 28, 2024 03:40 am by Editor Leave a Comment

* ሚዲያው አስቀድሞ ዝግጅት አድርጎበታል

ቀሲስ በላይን ግንባር አድርጎ አፍሪካ ኅብረትን ለመዝረፍ የተወጠነው ሤራ መክሸፉ አርብ ዕለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አለሳልሶ ይፋ አድርጎታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃላ አቀባይ አቶ ነቢዩ ተድላ “ጉዳዩ በሕግ ያለ ነው። ዝርዝር ልንናገር አንችልም። የተሞከረው ጥቃት ግን ከሽፏል። ጉዳዩ ወደ ሌላ ደረጃ ሳያልፍ ወይም ጉዳት ሳያስከትል ለመቆጣጠር ተችሏል” ማለታቸው ጉዳዩ ሤራ መሆኑን ያመላክታል።

“ከኅብረቱ ጋር ባደረግነው ቀጥተኛ ውይይት ይህ አይነት እሳቤ በተቋሙ ውስጥ እንደሌለ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አረጋግጠዋል” ሲሉ በመግለጫቸው ያመለከቱት አቶ ነቢዩ ጉዳዩ ሕግ የያዘው በመሆኑ ዝርዝር ለመስጠት እንደማይችሉ ገልጸዋል። የጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ዜናው ከተሰማበትና ሪፖርተር ጋዜጣ በአማርኛና በእንግሊዘኛ ሁለት የተለያዩ ዜናዎች ካሰራጨ በኋላ የተለያዩ አካላትንና ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ክፍሎችን ለማነጋገር ሞክሯል።

ተባባሪያችን መረጃዉን ጠቅሶ እንዳለው ከሆነ አጀንዳውና ሤራው በቀሲስ በላይ ተግባር የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ተዓማኒነት የሌለው አድርጎ በማሳየት “አፍሪካ ኅብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለውን ዜና ማራገብ ነበር። እንደመረጃው ከሆነ ለጊዜው ስማቸው የማይጠቀሱ ስድስት ሚዲያ አውታሮች ጉዳዩን በፍጥነት እንዲያራቡ የሤራው አቀናባሪዎች አስቀድመው ዝግጅት አድርገዋል።

“ነጻ ፕሬስን” ተገን አድርገው የሚሠሩትና በዚሁ ጥላ ሥር የሚርመሰመሱትን አካላት ለዚሁ ሤራ ያዘጋጀው ይህ “ተራና ሊሳካ የማይችል” የተባለ የዝርፊያ ሙከራ ቀድሞ በሚፈለገው መልኩ በእንግሊዝኛ ያሰራጨው ሪፖርተር የሤራው አካል ይሁን አይሁን መረጃውን በዝርዝር የሰጡት ክፍሎች አላስታወቁም። ይሁን እንጂ ሪፖርተር በአማርኛ ዘገባ ያልጻፈውን “ዋና ተፈላጊ አስኳል ጉዳይ” በእንግሊዝኛ ማቅረቡ ብዙ መልዕክቶች እንዳሉት በርካታ አስተያየት ሰጪዎች በቁጣና በትችት ገልጸዋል።

ዜናውን ከሪፖርተር እንግሊዘኛ ወስደው ያራቡትን ጨምሮ ለዚሁ ተግባር የተዘጋጁት ሌሎች ሽፋናቸው ሚዲያ የሆኑ ዜናውን በሚፈለገው መጠን ያላሰራጩት ከአፍሪካ ኅብረት ከፍተኛ ኃላፊዎች ዘንድ ወዲያውኑ ቅሬታ በመነሳቱ እንደሆነ የጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ሰምቷል።

ባለፉት ሦስት ዐሥርተ ዓመታት የትህነግ ኃይሎች አፍሪካ ኅብረት ውስጥ በብዛት መሰግሰጋቸውን ያወሱት የዜናው ባለቤቶች ይህ ሤራ በነዚሁ አካላት የተገመደና ሆን ብለው “የተከበሩ” የሚባሉ የቤተ ክህነት ሰው በመጠቀም ሤራውን ክብደት እንዲኖረው ማድረጋቸውን ያክላሉ። የሤራውን አካሄድ በውል የተረዱት ወገኖች እንደሚሉት ስማቸው ሳይጠቅስ ለሪፖርተር መረጃ እንዲሰጠው ያደረጉት እነዚሁ ወገኖች ናቸው ይላሉ። ሪፖርተር በእንግሊዝኛ ባወጣው ዘገባ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአፍሪካ ኅብረት ምንጭ ኅብረቱ የባንክ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር በማድረግ ሃሳብ ላይ ወስኗል ብለው እንደነገሩት ዘግቦ ነበር።

ዜናው ይፋ ከሆነ ጀምሮ ቀሲስ በላይን አፍሪካ ኅብረት ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይዘዋቸው የሄዱት ሰዎች ማንነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ዘገባዎች አለመሰማታቸው፣ ፖሊስ በፍርድ ቤት አፍሪካ ኅብረት ግቢ ውስጥ ያሉትን የካሜራ መረጃዎች ከመጠየቁ ጋር አንድ ላይ ተዳምሮ “ከጀርባ ያሉት እነማን ናቸው?” የሚለውን ጉዳይ እንደሚያጎላው ጉዳዩን በአንክሮ የሚከታተሉ ይገልጻሉ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ “ጉዳዩ በሕግ ተይዟል” ሲሉ ለጊዜው ዝምታ ቢመርጡም፣ ጎልጉል ባለው መረጃ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ሙሉ መረጃውን አግኝተውታል። ቀድሞውንም “ኅብረቱ የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር ሊያዘዋውር ነው” ለሚለው የሤራ ዜና ሲባል እንጂ በተግባር ዝርፊያ ሊከናውን እንደማይችል ተረድተው ሤራውን የከወኑትን አካላት ቀሲስ በላይ ፍርድ ቤት በቀረቡ ዕለት ለምን ለችሎቱ ይፋ አላደረጉም በሚል ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጠው ይህ መረጃ አድሮ ይፋ እንደሚሆን የዜናው ባለቤቶች አክለው አስታውቀዋል።

ሪፖርተር በዚህ ርቀት ዜናውን የሠራበት፤ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ያወጣው ዘገባ የተለያየ የሆነበት፤ ከዚህ በፊትም እንደዚሁ ዓይነት በሤራ የተገመዱ ዘገባዎችን በተደጋጋሚ ሲያወጣ መቆየቱ፤ ወዘተ ትያቄ የሚያስነሱ ጉዳዮች ሆነዋል። ለአብነት ከሚጠቀሱት መካከል አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ የተመሠረተ ቀን እጅግ በርካታ ጉዳዮች በአፈ ጉባዔ ታገሠ ጫፎም ሆነ በዋነው ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን የተነገሩ ቢሆንም ሪፖርተር ግን የዜናው ዋና ሃሳብ ያልሆነውን አጀንዳ በማንሳት ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ መንግሥት ጣልቃ ከገባብን ሥልጣኔን እለቃለሁ አሉ በሚል ርዕስ ከጥሩ ገላጭ ፎቶ ጋር ያወጣው የተንሻፈፈ ዘገባ አንዱ ተጠቃሽ ነው።

ከሁሉ በላይ የሚዲያው ኃላፊ በቅርቡ ከተመሠረተው የኢትዮጵያ ሚዲያ ካውንስል ጋር ያለው ቁርኝት ይሆን ሪፖርተርን ለዚህ ዓይነት ሙያዊ ሥነምግባር የጎደለው ዘገባዎች እንዲያወጣ ያደረገው የሚለው ሌላ የሚነሳ ጥያቄ ሆኗል። ይህ ዓይነት የጥቅም ግጭት (conflict of interest) ካለ በገለልተኛ ወገን ጉዳዮች የሚታዩበት አግባብ ሊኖር ይገባል የሚል የመከራከሪያ ሃሳብ የሚያቀርቡ መኖራቸውን መረጃ አቀባያችን ጠቁሟል።    

የጀርመን ድምጽ የተንሻፈፈውን የሪፖርተር ዘገባ በተመለከተ የዘገበውን ከዚህ በታች አቅርበናል፤

የአፍሪቃ ሕብረት “የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” በሚል የተሰራጨው መረጃ “የተሳሳተ” ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ (አርብ) አስታወቀ። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ ነቢዩ ተድላ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የአፍሪቃ ሕብረት በግቢው ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳቡ ላይ በሀሰተኛ ሰነድ ገንዘብ ለማዘዋወር የተደረገበትን ሙከራ ተከትሎ መሰል መረጃዎች ቢወጡም “ከሕብረቱ ጋር ባደረግነው ቀጥተኛ ውይይት ይህ አይነት እሳቤ በተቋሙ ውስጥ እንደሌለ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አረጋግጠዋል” ሲሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከሕብረቱ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ባደረገው ውይይት “በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለው የድርጅቱ ሒሳብ በአስተማማኝ ሁኔታ እየተጠበቀ እንደሆነ” የሕብረቱ ኃላፊዎች መናገራቸውንም ቃል አቀባዩ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ የሆኑት ሊቀ ዐዕላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ከሳምንት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ተቀማጭ በሆነው አሕጉራዊው ድርጅት የአፍሪቃ ሕብረት ዋና ግቢ ውስጥ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመቅረብ፣ “ከሕብረቱ የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ” በተባሉ ሀሰተኛ ሰነዶች በመጠቀም ከሕብረቱ የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ ሒሳብ ከስድስት ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማዘዋወር ሲሞክሩ መያዛቸውን ተከትሎ፤ በሀገር ውስጥ ተነባቢ የሆነው The Report የእንግሊዝኛው ጋዜጣ፤ በስም ያልተጠቀሱ የአፍሪቃ ሕብረት የገንዘብ ባለሙያዎችን ዋቢ አድርጎ ሕብረቱ የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ከኢትዮጵያ ሊያዘዋውር መሆኑን እንደገለፁለት ዘግቧል።

ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከሕብረቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በቀጥታ መወያየታቸውን የገለፁት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢዩ ተድላ መረጃው “ትክክለኛ አይደለም” ብለዋል። የተፈጠረው ክስተት በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ነባራዊ ሁኔታ ላይ ያስከተለው ተጽዕኖ ስለመኖር አለመኖሩ የጠየቅናቸው ቃል ዐቀባዩ “ጉዳዩ በሕግ ያለ ነው። ዝርዝር ልንናገር አንችልም። የተሞከረው ጥቃት ግን ከሽፏል። ጉዳዩ ወደ ሌላ ደረጃ ሳያልፍ ወይም ጉዳት ሳያስከትል ለመቆጣጠር ተችሏል” በማለት መልሰዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Politics, Religion Tagged With: African Union, EOTC, Kesis Belay, Reporter

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule