• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

February 15, 2023 03:13 pm by Editor 1 Comment

“የቀረው ደግሞ ወደ ትግራይ ሄደን የቀሩትን ማምጣት ነው”

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አባቶች መካከል ተፈጥሮ የነበረው አለመግባባት በንግግር እና ውይይት መፈታቱ ተገልጿል።

ቤተክርስቲያኗ ያጋጠማትን ፈተና ለመፍታት የሃይማኖት አባቶቹ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሀገር ሽማግሌዎች በጋራ ምክክር አድርገዋል።

በውይይታቸውም አንድነትን የሚያፀና እና አገልግሎትን የሚያሰፋ መንገድ መከተል ተገቢ መሆኑን በማመን ከስምምነት መደረሱን የሃይማኖት አባቶች ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል።

ከቋንቋ ጋር በተገናኘ የሚነሡ ሐሳቦችን ለመመለስ ቤተክርስቲያን የጀመረችውን ሥራ አጠናክራ እንድትቀጥል ከመግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን በበጀት እና በሰው ኃይል ማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶታል።

በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ እምነትን ለማጠናከር የሚያስችሉ ማሰልጠኛ ኮሌጅ እና ዩኒቨርስቲዎች እንዲጠናከሩ እና ቤተ እምነትን ለትውልድ ለማሻገር መፈታት የሚገባቸውን ችግሮች በጥናት እና በአሠራር መፍታት እንደሚገባም መተማመን መፈጠሩ በመግለጫው ተጠቁሟል።

የስምምነቱ አንኳር ነጥቦች፤

“ስምምነቱ ማስገደጃ ሆኖ የቀረበ ሳይሆን የቤተክርስቲያን ስርዓት ቀኖና ባከበረና ባስከበረ ሙልኩ የተከናወነ ነው” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ አብርሃም።

ከሰሞኑ ያጋጠመውን ፈተና ለመፍታት ከሁለቱም ወገን ያሉ አባቶች ተገናኝተው ምክክር ማድረጋቸውና ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።

የስምምነቱ ዋና ነጥቦች

የካቲት 8 ቀን 2015 ባደረግነው ውይይት የሚከተሉትን የመግባቢያ ሐሳቦች ላይ ደርሰናል።

1. በኦሮሚያ ክልል በኦሮምኛ ቋንቋ ትምህርት፤ ቅዳሴ እና ሌሎችም አገልግሎቶች እንዲሰጡ የተጀመረው ሥራ የሕዝቡን ጥያቄ በሚመልስ መልኩ እንዲጠናከር። ለዚህም ከዚህ በፊት ከተደረገው በተጨማሪ አስፈላጊው በጀትና የሰው ኃይል እንዲመደብ፤

2 በኦሮሚያና በሌሎች አካባቢዎች የተዳከመ አብያተ ክርስቲያናት ቋንቋውን በሚያውቁ አገልጋዮችና በአገልግሎት እንዲጠናክሩ አስፈላጊው ዕቅድ ተዘጋጅቶ ከበፊቱ በበለጠ ተገቢው በጀትና የሰው ኃይል እንዲመደብ፤

3. በኦሮሚያ እና በሌሎች አካባቢዎች የሚያገለግሉ ቋንቋውን የሚያውቁ አገልጋዮችን የሚያሰለጥኑ ኮሌጆች እና ማልጠኛዎች እንዲከፈቱ፤ የተከፈቱትም እንዲጠናከሩ እንዲደረግ፤

4. ለኦሮሚያ አህጉረ ስብከት በቂ የሆነ የኦሮምኛ ቋንቋን የሚያውቁና በቋንቋው የሚያገለግሉ ኤጲስቆጶሳት በቀጣይ የግንቦት (ርክበ ካህናት ተወስኖ እንዲሾሙ)፤

5. ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ብጹዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ እና ብጹዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ወደ ቀደመ ሀገረ ስብከትና የክህነት ማዕረጋቸው እንዲመለሱ፤

6. በሦስቱ አባቶች የተሾሙት አባቶች ቀድሞ ወደነበሩት የክህነት ማዕረግ ይመለሳሉ። ከእነርሱ ውስጥ በቤተ ክስቲያን ሕግና ሥርዓት የሚያሟሉት እንደገና በቅዱስ ሲኖዶስ እንዲሾሙ ይደረጋል።

7. በአስተዳደራዊ ጉዳዮች፣ በፋይናንስ፣ በምደባ፤ በቅጥር የሚታዩ ክፍተቶችን በጥናት የወንጌል አገልግሎትን በሚያጠናክር መልክ እናሻሽላለን።

8. የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት የበለጠ ለማጠናከርና ለትውልድ አርአያ የሚሆን ቤተ ክህነት እንዲኖረን ለማድረግ አሠራራችንን በጥናት አሻሽለን ቤተ ክርስቲያንን ለትውልድ እናሻግራለን።

9. ጥላቻን የሚያባበሱ ጉዳዮችን ከማድረግ መቆጠብ ይገባል። ሚዲያዎች፣ አክቲቪስቶች፣ መምህራን እና አባቶች ፍቅርን ከሚያጠፋ፣ ጥላቻን ከሚያበዛና መለያየትን ከሚያሰፋ ነገር ሁሉ እንዲቆጠቡ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። ይሄንን ተግባር ሆን ብለው የሚያደርጉትንም እናወግዛለን።

10. የገጠመን ፈተና ይበልጥ ውስጣችንን ለመፈተሽ፣ አንድነታችንን ለማጠናከር፤ ወንጌልን የበለጠ ለመስበክና የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለማስፋፋት ለበጎ እንጠቀምበታለን።

በመጨረሻም ፍቅር፣ ይቅርታ እና አንድነት እንዲመጣ የደከማችሁትን ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ስም እናመሰግናለን። ዋጋችሁንም እግዚአብሔር እንዲከፍላችሁ እንጸልያለን።

በስምምነቱ ወቅት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ “ጠንካራ ቤተክርስቲያን፣ ሌላ ሺህ ዘመን ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት … ብለን ተስማምተን የጋራ መግለጫ አውጥተን ይህ ሁሉ ድግስ አባታችን ጋር ሳይደርስ እንዴት ይቀራል ብለን ነው የመጣነው፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ብዙ ጥበበኛ፣ ሰፊ ልብ ያላቸው፣ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች እንዳሉ አይቻለሁ፤ … በውጪ እንደሚባለው አይደለም፤ ብዙ ልባቸው የሰፋ እግዚአብሔርን የሚፈሩ፣ ጥሩ ልብ ያላቸው፣ ለአገራቸው ለቤተክርስቲያናቸው የሚቀኑ አባቶች እንዳሉ ለማወቅ ችያለሁ፤ ይህ መታደል ነው፤ ሁሉ አገር ይህ ዓይነት ዕድል የላቸውም፤ … የዛሬው ተሳክቷል፤ የቀረው ደግሞ ወደ ትግራይ ሄደን የቀሩትን ማምጣት ነው” ብለዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Religion Tagged With: abiy ahmed, Abune Mathias, Abune Sawiros, Ethiopian Orthodox Church, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    February 16, 2023 11:26 am at 11:26 am

    የመግባቢያ ነጥቦቹ እንደ አስርተ ቃላቱ አሥር መሆናቸው ታስቦበት ይሁን አጋጣሚ ባይገባኝም በየሰበቡ ከመገዳደል ስምምነቱ እስካዳነ ድረስ መልካም ነው ብሎ ማለፉ ይሻላል እና አልፈዋለሁ፡፡ የሃገራችን የፓለቲካ ችግር ጅምሩ ላይ አይደለም፡፡ ሁሌ አንድን ገፍትረው ስልጣን ላይ ቁጢጥ ሲሉ ቃላቸው ማር ነው፡፡ መነገጃቸው ህዝብ፤ የሃገር አንድነትና ሃይማኖት ናቸው፡፡ ጭንቁ የሚመጣው መሃሉ ላይ ነው፡፡ ያለምንም ደም እንከንዋ ይውደም ተብሎ ነበር አይደል፡፡ መቸም አታድርስ ነው፡፡ አይጣል ይላሉ የሃገሬ ሰዎች በሰው ላይ ከበድ ያለ ነገር ሲደርስ ለራሳቸውም እድል ፈንታ አዝነው ፈጣሪዬ የምችለው ስጠኝ በማለት ሰማይ ሰማይ እያዪ ይማጠናሉ፡፡ በኢትዮጵያ ፓለቲካ እጃቸውን ያስገቡ ሁሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የምችለው ስጠኝ ማለታቸው አይቀሬ ነው፡፡ ለዚያውም ከእሳቱ ከተረፉ!
    በሃገራችን ውስጥ ለነበረውና አሁንም ላለው ቆሻሻ ፓለቲካ መንግስታት ብቻ ሳይሆኑ ህዝቡ ራሱ ተጠያቂ ነው፡፡ የሚናገረው ሌላ ተግባሩ ሌላ፡፡ እግዚኦ ሲል ውሎ የሰው ቤት ዘረፋ ላይ የሚሰማራ፤ ምንም መጠለያ የሌላቸውን የሚያጠቃ፤ በዘሩና በቋንቋው ተሰልፎ ሰውን እየመረጠ አንገት የሚቀመጥል የእብድ ስብስብ የሞላበት ሃገር ነው፡፡ ለዚህም ይሆናል በቅርቡ የወጣ አንድ ጥናት በሃበሻዋ ምድር የእብዶችን ቁጥር እትዬ ለሌ ላይ የሰቀለው፡፡
    ሰው በሰውነቱ ተመዝኖ፤ በሃገሪቱ ክፍል በፈለገበት ተዘዋውሮ የመኖር፤ የመስራት፤ የመማር መብቱ እስካልተጠበቀ ድረስ ኢትዮጵያ ማለት በክልል አፓርታይድ የተቆለፈች በቋንቋቸው የሰከሩ የሚያንገላቷት ምድር ናት፡፡ ቋንቋ መግባቢያ ነው፡፡ በአለም የታሪክ መዝገብ ላይ እንደ እንግሊዝ መንግስት ያለ በሰው ልጆች ላይ ጭካኔን ያደረሰ መንግስት የለም፡፡ ይሁን እንጂ ዛሬ ቋንቋቸው በአለም ላይ ከሚሰራባቸው ቋንቋዎች ቀዳሚውን ሥፍራ ይዞአል፡፡ በሃበሻ ምድር ዝም ብሎ በሆነ ባልሆነው ነገር መቦጫረቅ ሰውን ለመከራ ከመዳረጉ ሌላ የሚያመጣው አንድም ፍትሃዊ ነገር የለም፡፡ ባጭሩ በአማርኛ ተሰበከ፤ በኦሮምኛ ተቀደሰ ዋናው አምልኮው ላይ ነው፡፡ ችግሩ ይህን የቋንቋ ፓለቲካ ወደ ትጥቅ ትግል እያስገቡ ሊያፋልሙን የሚሹት የያኔና የአሁን ጠላቶቻችን አርፈው አይተኙምና ያው ሞኞችን እያስታጠቁ ለወገንህ ነው በማለት ያጫርሱናል፡፡ መቼ ነው የምንነቃው የሰው ተላላኪ ከመሆን? እየዘረፉና እያሽበሩ መኖር እውን የብሄር ጥያቄ ትግል ነው? ጭራሽ! ታሪክ የሚያሳየን የበረሃ አሸባሪዎች የከተማ አለቆች ሲሆኑም የከፋ አረመኔዎች እንደሆኑ ነውና!
    ዛሬ በዪክሬንና በራሺያ ባለው ግጭት የተነሳ አሜሪካንና የአውሮፓ ህብረትን ወደ ጎን በማድረግ ወደ ራሺያ የሚጠጉ ሃገሮች ቁጥር ከፍ በማለት ላይ ይገኛል፡፡ የሚበልጡትም በአፍሪቃ አህጉር ያሉ ሃገሮች አፍቃሪ ራሺያ እየሆኑ ነው፡፡ ይህ የጅል እሳቤ ነው፡፡ ነጩ ኣለም ተፋልሞ ወደ ስምምነት ሲመጣ ጥቁሩን ኣለም ዞር ብሎ አያይም፡፡ አሁን በሱዳን፤ በኤርትራና በሌሎች ሃገሮች እየተዘዋወረ ዲስኩር የሚያሰማው የራሺያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጨነቀው እርጉዝ ያገባል እንዲሉ እንጂ ፍሬ የለሽ ዲስኩር ነው፡፡ አፍሪቃ የጦር መሳሪያ አያስፈልጋትም፡፡ የሚያስፈልጋት ሰላም፤ የእርሻና የቴክኖሎጂ ግኝቶች እንጂ፡፡ ያው እንደለመድት ሁለቱ ዝሆኖች ሲፋለሙ እኛው በመሃል እንጨፈለቃለን፡፡ ፓለቲካ የወስላቶች ገቢያ ነው፡፡ ኢትዮጵያንና ሱማሊያን ሲያላትሙ ራሺያና አሜሪካ ስፍራ እየተለዋወጡ ነበር፡፡ ልብ ያለው ያስተውል፡፡
    ታዲያ ይህ ሁሉ ዲስኩር ከሃይማኖት አባቶች መታረቅ ጋር ምን አገናኘው ይል ይሆናል አንባቢ፡፡ እኮ ሰከን በል፡፡ በደንብ ነው የሚገናኘው፡፡ በምድረ አፍሪቃ እሳት የሚቀጣጠለው በውጭ ሃይሎች አነሳሽነት፤ በሃገር በቀል ጅሎች ነው፡፡ ኢትዮጵያን ለመናድ ብዙ ድንጋይ ፈንቅለው ጊንጥ እየነደፋቸው አሁን ላይ ብለው ብለው በሃይማኖት ሳቢያ ሰው እንዲጫረስ ከህዋላ ሆነው እሳቱን የሚያነድት የውጭ ሃይሎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤ/ክ ማናወጥ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ይመቻቸዋልና፡፡ ለሃገር ቤት ፍጆታ አማራው እንዲህ ብሎ ኦሮሞው ያን አርጎ በማለት ወሬውን እናናፍሳለን፡፡ ጥልቅ ሚስጢሩ ግን ሌላ ነው፡፡ መመርመር፤ መጠንቀቅ፤ ማሰብ ይጠይቃል፡፡ ዛሬ Deepfake and Artificial Intelligence በአንድ ላይ ተጣምረው የፈጠራው ወሬ በቪዲዪና በሌላ መልኩ በማንሸራሸር ሰውን ያማታሉ፡፡ ዛሬ ዜና የሚባለው በየቀኑ የሚነገረን ሳይሆን ሳይነገር የቀረው ነው፡፡ ልብ ያለው ያስተውላል፡፡ ጀሮ ያለው ይሰማል፤ ይመዝናል፤ አይን ያለው አይቶ ይፈርዳል፡፡ ዛሬ ሃገራችን የሚያስፈልጋት ሰላምና መረጋጋት እንጂ በየጎጡ ጠበንጃ ይዞ እንዘጥ እንዘጥ የሚል በዘርና በቋንቋ የሰከረ ፓለቲከኛ አይደለም፡፡ በቅርቡ ታደሰ ወረደ በትግራይ ጉዳይ ላይ ገለጣ ሲሰጥ የሃዘን ልብስ ለብሳ የተቀመጠችውን አንዲት ወገናችን ሳይ ማን ሙቶባት ይሆን? በምንስ ሞተ በማለት የእሷን መከራ ሳሰላስል ታደሰ ወረደ በአማርኛና በትግርኛ የሰጠውን መግለጫ ልቤ ሳላስገባው ጉዳዪ አለቀ፡፡ መቼ ነው ሰው በሃዘንና በመከራ ጥቁር መልበስ የሚያቆመው? ያ ቀን ይመጣ ይሆን? አላውቅም፡፡ ለዛሬው የሰላሙ ስምምነት ወሸኔ ነው፡፡ ዘላቂነት ይኑረው፡፡ በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule