• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ

August 13, 2025 12:58 am by Editor 2 Comments

ሰሞኑን ሞዐ ተዋሕዶ አየሩን ሞልቶታል። በተለይ በቅርቡ ከሞዐ ተዋሕዶ አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ፋንታኹን ዋቄ የሰጡት ቃለ ምልልስ ወደኋላ ሄደን ብዙ ነገሮችን እንድንዳስስ የሚያስደርግ ሆኗል። የዛሬ ሦስት ዓመት በቀነኒሳ ሆቴል ዶ/ር ወንደሰን በሚመራው ስብሰባ መግለጫ በሰጡበት ወቅት የተናገሩትና ሰሞኑን የተሰማውን ጉዳይ ባጭሩ ለማስቀመጥ እንሞክራለን። ይህንን በማድረግም የሞዐ ተዋሕዶን ሁኔታ ለየት ባለ ሁኔታ ለማየት እንሞክራለን፤ እንደተባለው ሞዐ ሃሳብ የሚያመጣና ወደ ሕዝቡ የሚያሰርጽ ንቅናቄ ነው? ወይስ ሌላ ተልዕኮ አለው? የሚለውን በንጽጽር እናያለን።

የዛሬ ሦስት ዓመት አካባቢ በቀነኒሳ ሆቴል ከተካሄደው የሞዐ ተዋሕዶ ስብሰባ በኋላ የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ከሶስት የሞዐ ተዋሕዶ አመራሮች ጋር ውይይት አድርጎ ነበር። በውይይቱ የተገኙት መምህር ገብረመድኅን እንየው፣ መምህር ያረጋል አበጋዝና መምህር ፋንታኹን ዋቄ ሲሆኑ ከተነሱላቸው ጥያቄዎች ጥቂቱን ብቻ በመውሰድ የሰጡትን ምላሻቸውን እናያለን።

ከቀረቡላቸው ጥያቄዎች አንዱ የውክልና ጉዳይ ነበር። እናንተን ማን ወክሏችሁ ነው ይህንን ጉዳይ በኦርቶዶክስ ምዕመናን እና በቤተ ክርስቲያኗ ስም የምታራምዱት የሚል ነበር። ይህ ጥያቄ ትንሽ ያበሳጫቸው እንደነበር ከምላሻቸው መረዳት ቻላል። ለጥያቄው የሰጡት ምላሽ፤ በቅድሚያ ሲኖዶሱ በተደጋጋሚ ጥሪ ሲያደርግ እንደነበርና የእርሱ አካሄድ ለዚያ ምላሽ እንደሆነ፤ ከዚያም በዋነኛነት ያስረዱት ጉዳቱና ችግሩ የሚታይና ማስረጃም ሆነ ውክልና የሚያስፈልገው እንዳልሆነ ነው። እንዲያውም የውክልና ጥያቄ ሤራዊና በውስጡ ትክክለኛ እሳቤ የሌለው የተንኮልና ውዳቂ ሃሳብ እንደሆነ በእንደምታ አመልክተዋል።

የሞዐ ሰዎች የውክልናን ጥያቄ ሲመልሱ ባለመናገር ያሳወቁት ነገር ማንም ምዕመን ተሰብስቦ ወይም ከየትኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ መምሪያ በጉዳዩ ላይ እንዲሠሩበት ተጠይቀው ሳይሆን የኦርቶዶክስን ችግር እናውቅላታለን፤ ለችግሯ መፍትሔ እንፈልግላታለን ከሚል ነው። በሌላ አነጋገር በአውቅልሃለሁ ባይነት ነው የተነሱት እንጂ ውክልና ኖሯቸው አይደለም።

በመሠረቱ ይህ ስህተት አይደለም። ነገር ግን የሞዐ ሰዎች በነጻ አውጪ ግምባር የተደራጁትን ቡድኖች (ኦነግ፣ ትህነግ፣ ኦብነግ፣ …) በጣም ያወግዛሉ፤ ይነቅፋሉ። ከዚህ አኳያ የውክልናው ጥያቄ እነርሱንም ልክ እንደ ነጻ አውጪ ግምባሮች ያለ ሕዝብ ውክልና በእናውቅልሃለን ባይነት የተነሱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ነው። ነጻ አውጪ ግምባሮች “ነጻ አወጣዋለሁ” በሚሉት ሕዝብ ስም የሚደራጁት በብዙ መልኩ አዋጪ ስለሆነ ነው እንጂ፤ ሕዝቡ ተሰብስቦ ነጻ የሚያወጣን ቡድን ያስፈልጋል ብሎ ስላቋቋማቸው አይደለም፤ ሞዐም እንዲሁ ነው።

ስለዚህ ሞዐ ተዋሕዶ አመሠራረቱ እንደ አብዛኛው ነጻ አውጪ ግምባር በአውቅልሃለሁ፤ ችግርህን እረዳልሃለሁ፤ ወዘተ በሚል ነው። ከላይ እንዳልነው ይህ ስህተት ላይሆን ይችላል፤ ነገር ግን በተመሳሳይ ሁኔታ በነጻ አውጪ ስም የተቋቋሙትን ጎጠኛ፣ ጭፍንና ሀገር አጥፊ ቡድኖችን ለመውቀስ የሞራል ልዕልና አይሰጥም። እነርሱም በሕዝብ ስም ለጥቅምና ለዓላማ ነው የተዋቀሩት፤ ሞዐም እንዲሁ በብዙኃኑ የኦርቶዶክስ አማኝ ስም ለራሱ ዓላማ የተዋቀረ ነው።

የሞዐ ሰዎች በተደጋጋሚ የሚያነሱት ነገር ፍትሕ፣ ርትዕ፣ እውነት፣ ሐቅ ወዘተ የተሰኙ ኦርቶዶክሳዊ እሴቶች የሚሏቸውን ነው። ትክክል ነው ኦርቶዶክስ የእነዚህና የሌሎች እጅግ የላቁ እሴቶች ባለቤት ነች፤ ሕዝብንም በዚህ መሥመር አንጻለች፤ አብቅታለች። ተጽዕኖዋም የሚታይ እና ዘመናትን የዘለቀ፤ ድንበር የተሻገረ ነው።

በቀነኒሳ ሆቴል በተደረገው ስብሰባም ሆነ በቀጣይ በተደረጉ ቃለ ምልልሶችም ሆነ ውይይቶች የሞዐ ሰዎች ስለ እውነት አጥብቀው ይናገራሉ፤ ራሳቸውንም የእውነት ጠበቃ አድርገው ያቀርባሉ። ይህንን እነርሱ “አምላካዊ እውነት” ያሉትን ይዘው ደግሞ አሸናፊ እንደሚሆኑ በተደጋጋሚ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ነገር ግን ሰሞኑን አቶ ፋንታኹን ዋቄ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ ፋኖን ያደራጁት ብቻ ሳይሆን፣ አሁንም ፋኖ እየተመራ ያለው በሞዐ ተሐድሶ አስተሳሰብና እሴት እንደሆነ ገልጸዋል። እንዲያውም አሳምነው ጽጌ ስለ ሞዐ አደረጃጀትና ሃሳብ ሰምተው የሞዐ አደራጆችን ሲያነጋግሯቸው ሃሳቡን እርሳቸው (አሳምነው) የተቀበሉት ብቻ ሳይሆን የኔም ሃሳብ ነው፤ በሉ እኔና እናንተ አልተነጋገርንም ብለው ሁለቱም በየፊናቸው እንዲሠሩ ተስማምተው መለያየታቸውን አቶ ፋንታኹን ተናግረዋል።

ይህ አሁን የተሰማ የሞዐ ተዋሕዶ ዓላማና ሃሳብ ነውንጂ ቀነኒሳ ሆቴል ሲመሠረት በትጥቅ ትግል መንግሥትን ለመገልበጥ ነው ዋናው ሃሳባችን የሚል ነገር አልተነገረም። በቀጣይ በተሰጡ መግለጫዎችም የትኛውም የሞዐ ሃሳብ አራማጅ ይህንን በግልጽ ተናግሮ አያውቅም። ይኼ ታዲያ ውሸት አይደለም? ለቅዱስ ዓላማ ነው የተነሳነው፤ የያዝነው መሣሪያ እውነት ነው፤ አምላካዊ ነው፤ ሲል ከነበረ ቡድንና አመራር በዚህ ልክ መዋሸትና መሠሪ መሆን ግብዝነት አይደለም? የሞራል ልዕልናውስ የት ላይ ነው? ለሌላውስ ተከታይ (ምዕመን) ምን ዓይነት አርአያነት ነው?

በአውቅልሃለሁ ባይነት ተጀምሮ የሕዝብን ስሜት በስሑት ዓላማ የቀሰቀሰ፤ ድብቅ ሤራ የሚጠነስስ፤ ፍጹም እውነት ላይ ነው የተመሠረትነው በሚል ሰላማዊ እንቅስቃሴ የሚያደርግ መስሎ ሃሳብ ከፊቱ ብረት ከኋላው ያደረገ፤ ሥልጣን ለመቆጣጠር ሲል መጣሁልህ ያለውን ሕዝብ የሚያሰቃይ ቡድን፤ ምኑ ነው ሰላማዊ እንቅስቃሴ የሚባለው? ይልቅ በግልጹ ሞዐ ተዋሕዶ ነጻ አውጪ ግምባር (ሞነግ) ቢባል ለደጋፊም ለተቃዋሚው ብዙ ነገር ያቀልል ነበር።

ሞዐውያን የልዕለ እሴት ባለቤት ነን ይላሉ፤ በንግግራቸውም ይህንኑ አሳምረውና አጣፍጠው ይናገራሉ። ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ለምዕመኗ ነው የቆምነው ይላሉ። ነገር ግን የትግራይን ጉዳይ አያነሱም። ቤተ ክርስቲያን የተዋረደችውና ቀኖናዋ የተረገጠው በኦሮሞ ጳጳሳት መሪነት የጫካ ሲኖዶስ ሲመሠረት ብቻ ሳይሆን በትግራይም መንበረ ሰላማ ሲመሠረት ነው።

የትግራዩ እንዲያውም እጅግ የከፋ ነው። የመንበረ ሰላማን አካሄድ ሲኖዶሱ በግልጽ አውግዟል፤ አካሄዱንም ኮንኗል። መንበረ ሰላማም የሲኖዶሱን ውሳኔ ንቆና አልቀበልም ብሎ በራሱ መንገድ ሄዷል። ከላይ እንደገለጽነው ለሞዐ የውክልና ጥያቄ ሲቀርብለት የሰጠው አንዱ መከራከሪያ ነጥብ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለውን ነገር በተመለከተ ሲኖዶሱ ጥሪ አቅርቧል፤ እኛም ለዚያ ምላሽ ለመስጠት ነው ሞዐን ያቋቋምነው ብለዋል። ታዲያ ሲኖዶሱ የመንበረ ሰላማን አካሄድ አውግዞ ላወጣው መግለጫ ሞዐ ድጋፍ መስጠትና ለዚህ ሀገርን ለሚከፋፍል ቡድን ምላሽ ለመስጠት አሁን ባለው ቁመና ልክ ለምን አልተደራጀም? ቤተ ክርስቲያን ተዋረደች፤ “መንፈስ ቅዱስ የሚመራው ሲኖዶስ ውሳኔ ተናቀ” ብሎ ሞዐ ለምን ምዕመናንን አላስተባበረም?

እንደ ጫካው ሲኖዶስ የትግራይ መንበረ ሰላማም ለቤተ ክርስቲያን ኅልውና በጣም አስጊ ነው፤ ለሞዐ ግን አይደለም። ይህ የአገሪቱን ፓትሪያርክ ወደ ትግራይ ሲሄዱ ተቀብዬ አላነጋግርም፤ አላስገባም ያለ ቡድን እያስከተለ ያለው ጉዳት ለሞዐ የአጀንዳው አካል አይደለም፤ የቤተ ክርስቲያን ስደት መገለጫ አይደለም። ሲሆንማ ቤተ ክርስቲያን ማቅ መልበስ፣ ማልቀስ፣ እግዚኦ ማለት ያለባትና ኅልውናዋ የተደፈረው አሁን ነበር።

ሃቁ ይህ ሆኖ ሳለ የሞዐ ተዋሕዶ ጥላቻ እና አግላይና ጸረ መንግሥት ዓቋም ከየት መጣ የሚለው ጥያቄ እውነተኛ ምላሽ ስለሚያስፈልገው የምንመለስበት አጀንዳ ይሆናል።

ሞዐውያን በየሚዲያው እንደሚናገሩት ወይም ቀነኒሳ ሆቴል እንደሰጡት መግለጫና ማብራሪያ በላቀ የሞራል ልዕልና ውስጥ ያሉ፤ ኢትዮጵያን ለመታደግ የተነሱ ሰላማዊ ታጋዮች ሳይሆኑ በሃይማኖት ሰበብ ሁሉን የመቆጣጠር ምኞት ያላቸው፤ ተከታዮቻቸውን ከሃይማኖት ጋር በተቀላቀለ ጭፍን ፕሮፖጋንዳ የሚመሩ፤ በፊት ለፊት ሰላማዊ እንዲያውም መንፈሣዊ ታጋይ ነን እያሉ በስውር ግን የታጠቀ፣ ጨካኝ፣ አራጅ፣ ነውረኛ ቡድንን በቁጥጥራቸው ሥር ያደረጉና የሚመሩ “ነጻ አውጪ ግምባር” ናቸው። ስለዚህ “ሞዐ ተዋሕዶ ነጻ አውጪ ግምባር – ሞነግ” የሚለው በትክክል የሚገልጻቸው መጠሪያ ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics, Religion Tagged With: Fano, Moa Tewahido, State and religion, ሞነግ, ሞዐ ተዋሕዶ

Reader Interactions

Comments

  1. ተርፋሳ says

    August 30, 2025 03:52 pm at 3:52 pm

    የተሻለ ፕሮፓጋንዳ ነሥራት ብትችሉ ጥሩ ነው። ይህ ሕጻን እንኳ የማያሳስት ተራ የኩሽት ድምጽ ነው።

    Reply
  2. motuma says

    March 12, 2026 11:08 pm at 11:08 pm

    Maaloo baayee baqeqtani. Salfechu hinjiru?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule