• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው

April 24, 2025 12:43 am by Editor Leave a Comment

የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤል ”የሰባ ገብዣ” በሚል ርዕስ ስቅለት ዕለት ያቀረቡትን መልዕክት በተመለከተ እጅግ በርካታ ውግዘትና ፍረጃ ሲሰጥ እየተሰማ ነው። የሊቀ ጳጳሱን ስብዕና እና ማንነት ከማዋረድ ጀምሮ የሚሰጡት ስድብ አዘል “አስተያየቶች” ኢ-መንፈሳዊ፣ ጽንፈኛና አምባገነናዊ ናቸው።   

ገና ከጅምሩ በማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪና ብዙ ተከታይ አለን የሚሉ በሚሰጡ አስተያየት ሊቀ ጳጳሱን ከመዝለፍና ከማዋረድ አልፈው ግለሰባዊ ማንነታቸውን በማጉላት ሲሳደቡ ተሰምተዋል። እነዚህ “መምህራን” ብለው ራሳቸውን የሰየሙ ወይም ጥቂት ጊዜያት በቤተ ክርስቲያኗ የትምህርት ደጃፍ በማለፋቸው ብቻ “መምህር” ተብለው የሚጠሩ፤ በአቡኑ ላይ ለርካሽ የፖለቲካ መጠቀሚያ የሚውልና ከወንጌል አስተምህሮ የለቀቀ እጅግ ጸያፍ ንግግሮች በማሰማት ከሊቃውንቱ ጉባዔና ሲኖዶሱ ውሳኔ በፊት የአደባባይ ፍረጃ እየበየኑባቸው ነው፤ የሲኖዶሱን እጅ እየጠመዘዙም ነው።

ድርጊቱ በዕቅድና በዘመቻ መልክ የሚካሄድ እንደሆነ አንዱ ማሳያ፤ ቪዲዮውን ያወጣው ፍኖተ ጽድቅ የተባለው ሚዲያ በዩትዩብ ቻናሉ ሲሆን ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ቀን ድረስ ቪዲዮው ከወጣ አራት ቀናት አልፈዋል። በእነዚህ አራት ቀናት ቪዲዮውን የተመለከተው ሰው ቁጥር 22ሺህ ብቻ ሲሆን አስተያየት ሰጪውና ነቃፊው ግን “22 ሚሊዮን” መድረሱ ዘመቻው ከዕውቀት የጸዳና ሌላ ስሁት ዓላማ ያለው መሆኑ አመላካች ነው።

አቡነ ገብርኤል ያደረጉት ፖለቲካዊ ወይም ተራ ንግግር ሳይሆን ሃይማኖታዊ መልዕክት ያለው ነው፤ የመልዕክታቸው ይዘት ደግሞ ነገረ መለኮታዊ ወይም ቲዎሎጂካል ነው። እርሳቸው የተናገሩትን ከቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ አንጻር ስህተት ነው ወይም አይደለም የማለት ሥልጣን ያለው ቤተ ክርስቲያኗ ሥርዓቱን ጠብቃ ያዋቀረችው የሊቃውንት ጉባዔ ነው እንጂ የቲክቶክ ነጋድራሶች፣ የቴሌግራም ፊት አውራሪዎችና የዩትዩብ ተጧሪዎች መሆን የለባቸውም።

የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በዚህ ዓመት የካቲት ወር ባወጣው መረጃ ይህንን ብሎ ነበር፤ “የሊቃውንት ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ኀላፊነት መሠረት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት፣ ሥርዐተ አምልኮ፣ ታሪክና ትውፊት፣ ልሳነ መጻሕፍትና የዕውቀት ሀብታት፣ ጥበባተ አበውና ባህለ ሃይማኖትን መጠበቅና ማስጠበቅ፣ ማስፋፋትና በአግባቡ እንዲተረጐሙ ማድረግ፣ ዐቂበ እምነትን ማጠናከር፣ በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ልዕልና፣ ህልውና፣ የትምህርቷን ጥራትና ርትዐት መጠበቅ ዋንኛ የሥራ ድርሻው ነው።

“በቀድሞ ዘመን መናፍቅና ከሓዲ ሲነሣ፣ ሃይማኖትና ሥርዐት ሲጣስ፣ ዐላውያን የሐሰት ትምህርትን በዐውደ ጉባኤ ሲያሠራጩ፡ ሊቃውንት ከየአሉበት ተሰብስበው ዘርዐ ኑፋቄን አርመው፣ ኀይለ ክሕደትን አድክመው ርትዕት ሃይማኖትን አቆይተዋል። በእኛም ዘመን በርካታ ውይይትና ምክክር የሚያስፈልጋቸው ዐበይት ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ጥያቄዎች በመኖራቸው፤ ያለፈውን ለማጽናት፣ የሚመጣውን ለማቅናት የሊቃውንት መሰባሰብ እጅግ ተገቢ ሆኖ ይገኛል።”

ቤተ ክርስቲያኗ ይህንን የመሰለ በርካታ ዘመናትን የተሻገረ፣ እጅግ የዳበረ አሠራር እያላት ክብሯ በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚገኝ ፍርፋሪና “ዕውቅና (ላይክ)” ቀን ተሌት “በሚለፉ” መጻጉ የዕውቀት ድኩማን መዳፍ ሥር መውደቁ አብሮ ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው።    

አቡነ ገብርኤል ያቀረቡት መልዕክትን በተመለከተ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጎ ለረቡዕ” ቀጥሮት የነበረውን “የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት የሚገኙበትን” ውይይት ወደ አርብ አስተላልፎታል።

በተለመደው አሠራርና በበርካታዎች ዘንድ እንደሚጠበቀው በዚህ ዕለት ሲኖዶሱ ይህንን ስነ መለኮታዊ ጉዳይ በሊቃውንት ጉባዔ እንዲታይ ያደርጋል። ቀጥሎም የሊቃውንቱ ጉባዔ የሚሰጠውን አስተያየት ተመርኩዞም በአቡነ ገብርኤል ላይ ሲኖዶሱ ውሳኔ ያስተላልፋል። እስከዚያ ግን ዝምታ ወርቅ ነው።  

“ወኵሎ አመክሩ፣ ወዘሠናይ አጽንዑ።” “ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ” የሚለውን የቅዱሱን መጽሐፍ መመሪያ መከተል እየተቻለ (1ኛ ተሰሎንቄ 5:21) አስተዳደራዊውንም ሆነ አስተምህሮ ላይ ያነጣጠረውን ጉዳይ ሁሉ በግድ ለጥጦ ፖለቲካዊ ማድረግ፤ በተለይ ደግሞ ከርካሽ የዘር ፖለቲካ ጋር በማያያዝ በግድ እሳት ለማቀጣጠል መሞከር ወይ በሚያምኑት አስተምህሮ ላይ የዕውቀት እጥረት እንዳለ የሚያሳይ ነው ወይም አርነት የሚያወጣውን እውነት ማዳፈን ነው። ሁለቱም ያስኮንናል እንጂ አያጸድቅም።


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Religion Tagged With: Abune Gabriel, EOTC, ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤል, የሰባ ገብዣ

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule