• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው

April 24, 2025 12:43 am by Editor Leave a Comment

የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤል ”የሰባ ገብዣ” በሚል ርዕስ ስቅለት ዕለት ያቀረቡትን መልዕክት በተመለከተ እጅግ በርካታ ውግዘትና ፍረጃ ሲሰጥ እየተሰማ ነው። የሊቀ ጳጳሱን ስብዕና እና ማንነት ከማዋረድ ጀምሮ የሚሰጡት ስድብ አዘል “አስተያየቶች” ኢ-መንፈሳዊ፣ ጽንፈኛና አምባገነናዊ ናቸው።   

ገና ከጅምሩ በማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪና ብዙ ተከታይ አለን የሚሉ በሚሰጡ አስተያየት ሊቀ ጳጳሱን ከመዝለፍና ከማዋረድ አልፈው ግለሰባዊ ማንነታቸውን በማጉላት ሲሳደቡ ተሰምተዋል። እነዚህ “መምህራን” ብለው ራሳቸውን የሰየሙ ወይም ጥቂት ጊዜያት በቤተ ክርስቲያኗ የትምህርት ደጃፍ በማለፋቸው ብቻ “መምህር” ተብለው የሚጠሩ፤ በአቡኑ ላይ ለርካሽ የፖለቲካ መጠቀሚያ የሚውልና ከወንጌል አስተምህሮ የለቀቀ እጅግ ጸያፍ ንግግሮች በማሰማት ከሊቃውንቱ ጉባዔና ሲኖዶሱ ውሳኔ በፊት የአደባባይ ፍረጃ እየበየኑባቸው ነው፤ የሲኖዶሱን እጅ እየጠመዘዙም ነው።

ድርጊቱ በዕቅድና በዘመቻ መልክ የሚካሄድ እንደሆነ አንዱ ማሳያ፤ ቪዲዮውን ያወጣው ፍኖተ ጽድቅ የተባለው ሚዲያ በዩትዩብ ቻናሉ ሲሆን ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ቀን ድረስ ቪዲዮው ከወጣ አራት ቀናት አልፈዋል። በእነዚህ አራት ቀናት ቪዲዮውን የተመለከተው ሰው ቁጥር 22ሺህ ብቻ ሲሆን አስተያየት ሰጪውና ነቃፊው ግን “22 ሚሊዮን” መድረሱ ዘመቻው ከዕውቀት የጸዳና ሌላ ስሁት ዓላማ ያለው መሆኑ አመላካች ነው።

አቡነ ገብርኤል ያደረጉት ፖለቲካዊ ወይም ተራ ንግግር ሳይሆን ሃይማኖታዊ መልዕክት ያለው ነው፤ የመልዕክታቸው ይዘት ደግሞ ነገረ መለኮታዊ ወይም ቲዎሎጂካል ነው። እርሳቸው የተናገሩትን ከቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ አንጻር ስህተት ነው ወይም አይደለም የማለት ሥልጣን ያለው ቤተ ክርስቲያኗ ሥርዓቱን ጠብቃ ያዋቀረችው የሊቃውንት ጉባዔ ነው እንጂ የቲክቶክ ነጋድራሶች፣ የቴሌግራም ፊት አውራሪዎችና የዩትዩብ ተጧሪዎች መሆን የለባቸውም።

የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በዚህ ዓመት የካቲት ወር ባወጣው መረጃ ይህንን ብሎ ነበር፤ “የሊቃውንት ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ኀላፊነት መሠረት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት፣ ሥርዐተ አምልኮ፣ ታሪክና ትውፊት፣ ልሳነ መጻሕፍትና የዕውቀት ሀብታት፣ ጥበባተ አበውና ባህለ ሃይማኖትን መጠበቅና ማስጠበቅ፣ ማስፋፋትና በአግባቡ እንዲተረጐሙ ማድረግ፣ ዐቂበ እምነትን ማጠናከር፣ በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ልዕልና፣ ህልውና፣ የትምህርቷን ጥራትና ርትዐት መጠበቅ ዋንኛ የሥራ ድርሻው ነው።

“በቀድሞ ዘመን መናፍቅና ከሓዲ ሲነሣ፣ ሃይማኖትና ሥርዐት ሲጣስ፣ ዐላውያን የሐሰት ትምህርትን በዐውደ ጉባኤ ሲያሠራጩ፡ ሊቃውንት ከየአሉበት ተሰብስበው ዘርዐ ኑፋቄን አርመው፣ ኀይለ ክሕደትን አድክመው ርትዕት ሃይማኖትን አቆይተዋል። በእኛም ዘመን በርካታ ውይይትና ምክክር የሚያስፈልጋቸው ዐበይት ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ጥያቄዎች በመኖራቸው፤ ያለፈውን ለማጽናት፣ የሚመጣውን ለማቅናት የሊቃውንት መሰባሰብ እጅግ ተገቢ ሆኖ ይገኛል።”

ቤተ ክርስቲያኗ ይህንን የመሰለ በርካታ ዘመናትን የተሻገረ፣ እጅግ የዳበረ አሠራር እያላት ክብሯ በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚገኝ ፍርፋሪና “ዕውቅና (ላይክ)” ቀን ተሌት “በሚለፉ” መጻጉ የዕውቀት ድኩማን መዳፍ ሥር መውደቁ አብሮ ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው።    

አቡነ ገብርኤል ያቀረቡት መልዕክትን በተመለከተ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጎ ለረቡዕ” ቀጥሮት የነበረውን “የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት የሚገኙበትን” ውይይት ወደ አርብ አስተላልፎታል።

በተለመደው አሠራርና በበርካታዎች ዘንድ እንደሚጠበቀው በዚህ ዕለት ሲኖዶሱ ይህንን ስነ መለኮታዊ ጉዳይ በሊቃውንት ጉባዔ እንዲታይ ያደርጋል። ቀጥሎም የሊቃውንቱ ጉባዔ የሚሰጠውን አስተያየት ተመርኩዞም በአቡነ ገብርኤል ላይ ሲኖዶሱ ውሳኔ ያስተላልፋል። እስከዚያ ግን ዝምታ ወርቅ ነው።  

“ወኵሎ አመክሩ፣ ወዘሠናይ አጽንዑ።” “ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ” የሚለውን የቅዱሱን መጽሐፍ መመሪያ መከተል እየተቻለ (1ኛ ተሰሎንቄ 5:21) አስተዳደራዊውንም ሆነ አስተምህሮ ላይ ያነጣጠረውን ጉዳይ ሁሉ በግድ ለጥጦ ፖለቲካዊ ማድረግ፤ በተለይ ደግሞ ከርካሽ የዘር ፖለቲካ ጋር በማያያዝ በግድ እሳት ለማቀጣጠል መሞከር ወይ በሚያምኑት አስተምህሮ ላይ የዕውቀት እጥረት እንዳለ የሚያሳይ ነው ወይም አርነት የሚያወጣውን እውነት ማዳፈን ነው። ሁለቱም ያስኮንናል እንጂ አያጸድቅም።


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Religion Tagged With: Abune Gabriel, EOTC, ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤል, የሰባ ገብዣ

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule