• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው

April 24, 2025 12:43 am by Editor Leave a Comment

የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤል ”የሰባ ገብዣ” በሚል ርዕስ ስቅለት ዕለት ያቀረቡትን መልዕክት በተመለከተ እጅግ በርካታ ውግዘትና ፍረጃ ሲሰጥ እየተሰማ ነው። የሊቀ ጳጳሱን ስብዕና እና ማንነት ከማዋረድ ጀምሮ የሚሰጡት ስድብ አዘል “አስተያየቶች” ኢ-መንፈሳዊ፣ ጽንፈኛና አምባገነናዊ ናቸው።   

ገና ከጅምሩ በማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪና ብዙ ተከታይ አለን የሚሉ በሚሰጡ አስተያየት ሊቀ ጳጳሱን ከመዝለፍና ከማዋረድ አልፈው ግለሰባዊ ማንነታቸውን በማጉላት ሲሳደቡ ተሰምተዋል። እነዚህ “መምህራን” ብለው ራሳቸውን የሰየሙ ወይም ጥቂት ጊዜያት በቤተ ክርስቲያኗ የትምህርት ደጃፍ በማለፋቸው ብቻ “መምህር” ተብለው የሚጠሩ፤ በአቡኑ ላይ ለርካሽ የፖለቲካ መጠቀሚያ የሚውልና ከወንጌል አስተምህሮ የለቀቀ እጅግ ጸያፍ ንግግሮች በማሰማት ከሊቃውንቱ ጉባዔና ሲኖዶሱ ውሳኔ በፊት የአደባባይ ፍረጃ እየበየኑባቸው ነው፤ የሲኖዶሱን እጅ እየጠመዘዙም ነው።

ድርጊቱ በዕቅድና በዘመቻ መልክ የሚካሄድ እንደሆነ አንዱ ማሳያ፤ ቪዲዮውን ያወጣው ፍኖተ ጽድቅ የተባለው ሚዲያ በዩትዩብ ቻናሉ ሲሆን ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ቀን ድረስ ቪዲዮው ከወጣ አራት ቀናት አልፈዋል። በእነዚህ አራት ቀናት ቪዲዮውን የተመለከተው ሰው ቁጥር 22ሺህ ብቻ ሲሆን አስተያየት ሰጪውና ነቃፊው ግን “22 ሚሊዮን” መድረሱ ዘመቻው ከዕውቀት የጸዳና ሌላ ስሁት ዓላማ ያለው መሆኑ አመላካች ነው።

አቡነ ገብርኤል ያደረጉት ፖለቲካዊ ወይም ተራ ንግግር ሳይሆን ሃይማኖታዊ መልዕክት ያለው ነው፤ የመልዕክታቸው ይዘት ደግሞ ነገረ መለኮታዊ ወይም ቲዎሎጂካል ነው። እርሳቸው የተናገሩትን ከቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ አንጻር ስህተት ነው ወይም አይደለም የማለት ሥልጣን ያለው ቤተ ክርስቲያኗ ሥርዓቱን ጠብቃ ያዋቀረችው የሊቃውንት ጉባዔ ነው እንጂ የቲክቶክ ነጋድራሶች፣ የቴሌግራም ፊት አውራሪዎችና የዩትዩብ ተጧሪዎች መሆን የለባቸውም።

የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በዚህ ዓመት የካቲት ወር ባወጣው መረጃ ይህንን ብሎ ነበር፤ “የሊቃውንት ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ኀላፊነት መሠረት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት፣ ሥርዐተ አምልኮ፣ ታሪክና ትውፊት፣ ልሳነ መጻሕፍትና የዕውቀት ሀብታት፣ ጥበባተ አበውና ባህለ ሃይማኖትን መጠበቅና ማስጠበቅ፣ ማስፋፋትና በአግባቡ እንዲተረጐሙ ማድረግ፣ ዐቂበ እምነትን ማጠናከር፣ በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ልዕልና፣ ህልውና፣ የትምህርቷን ጥራትና ርትዐት መጠበቅ ዋንኛ የሥራ ድርሻው ነው።

“በቀድሞ ዘመን መናፍቅና ከሓዲ ሲነሣ፣ ሃይማኖትና ሥርዐት ሲጣስ፣ ዐላውያን የሐሰት ትምህርትን በዐውደ ጉባኤ ሲያሠራጩ፡ ሊቃውንት ከየአሉበት ተሰብስበው ዘርዐ ኑፋቄን አርመው፣ ኀይለ ክሕደትን አድክመው ርትዕት ሃይማኖትን አቆይተዋል። በእኛም ዘመን በርካታ ውይይትና ምክክር የሚያስፈልጋቸው ዐበይት ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ጥያቄዎች በመኖራቸው፤ ያለፈውን ለማጽናት፣ የሚመጣውን ለማቅናት የሊቃውንት መሰባሰብ እጅግ ተገቢ ሆኖ ይገኛል።”

ቤተ ክርስቲያኗ ይህንን የመሰለ በርካታ ዘመናትን የተሻገረ፣ እጅግ የዳበረ አሠራር እያላት ክብሯ በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚገኝ ፍርፋሪና “ዕውቅና (ላይክ)” ቀን ተሌት “በሚለፉ” መጻጉ የዕውቀት ድኩማን መዳፍ ሥር መውደቁ አብሮ ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው።    

አቡነ ገብርኤል ያቀረቡት መልዕክትን በተመለከተ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጎ ለረቡዕ” ቀጥሮት የነበረውን “የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት የሚገኙበትን” ውይይት ወደ አርብ አስተላልፎታል።

በተለመደው አሠራርና በበርካታዎች ዘንድ እንደሚጠበቀው በዚህ ዕለት ሲኖዶሱ ይህንን ስነ መለኮታዊ ጉዳይ በሊቃውንት ጉባዔ እንዲታይ ያደርጋል። ቀጥሎም የሊቃውንቱ ጉባዔ የሚሰጠውን አስተያየት ተመርኩዞም በአቡነ ገብርኤል ላይ ሲኖዶሱ ውሳኔ ያስተላልፋል። እስከዚያ ግን ዝምታ ወርቅ ነው።  

“ወኵሎ አመክሩ፣ ወዘሠናይ አጽንዑ።” “ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ” የሚለውን የቅዱሱን መጽሐፍ መመሪያ መከተል እየተቻለ (1ኛ ተሰሎንቄ 5:21) አስተዳደራዊውንም ሆነ አስተምህሮ ላይ ያነጣጠረውን ጉዳይ ሁሉ በግድ ለጥጦ ፖለቲካዊ ማድረግ፤ በተለይ ደግሞ ከርካሽ የዘር ፖለቲካ ጋር በማያያዝ በግድ እሳት ለማቀጣጠል መሞከር ወይ በሚያምኑት አስተምህሮ ላይ የዕውቀት እጥረት እንዳለ የሚያሳይ ነው ወይም አርነት የሚያወጣውን እውነት ማዳፈን ነው። ሁለቱም ያስኮንናል እንጂ አያጸድቅም።


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Filed Under: Left Column, Religion Tagged With: Abune Gabriel, EOTC, ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤል, የሰባ ገብዣ

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule