• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

April 8, 2025 10:06 pm by Editor Leave a Comment

ሪፖርተር በሌላ ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በኃላፊነት ተጠየቀ፤ ይህንን የጠየቀው የአዲስ አበባ አስተዳደር ሲሆን ሪፖርተር መረጃውን ካላስተካከለ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል። መግለጫው ከዚህ በታች ይገኛል:-

ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ፣

የተዛባና ሚዛናዊነት የጎደለው መረጃን ግልፅ ስለማድረግ፣

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በመጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም “በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የባለድርሻ አካላትን ግንዛቤና ተሳትፎ ማሳደግን” አላማው ያደረገ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ማዘጋጀቱ ይታወሳል። መድረኩ የታለመለትን አላማ እንዲያሳካም በእለቱ የውይይት መድረኩን እንዲዘግቡ በጽ/ ቤታችን ከተጠሩት ከ15 በላይ የሚሆኑ የመደበኛና የዲጂታል ሚዲያዎች ተገኝተው ዘገባቸውን አሰራጭተዋዋል።

 ተቋማችን ከመድረኩ መጠናቀቅ በሁዋላ ባካሄደው የሚዲያ ዳሰሳና ቅኝት ላይ ግን ሪፖርተር ጋዜጣ በትናንትናው እለት ሰኞ መጋቢት 29/ 2017 ዓ.ም “የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የኑሮ ውድነቱ አናታቸው ላይ ወጥቷል” የሚል ርአስ የያዘ ዘገባ ማውጣቱን ተመልክተናል።

በመሠረቱ በጽ/ ቤታችን በተጠራው መድረክ ላይ ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው የመወያያ ርእሰ ጉዳዪ ” የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ላይ የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ” እንጅ የንግድ አሊያም የገቢ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ አልነበረም።

ሆኖም ግን በወቅቱ በመድረኩ ላይ ከተሳተፉት ከ200 በላይ ታዳሚዎች በርካቶች መድረኩ የተዘጋጀበትን ርእሰ ጉዳይ መሠረት በማድረግ ሃሳባቸውን እና አስተያዬታቸውን በነፃነት ያንሸራሸሩበት ሁኔታ ተስተውሏል።

ይሁንና በወቅቱ በመድረኩ ላይ ተገኝቶ ዘገባውን ያወጣው ሪፖርተር ጋዜጠኛ ከመድረኩ አውድ ውጭ በርእሰጉዳይነት ያልተካተ፣ የመድረኩን ሙሉ ስእል የማያሳይ፣ ቁንፅል፣ ስሜት ቀስቃሽ፣ ተጨባጭ መረጃ ላይ ያልተመሰረተ እና ከጋዜጠኝነት የሙያ ስነምግባር ያፈነገጠ ዘገባ ማሰራጨቱ ተቋማችን በህዝብ ዘንድ ያለውን አመኔታ ሆን ተብሎ ለማሳጣት የተፈፀመ እኩይ ተግባር መሆኑን ተገንዝበናል።

በተለይም ደግሞ የሪፖርተር ጋዜጣ ዋነኛ የዜና ርእስ የሆነው አስተያዬት የዜናው ቀዳሚ ርእስ (Headline) በማድረግ ማውጣቱ ስሜታዊነት የተንፀባረቀበት፣ ሃላፊነት የጎደለው እና በምንም አይነት መስፈርት ተቀባይነት የሌለው እንዲሁም የጽ/ቤታችን የህዝብ ቅቡልነትና ተአማኒነት ሆን ተብሎ ለመሸርሸር የተፈፀመ በመሆኑ ሪፖርተር ጋዜጣ ይህንኑ በአስቸኳይ እንዲያርምና ማስተባበያ እንዲያወጣ እያሳሰብን ይህ ካልሆነ ግን ጽ/ቤታችን ህጋዊና አስተዳደራዊ መንገዶችን በመከተል ተጠያቂነትን እንደሚያረጋግጥ በጥብቅ እናሳውቃለን ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: False info, false news, Reporter

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule