• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

April 8, 2025 10:06 pm by Editor Leave a Comment

ሪፖርተር በሌላ ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በኃላፊነት ተጠየቀ፤ ይህንን የጠየቀው የአዲስ አበባ አስተዳደር ሲሆን ሪፖርተር መረጃውን ካላስተካከለ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል። መግለጫው ከዚህ በታች ይገኛል:-

ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ፣

የተዛባና ሚዛናዊነት የጎደለው መረጃን ግልፅ ስለማድረግ፣

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በመጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም “በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የባለድርሻ አካላትን ግንዛቤና ተሳትፎ ማሳደግን” አላማው ያደረገ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ማዘጋጀቱ ይታወሳል። መድረኩ የታለመለትን አላማ እንዲያሳካም በእለቱ የውይይት መድረኩን እንዲዘግቡ በጽ/ ቤታችን ከተጠሩት ከ15 በላይ የሚሆኑ የመደበኛና የዲጂታል ሚዲያዎች ተገኝተው ዘገባቸውን አሰራጭተዋዋል።

 ተቋማችን ከመድረኩ መጠናቀቅ በሁዋላ ባካሄደው የሚዲያ ዳሰሳና ቅኝት ላይ ግን ሪፖርተር ጋዜጣ በትናንትናው እለት ሰኞ መጋቢት 29/ 2017 ዓ.ም “የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የኑሮ ውድነቱ አናታቸው ላይ ወጥቷል” የሚል ርአስ የያዘ ዘገባ ማውጣቱን ተመልክተናል።

በመሠረቱ በጽ/ ቤታችን በተጠራው መድረክ ላይ ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው የመወያያ ርእሰ ጉዳዪ ” የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ላይ የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ” እንጅ የንግድ አሊያም የገቢ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ አልነበረም።

ሆኖም ግን በወቅቱ በመድረኩ ላይ ከተሳተፉት ከ200 በላይ ታዳሚዎች በርካቶች መድረኩ የተዘጋጀበትን ርእሰ ጉዳይ መሠረት በማድረግ ሃሳባቸውን እና አስተያዬታቸውን በነፃነት ያንሸራሸሩበት ሁኔታ ተስተውሏል።

ይሁንና በወቅቱ በመድረኩ ላይ ተገኝቶ ዘገባውን ያወጣው ሪፖርተር ጋዜጠኛ ከመድረኩ አውድ ውጭ በርእሰጉዳይነት ያልተካተ፣ የመድረኩን ሙሉ ስእል የማያሳይ፣ ቁንፅል፣ ስሜት ቀስቃሽ፣ ተጨባጭ መረጃ ላይ ያልተመሰረተ እና ከጋዜጠኝነት የሙያ ስነምግባር ያፈነገጠ ዘገባ ማሰራጨቱ ተቋማችን በህዝብ ዘንድ ያለውን አመኔታ ሆን ተብሎ ለማሳጣት የተፈፀመ እኩይ ተግባር መሆኑን ተገንዝበናል።

በተለይም ደግሞ የሪፖርተር ጋዜጣ ዋነኛ የዜና ርእስ የሆነው አስተያዬት የዜናው ቀዳሚ ርእስ (Headline) በማድረግ ማውጣቱ ስሜታዊነት የተንፀባረቀበት፣ ሃላፊነት የጎደለው እና በምንም አይነት መስፈርት ተቀባይነት የሌለው እንዲሁም የጽ/ቤታችን የህዝብ ቅቡልነትና ተአማኒነት ሆን ተብሎ ለመሸርሸር የተፈፀመ በመሆኑ ሪፖርተር ጋዜጣ ይህንኑ በአስቸኳይ እንዲያርምና ማስተባበያ እንዲያወጣ እያሳሰብን ይህ ካልሆነ ግን ጽ/ቤታችን ህጋዊና አስተዳደራዊ መንገዶችን በመከተል ተጠያቂነትን እንደሚያረጋግጥ በጥብቅ እናሳውቃለን ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: False info, false news, Reporter

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule