• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው!

February 2, 2025 05:32 pm by Editor 1 Comment

የመሠረት ሚዲያ ባለቤት አቶ ኤሊያስ መሠረትን በስም ጠቅሶ የመንግሥት ተከፋይ እንደሆነ የፋኖ አንድ ክንፍ መሪ እስክንድር ነጋ በይፋ ተናገረ። እስክንድር “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ” ሲል አመልክቷል።

እስክንድር ይህን ያለው ከEMS ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ሲሆን፣ መነሻው አቶ ኤሊያስ መሠረት በአባቱ ስም እንደሰየመው በሚገልጸው የግሉ ሚዲያ ላይ እስክንድርን ጠቅሶ “ከመንግሥት ጋር ለመደራደር የተዘጋጀው የፋኖ ክንፍ ንግግሩ በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ እንዲሆን ጠየቀ” በማለት ሪፖርት ማድረጉን ተከትሎ ነው።

አቶ ኤሊያስ “መሠረት ሚዲያ ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ ሚዲያ ውስጥ በሠሩ እና አሁንም እየሠሩ ባሉ ጋዜጠኞች ሚዛናዊ፣ አዳዲስ እና ፈጣን መረጃዎችን ለአንባቢዎች ያደርሳል” በሚል መሪ እሳቤ እንደሚሠራ በማኅበራዊ ገጹ ላይ አስፍረዋል።

እስክንድር ነጋ በቃለ ምልልሱ “ኤሊያስ ስሙን የተከለው ፋክት ቼክ በሚባል የማኅበራዊ ሚዲያ የሐሰት ልጥፎችን አጋልጣለሁ” በሚል መሆኑን ደጋግሞ አመልክቷል። ይህን ካለ በኋላ “እሱ ጋር ሲደርስ ፋክት ቼክ አይሰራም ወይ?” በማለት ጠይቋል።

የቀድሞው የባልደራስ መሪና የአሁኑ የትጥቅ ትግል መሪ እስክንድር ነጋ “የኤሊያስ መሠረት ጭንብል ወልቋል” ሲል አጋጣሚው ማንነቱን ይፋ እንዲሆን ያስቻለ መሆኑን አመልክቷል። ዓላማውም ፋኖን ከሕዝብ ለማጣላትና ተቀባይነቱ ላይ ጥላ ለማጥላት መሆኑ ግልጽ እንደሆነ በዜናው ውስጥ የተሰገሰጉትን ጉዳዮች ተንተርሶ አመልክቷል።

አቶ ኤሊያስ መሠረት በዘገበው መረጃ “… በእስክንድር ነጋ የሚመራው የፋኖ ክንፍ ድርድሩ በውጭ ሀገራት እንዲሆን እየጠየቀ መሆኑ ታውቋል” ብሏል።

“የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደተናገሩት ታጣቂ ክንፉ ድርድሩ በአውሮፓ አልያም በአሜሪካ እንዲደረግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል” ይላል በዜናው መግቢያ።

እስክንድር ራሱ የኢጋድ፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ የአፍሪካ ኅብረት እና የአሜሪካ ተወካዮች መገኘታቸውን ገልፆ እንደነበር የሚያስታውሰው የአቶ ኤሊያስ ዘገባ፣ ምንጮቹ እንደተናገሩ በመግለጽ ከሁለቱም ወገን ቀረቡ የተባሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ጠቁሟል።

ከየትኛው ወገን ያሉ ምንጮች እንደነገሩት ምንም ሳይጠቅስ መረጃውን ያወጣው አቶ ኤሊያስ፤ ከነእስክንድር በኩል ለመንግሥት የቀረቡት ቅድመ ሁኔታዎች ብሎ ከዘረዘረው “ክልሉን ማስተዳደር፣ በፌደራል መንግሥቱ በሥልጣን መወከል” የሚል ይገኝበታል።

“በመንግሥት ዝግ ስብሰባ ላይ ሲያጨቃጭቅ የነበረው የነእስክንድር ክንፍ ዓቅም ጉዳይ ሲሆን ግምገማውም በሀገር ውስጥና በውጭ ተቀባይነትን ለማግኘት መነጋገሩ እንደ  አማራጭ ተወስዷል” ያሉን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጫችን ሸዋ ላይ ድርጅቱ የተሻለ አቅም እንዳለው፣ ነገር ግን ጎጃም ላይ የለም የሚባል ደረጃ ላይ እንደደረሰ መረጃ ቀርቦ ንግግር ተደርጎበታል ብለዋል” ይላል የአቶ ኤሊያስ መረጃ።

አንዳንዶችም ይህ የመንግሥት መረጃ በቀጥታ ከመንግሥት ሰዎች ይሁን ወይም እስክንድርን ከሚቃወሙ የፋኖ ታጣቂዎች ወይም ከዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ተወካዮች ማግኘቱን መጠነኛ ፍንጭ አለመስጠቱ አቶ ኤሊያስ ከነማን ጋር ነው የሚሠራው? የዜናውስ ዓላማ ምንድነው? ብለው እንዲይቁ አድርጓቸዋል።

አቶ ኤሊያስ ይህን ጽሁፍ ባሰራጨበት የፌስ ቡክ ገጹ ላይ አስተያየት ከሰጡ በርካታ ተከታዮች መካከል Menbere Kassaye የተባሉ “ቆይ ሁሉም ይሁን እሺ ። እስክንድር ላይ የተተኮረው ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ መንግሥታት ጋር ቀደም ሲል ግኑኝነት ስለነበረው። የጎጃሙ ተዳክሟል። ጠንከር ያለው የሸዋው ነውን ምን አመጣው? በመንግሥት በኩል እነ እስክንድር ተጠያቂዎችን አሳልፈው እንዲሰጡ ተጠይቀዋል ይላል። እነዛ ፀጉራቸውን አንዠርግገው በሱፍ ተሸፍነው፣ አዲስ አበባ የደረሰችበትን ሲጎበኙ የነበሩት እነ ጃል ሰኚ ማንን አሳልፈው ሰጥተዋል?” ሲሉ ለአቶ ኤሊያስ ዘገባ ጥያቄ አስፍረዋል።

አቶ ኤሊያስ በጻፈው ዜና መንግሥት “ተጠያቂ የሚሆኑ አባላቱን አሳልፎ መስጠት” የሚል ቅድመ ሁኔታ ማቅረቡ፣ እስክንድር የፋኖን ታጋዮች አሳልፎ ለመስጠት ሊስማማ እንደሚችል አድርጎ በውስጥ አዋቂዎች ስም ዜናው ውስጥ የተካተተ መርዝ እንደሆነም በርካቶች አመላክተዋል።

ዜናው መለስ ብሎ “ቢያንስ ሸዋን ማ(ጠ)ቃለሉ እንደ ጥሩ ዕድል በመታየቱ እና የድርድር ዝርዝር መረጃም የሚቀበሉ ዓለም አቀፍ ተቋማትም በመንግሥት የንግግሩ ቦታ ስለተጓጓዙ ውይይቱ ተደርጓል” ሲል ድርድር ስለመደረጉ በርግጠኛነት ያወራል። እስክንድር ግን “አንድም የመንግሥት ሰው ድርሽ አላለም፤ የተነጋገርነው ዕርዳታ በሚገባበት አግባብ ነው። ረሃብ አለ። ሕዝብ ድጋፍ ማግኘት አለበት። … ” በማለት የንግግሩን ዋና ነጥብ ያለውን ይገልጻል።

ሌላ Bitania Alula የተባሉ አስተያየት ሰጪ ስለ ሚዲያዎች አመሠራረት ካብራሩ በኋላ “… እራሱን [መሠረት ሚዲያ] ብሎ የሚጠራ ተቃዋሚ ዘመም ሚዲያ የፃፈውን ካያችሁት በተመሳሳይ መልኩ ከላይ የፃፍኩትን የውጭ ሚዲያዎች ዓይነት ነው። “መሠረት ሚዲያ” የፃፈው የውሸት ዘገባና ፍጹም ጎጃም ዘመም ዘገባ ነው። ከዚያ ይልቅ አስረስ ማረ ለፕሮፓጋንዳ ብሎ የፃፈውን ዘገባ እንደወረደ ያቀረበ ነው። ዘገባው በአጠቃላይ የተፃፈው በእነ [አስረስ ማረ] ነው። አጠቃላይ ምንም ድርድር በሌለበት ሁኔታ “የእስክንድር ቡድን ተደራደረ” በሚል የውሸት ዘገባ ሽፋን የሰጠው የእነ አስረስ ማረ ዘመም ደጋፊ ሚዲያ ነው” ብለው በጽሁፉ ግርጌ ጽፈዋል።

አቶ ኤሊያስ በዘገባው “ተንታኝ” ያለውን ሰው ጠቅሶ “… አሳሳቢው ጉዳይ አሁንም ልክ እንደነ ጃል ሰኚ እንዳይሆን ነው፣ ሙሉ ሰላም ለማምጣት የተወሰነ ቡድን ሳይሆን ሁሉንም አካታች መሆን አለበት” ሲሉ “ተንታኙ” ለአቶ ኤሊያስ መናገራቸውን መረጃው ጠቅሷል። ይህንን እስክንድርን ከጃል ሰኚ ጋር የማነጻጸሩን አካሄድ ያወገዙ ግን እጅግ ብዙ ናቸው። ጃል ሰኚ በአሥር ሺህ የሚቆጠር ሠራዊት ይዞ መግባቱ አይዘነጋም።

ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች አቶ ኤሊያስ መሠረትን በቀድመው የህወሃት/ትህነግ አፋኝ አገዛዝ ዘመን የነበረውን የ“ጋዜጠኛነት” ሚና በማንሳት ይከሱት እንደነበር ያስታወሱ “የኤሊያስ መሠረት ጭምብል ዛሬ ወልቋል” በማለት እስክንድር የተናገረውን ያጠናክራሉ። ድጋፋቸውንም ይሰጣሉ።

ስዩም ተሾመ በአቶ ኤሊያስ ላይ በተደጋጋሚ በማስረጃ ማቅረቡን ጠቅሰው በዘመነ ትህነግ፤ የውጭ ሚዲያዎች ለትህነግ ጥሩ ሽፋን እንዲሰጡ የማመቻቸት፣ ትህነግን የሚደግፍ ሪፓርት በማዘጋጀት እሱ ራሱ ይሠራበት በነበረ የውጪ ሚዲያ በማሳተም፣ በወቅቱ ሕዝብ ላይ በደል ሲፈጸም፣ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ተቋማዊ ዘረፋ ሲፈጸም በውጭ ሚዲያዎች ከለላ በመስጠት አቶ ኤሊያስ ለሚሠራው ሥራ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል ዳጎስ ክፍያ ይፈጸምለት እንደነበር ለማስታወስ የተገደዱ ተቃውሞ እያሰሙ ነው።

እስክንድር ድርድር ባያደርግም ንግግር መደረጉን፣ ንግግር መደረጉ ወደ ቀጣይ ድርድር እንደሚያመራ የጠቆሙ ክፍሎች፣ አቶ ኤሊያስ አየር መንገድ ውስጥ እስር ቤት እንደነበር እያወቁ ከተወልደ ገብረመድኅን ጋር በነበረው የጥቅም ግንኙነት ምክንያት ዝም በማለት፣ ለዚህም ውለታው በአየር መንገዱ በጀት ሞሪሺየስ የጫጉላ ሽርሽር ማድረጉን ያስታውሳሉ። ተወልደ ወደ አሜሪካ ሲኮበልልና በዴልታ አየር መንገድ ውስጥ ሥራ ማግኘቱን ከተወልደ ቤተሰብ ቀድሞ መረጃውን ይፋ ያደረገው አቶ ኤሊያስ መሆኑን እንደ መረጃ ያቀርባሉ።  

ከለውጡ በኋላ በርካታ ድርጅታዊ ጥቅም በማጣቱ ወደ ተቃዋሚነት ማደጉን የሚገልጹና በርካታ መረጃዎች ከአየር መንገዱ ሲወጣና በስዩም ተሾመ በኩል ሲሰራጭ እንደነበር የሚገልጹ “አቶ ኤሊያስ ከፓርቲና መንግሥት ጋር ተሰናስሎ በምሥጢር በመሥራት በዘርፉ በቂ ልምድና የዳበረ ኔትዎርክ ያለው፣ እርቅና ሰላም ፍጹም የማይመቸው የሚዲያ ታጋይ ነው” ይሉታል።

ይህንኑ ልምድ አሁን በተቃዋሚ ስም ግን በድብቅና ረቂቅ በሆነ መንገድ በሥልጣን ላይ ካለው መንግሥት ጋር እየሠራበት እንደሆነ ጠቋሚ ነገሮች አሉ የሚሉ ወገኖች፤ አቶ ኤሊያስ በእስክንድር ላይ ያወጣው ይህ መረጃ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ይጠቅሳሉ። ውጤቱም ሸኔን ከፋፍሎ እንደተሠራው ሥራ በቋፍ ላይ ያለውን የፋኖን አደረጃጀት ከፋፍሎ መንግሥትን የመጥቀም አደገኛና መሠሪ ዜና ነው አቶ ኤሊያስ የሠራው በማለት ይከስሳሉ።

በእስክንድር ሥር ያለው ታጣቂ እጁን ከሰጠ ሌሎቹ ፋኖዎች እጅ አንሰጥም የሚሉበትን ምክንያት ያሳጣል፤ በዓለምአቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድም ዕርቅን አለመቀበል ተቀባይነት ስለሌለው በጎጃም፣ በጎንደርና በወሎ የሚገኙ የፋኖ አደረጃጀቶችን ለከፋ መከፋፈል የሚዳርግ መርዝ የተቀላቀለበት ዜና ነው አቶ ኤሊያስ የዘገበው ይላሉ። 

አቶ ኤሊያስ ግን ለራሱ የሚሰጠው ግምትና የጋዜጠኛነት ማዕረግ ሰሞኑን በራሱ ገጽ “በጀት = 0 ብር፤ የሰራተኛ ብዛት = 1፤ በጎ ፈቃደኞች = 3፤ ተፅእኖ = 100 ፐርሰንት፤ ሁሌ እኮራለሁ!” በማለት ነው። ይህን የገጽታ ግንባታ ራሱ የሰጠ ሲሆን በዚሁ ልጥፍ ሥር በርካቶች “አይተኬ፣ አይበገሬ፣ አንድ ለእናቱ…” በሚል አበባ በትነውለታል። አፋቸውን በጃቸው የጫኑም አሉ።

አቶ እስክንድር መሠረት ሚዲያንና አቶ ኤሊያስን በስም ይጠቀሱ እንጂ መረጃ ለማጣራት “እሁድ እስኪያልፍ ምን አጣደፋቸው” ሲል ሌሎች በተመሳሳይ የዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደነገሯቸው ገልጸው የዘገቡትን “ሚዲያዎች” ወቅሷል። እሁድ ቢሮ ዝግ በመሆኑ ቢያንስ በድርድሩ ተገኙ የተባሉትን ዓለምአቀፍ ተቋማት ሰኞ ቢሮ እስኪከፈት ጠብቀውና እነርሱ ጠይቀው ለማጣራት አለመሞክራቸውን የገለጸው እስክንድር፣ “ይህ የጋዜጠኝነት ሀ፣ ሁ፣ ነው” ብሏል።

እስክንድርን ያናገሩት የEMS የተቃዋሚ ጎራ አባላት አቶ ፋሲልና አቶ ወንድማገኝ ዋናው ዓላማቸው እስክንድር “ድርድር አልተደረገም” እንዲል ስለነበር በመሠረት ሚዲያና በሌሎች ላይ ለቀረበው የተዓማኒነት ጥያቄ ብዙም ትኩረት እንዳልሰጡ ከውይይቱ ለመረዳት ይቻላል።

አቶ ኤሊያስን እናውቀዋለን የሚሉና ከህወሃት/ትህነግ ዘመን ጀምሮ በጋዜጠኛነት ስም ሸፍጥ ሲሠራ የኖረ ነው በማለት የሚከሱት፤ በኬኒያ የሚያደርገውን፤ በቀድሞ ጊዜ ግንኙነት ከመሠረተባቸው የውጪ ሚዲያ አካላትና የትህነግን ዓላማ በማስፈጸም ትልቅ ድጋፍ ሲሰጥ የነበረውን፤ ከቀድሞ የአየር መንገድ ኃላፊ ተወልደ ገብረመድህን ጋር አቶ ኤሊያስ የነበረውን ግንኙነት በመጥቀስ አሁን ደግሞ በተቃዋሚ፣ በ“ፋክት ቼክ” አድራጊነትና በ“ጋዜጠኝነት” ስም እንደ ቀድሞው በድብቅ ለመንግሥት የሚሠራ መሆኑን ይህ ስለ እስክንድር ድርድር ያወጣውን መንግሥት ዘመም መረጃ በዋቢነት ይጠቅሳሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: Elias Meseret, Eskinder Nega, Fano, Meseret Media

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    February 4, 2025 09:57 pm at 9:57 pm

    መቼ ነው ከፓለቲካው ዓለም እርቀን ቆም ብለን ህይወትን የምናጣጥመው? መቼ ነው በጎሳና በብሄር ፓለቲካ መጠፈራችን ቀርቶ ፍጥረትን በማድነቅ ፓለቲካ ያልበረዘው ንጽህ አየር የምንስበው? ሃበሻ በደረሰበት ሲራኮት፤ ሲካሰስ፤ ሲደባደብ፤ በዚህም በዚያም ሲጠላለፍ እድሜ ልኩን መኖሩ እንደ ስልጣኔ ቆጥሮ በየዘመናቱ አንድ በአንድ ላይ አካኪ ዘራፍ ያዙኝ ልቀቁኝ ይላል። የምንኖረው የእድሜ ልክ ስንት ነው? ለዚህች አጭር ዘመን ይህ ሁሉ ገመና።
    በቅርቡ በርሊን ከተማ የሚገኝ ሰው ደወለና ምነው ጠፋህ አለኝ። አይ አንተ እንጂ እኔ አልጠፋሁም ስል። አይ እኔማ ወደ ሃገር ቤት ሂጄ ነው አለኝ። እንዴ ሃገር ቤት ሄድኩ ካልከኝ እኮ 3 ወራት አልሞላም ስለው እየሳቀ አዎን እንዳንተ እንደ ደብተራ ደብተር ላይ ተደፍተን አንውልም የሚሰሩ እጆቻችን ይሰራሉ ሲለኝ ሃገር ቤት ምን እየሰራህ ነው አልኩት። እባክህ ቤት ጀምሬአለሁ አለኝ። አዲስ ቤት ገዛሁ ካልከኝ እኮ ዓመት አልሞላም ስለው አዎን ሌላ ነዋ ሲለኝ ተገረምኩና። እንዴት ባለ ሂሳብ ነው አንተ የጀርመን መንግስት ጥገኛ ሆነህ ያለሥራ የተቀመጥክ ሰው ባለ ሁለት ቤት የምትሆነው? ቀደም ብዬ እኮ እጃችን ይሰራል ብዬህ ነበር አልገባህም መሰል ሲለኝ። ወንድሜ እኔ ታክስ የማይከፈል ገቢና ሥራ ሌብነት እንጂ ሥራ ነው አልልም በማለት ትንሽ ተፏገርንና በመጨረሻም የህዝቡን መከራ የምታበዙት እናንተ ናችሁ አልኩት። እንዴት አለ። ሰርቃቹሁም፤ ተበድራችሁም እዚያ ሥፍራና ቤት እየገዛችሁ ኗሪውን የጎዳና ሰው ያደረጋችሁ። ነገርየውን ሁሉ ያስወደዳችሁት አንተና መሰሎችህ ናቸሁ። እኔ መንግስት ብሆን እንደ እናንተ ላለው 100% ታክስ ነበር የምጥለው ስለው ብዙ ከተነፈሰ በህዋላ እንዴት አለኝ። የምትገዛው ቤት 10 ሚሊዪን ብር ካወጣ 20 ሚሊዪን አስከፍልሃለሁ። በ 10 ሚሊዪን ለሁለትና ለሶስት ቤተሰቦች ቤት እሰራበታለሁ። ቆጣ አለና ይሄ ሶሻሊዝም ነው ኮሚኒዝም አለኝ። ሁለቱም አይደለም። ፍርድ ላጡ መቆም ይባላል ስለው ዘጋብኝና ጫወታችን አበቃ። ስንቱ የሃበሻ ሌባ ነው በካናዳ፤ በአሜሪካ፤ በአውሮፓና በሌሎችም የሃገሪቱ ክፍሎች በመንግስት ቤት እየኖረና እየተደጎመ ሙሉ ስራው ሃገር ቤት የሆነ? ህሊና የሌለው ትውልድ! ሃፍረት የማይሰማው የገፋፊ ስብስብ።
    ዛሬ በሃገራችን ኑሮ ከመወደድ የተነሳ ህዝባችን ጾሙን እያደረ ነው። በዚያ ላይ በዚህም በዚያም የታጠቁ ሃይሎች ሲያዋክቡትና ሲገድሉት አልፎ ተርፎም እንደ ከብት አግደው ገንዘብ ክፈሉ ሲሉት ስሰማና ሳነብ ሰው እንስሳ መሆኑን ለመረዳት ጊዜ አይፈጅብኝም። በሰው እንባና ደም የእለት እንጀራን ማግኘት። አድነኝ ነው የሚያሰኝ። መንግስት ተብየው የሚያስረው የሚገርፈው ከአስከሬን ጋር አብሮ የሚያሳድረው ለሃገርና ለወገኑ ያደሩትና የሰላም ሰዎችን ነው። ለምን ይሆን በቅርቡ ከእናቷ ፊት ታፍና ዘብጥያ የወረደችው ምሥራቅ ተረፈ? በእውነት ለመንግስት ስልጣን አስግታ ወይስ ሌላ የጊዜው አለቆች ያልወደድላት ጉዳይ አለ? ከክፋት መሰላል ወደ ሌላ የከፋ መሰላል እየተሸጋገርን ኖረናል ብለን እንሞታለን። መኖር አይበለው። ሁሌ ኡ ኡታ ሁሌ ለእኔ ብቻ። ሃገር ሲያረጅ ጃርት ያበቅላል ያሉት ለካ ለዚህ ነው። ምንም የሃብት ክምር ቢኖርህ ከሞት አያድንህም። የሰው መኖር የሚለካው ለሌላው በመኖሩ ነው። እንደ አሳማ የተገኘውን ሁሉ በልቶና ጠጥቶ መድለብ ለፍርድ ቀን ራስን ማዘጋጀት ይሆናል። ያች ቀን ስትመጣ ደግሞ የሚሽራት ምድራዊ ሃይል አይኖርም።
    ማነው ለትግራይ ህዝብ የቆመ፤ ስቃዪን የተካፈለ? ጠበንጃ አንጋቾች? በጭራሽ? ማነው ለአማራ ህዝብ መከራ ምንጩ ፋኖና ተፋላሚው መንግስት አይደሉምን? ማነው ለኦሮሞ ህዝብ ችግርና መከራ ተጠያቂው? ኦነግና መሰሎቹ አይደሉም? ግን በየዘሩ ለተሰለፈ ተውሳክ ሰውን በሰውነት አቻ አድርጎ የማየት አይኑ ፈሷልና ሁሉም በየጎጡ ያቅራራል። በመሃል ለሰላም ለደስታ ለነጻነት ቃል የተገባለት ህዝብ ያልቃል። ለገባው ከጦርነት ሰላም ይመረጣል። ዝንተ ዓለም ጠበንጃ ይዞ እንዘጥ እንዘጥ ከማለት ጥቂትም ቢሆን በሰላም ሰርቶ መኖር ይመረጣል። መንግስት ታጣቂዎችን ሲኮንን እነርሱ ብልጽግናን ሲሞግቱ ይኸው ህዝባችን በመሃል አለቀ። ኸረ ተው ልብ ግዙ። የዘር ፓለቲካ ለማንም አይጠቅምም። በሉ በዚህች የእንግሊዘኛ ግጥም ልሰናበታችሁ። ለገባው ይግባው።

    The fruits of labor, once so near,
    Are swept away, replaced by fear.
    Each coin we save, each note we hold,
    The worth they have, in time, grows old.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule